Tuesday 5 November 2013

ዶላር ለመሰብሰብ ወደ ሙኒክ ያቀናው የህወሀት ቡድን አልቀናውም November 3, 2013


በአባይ ግድብ ስም ቦንድ በመሸጥ ጠቀም ያለ ዶላር ለመሰብሰብ አቅዶ ወደ ጀርመን፣ ሙኒክ ከተማ የተንቀሳቀሰው የህወሀት/ኢህአዴግ መልዕክተኛ ቡድን ከኢትዮጵያውያን የደረሰበትን ከፍተኛ ተቃውሞ መቋቋም ሳይችል ቀርቶ ያሰበውን ዶላር ሳይሰበስብ ቀርቷል።
ኢትዮጵያውያኑ የእለቱ መሪ መፈክራቸው አድርገውት የዋሉት እየተለመደ የመጣውን “ወያኔ ሌባ” የሚለውን መፈክር ሲሆን የታሰሩ ጋዜጠኞችና የፖለቲካ እስረኞችም እንዲፈቱ ጠይቀዋል።
ቀደም ሲል የህወሀት/ኢህአዴግ ቡድን የቦንድ ሽያጩን ሊያከናውን አቅዶ ከነበረበት የሆቴል አዳራሽ ባለቀ ሰዓት ተባሮ ነው ዛሬ ኢትዮጵያውያኑ ተቃዋሚዎች ተቆጣጥረውት የዋሉትን አዳራሽ እመንደር ውስጥ ሊከራይ የተገደደው።