Thursday 12 December 2013

የተከበሩ አፍሪካዊ ኔልሰን ማንዴላ ስንብት!

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም ከነጻነት ለሀገሬ
ኔልሰን ሮሺስላሽላ ማንዴላ ለነጻነት የሚያደርጉትን ረዥሙን ጉዞ እ.ኤ.አ በ2013 መገባደጃ ወር ላይ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ደመደሙ፡፡
ፀሐይ የደቡብ አፍሪካን ሕዝብ ከአፓርታይድ የጭቆና አገዛዝ ነጻ ባወጡት ኔልሰን ማንዴላ ላይ የመጨረሻ ማህለቋን ጣለች፡፡ ኔልሰን ማንዴላ ፈለግ አቸዉን ትተውልን አልፈዋል፡፡ በጥላቻ በተዘፈቀው ዓለም፣ በማያቋርጥ ሁኔታ በፍርሃት ተሸብቦ በሚገኘው ህዝብ፣ በአምባገነኖች በሃይል ተይዞ በሚሰቃየው ብዙሀን ህዝብ እና ስሜት አልባ ተደርጎ በተያዘው ህዘብ ላይ የፀሐይን ማህለቅ ለመጣል የኔልሰን ማንዴላን ፈለግ መከተል አለብን፡፡ በምንም ዓይነት መልኩ አንፈራም፣ የኔልሰን ማንዴላ መንፈስ ከአጠገባችን ናትና!
ኔልሰን ማንዴላን በፍጹም አግኝቻቸው አላውቅም፣ ባገኛቸው እንዴት ደስ ባለኝ! ለማግኘት የምፈልገው ደግሞ በዓለም ላይ እጅግ ከተከበሩት ሰው ጋር ተገናኝቸ ነበር በማለት ለስሜቴ ክብር ለመስጠት አይደለም፣ ነገር ግን ለአፍሪካውያን ክብርን፣ ኩራትን እና ሞገስን ላጎናጸፉት እኒያን ጀግና ኔልሰን ማንዴላን በዚህ አጋጣሚ አመሰግናለሁ የምትለዋን ቃል በትሕትና  ለማቅረብ እንጅ፡፡
ኔልሰን ማንዴላ ድልድይ ቀያሽ ነበሩ፡፡ ዘርን፣ ጎሳን እና የህብረተሰብ መደብን የሚያገናኙ ድልድዮችን ገንብተዋል፡፡ ኔልሰን ማንዴላ እሳት አጥፊ ነበሩ፡፡ በዘር እና በጎሳ ጥላቻ ተቀጣጥሎ የነበረውን ቤት እሳት በማጥፋት በደቡብ አፍሪካውያን ዘንድ እውነት እና ዕርቅ እንዲሰፍን አድርገዋል፡፡ ኔልሰን ማንዴላ መንገድ ቀያሽ ነበሩ፡፡ በረዥሙ ጉዞ ወደ ነጻነት የሚያደርሱ በስም “ደግነት“ እና  “ዕርቅ“ የሚባሉ ሁለት መንገዶችን በመገንባት የተናገሩትን በተግባር አሳይተዋል፡፡ ኔልሰን ማንዴላ የህንጻ ንድፍ ነዳፊ/architect ነበሩ፡፡ በአፓርታይድ አመድ ላይ በብዙሃን ዘር ዴሞክራሲ የተዋበውን ማማ ገንብተዋል፡፡ ኔልሰን ማንዴላ የልዩ ተሰጥኦ ባለቤት ነበሩ፡፡ ጥቁር እና ነጭ እርግቦችን በአንድ ጊዜ በመልቀቅ በነጻነታቸው ተንፈላስሰው እንዲበሩ አድርገዋል፡፡ ኔልሰን ማንዴላ ለዘላለም የሚኖር የለውጥ ሐዋርያ ነበሩ፡፡ ጥላቻን በፍቅር፣ ፍርሃትን በወኔ፣ ጥርጣሬን በእምነት፣ ታጋሽየለሽነትን በሩህሩህነት፣ ቁጣን በመግባባት፣ ጥላቻን በስምምነት፣ እና ቅሌትን በክብር የሚለውጡ ነበሩ፡፡
ኔልሰን ማንዴላ በዘመናዊው የህብረተሰብ ታሪክ ሂደት ውስጥ እንከን ባለባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ዘንድ እንከንየለሽ በመሆን እንከን ያላቸው ሰው ነበሩ፡፡ ሙሉ በሙሉ በዘር፣ በጎሳ እና በመደብ በተከፋፈሉ ወገኖቻቸው ላይ አንከንየለሽ ማህበርን ለማምጣት ጥረት አድርገዋል፡፡ ነጭ ደቡብ አፍሪካውያንን በልቦቻቸው ውስጥ ዘልቀው ከገቡት ከአፓርታይድ መጥፎ ገጽታ እና ከአስቀያሚ ዘረኝነት አድነዋቸዋል፡፡ በጥቁር ደቡብ አፍሪካውያን ልቦች እና ነፍሶች ውስጥ ይንከባለሉ የነበሩትን የበቀል ጥላቻዎች  ወደ ፍቅር እና ወንድማዊነት ስሜት ቀይረዋቸዋል፡፡ ኔልሰን ማንዴላ በእራሳቸው ልብ ውስጥ የፍቅር፣ የስምምነት እና የዕርቅ ጓሮን አልምተዋል፡፡ ኔልሰን ማንዴላ እጅግ በጣም እንከን ለበዛባቸው የማህበረሰብ ክፍሎች ምክራዊ መልዕክት እንዲህ በማለት አስተላልፈዋል፣ “ሰው ከጠላቱ ጋር ሰላም ለማውረድ ከጠላቱ ጋር አብሮ መስራት አለበት፣ እና ያ ጠላት የነበረው ወዳጅ ይሆናል“፡፡ ሌሎቻችን ግን ጠላትን በመግደል ሰላም እናመጣለን ብለን እናምናለን!
ማንዴላ መጥፎ ነገር ለማድረግ ጥሩ ጊዜ የለም በማለት ዓለምን አስተምረዋል፣ ሆኖም ግን “የሚመጣው ጊዜ ሁሉ ጥሩ ነገር ለማድረግ መሆኑን ማመን አለብን“፡፡  ለደቡብ አፍሪካውያን እና ለመላው አፍሪካውያን እንዲህ በማለት አስተምረዋል፣ “ለቆንጆዋ ደቡብ አፍሪካ እንዲሁም ለመላዋ አፍሪካ ህልሞች ካሉ እነዚህ ህልሞች ወደ ተግባር እንዲሸጋገሩ የሚያስችሉ መንገዶችም አሉ“፡፡ ከእነዚህ መንገዶች ሁለቱ “ደግነት” እና “ይቅርታ አድራጊነት” በመባል ሊሰየሙ ችለዋል፡፡ እነዚህን የማንዴላን ቃላት ለዘላለም ስናስታውሳቸው እንኖራለን፡፡ የሮበርት ፍሮስትን አባባል በመዋስ፣
እኛ …ይህንን በጥልቅ ተንፍሰን እንናገራለን፣
የትም በጊዜዎች እና በጊዜዎች ቢሆንም፣
ሁለት መንገዶች ሁለት መንታ መንገዶች በደን ጫካ ዉስጥ ነበሩ
ማንዴላ ጥቂትሰዎች የተጉአዙበትን መንገድ ወሰዱ፣
እና ሁሉንም ልዩነት ያመጣው ይኸ ነው፡፡
በደቡብ አፍሪካ ሁሉንም የመልካም ስራ ልዩነት ያመጡት ደግነት እና ይቅርታ አድራጊነት ናቸው፡፡
ሃያ ሰባት እና ከዚያም በላይ በትንሽ እስር ቤት አድሚያቸውን ያሳለፉ ሰው ስለ ሰው ልጅ ነጻነት ትክክለኛ ትርጉም እንዲህ በማለት አስተምረውናል፣ “ነጻ መሆን እግረሙቅን ከእጅ ወይም ከእግር ማስወገድ አይደለም፣ ነገር ግን ሌሎችን በማክበር እና ነጻነታቸውን በማራመድ የመኖር መንገድ ነው“ ፕሬዚዳንት ክሊንተን “በተሻለው ቀን ሁሉ ሁላችንም ኔልሰን ማንዴላን መሆን አለብን“ ሲሉ እውነትም ልክ ናቸው፡፡ ነገር ግን ዛሬ መጥፎው ቀናችን ነው፣ ምክንያቱም ኔልሰን ሮሺስላሽላ ማንዴላ አብረውን የሉምና! ዛሬ ማንዴላን ለዘላለም ተነጥቀናል!
ኔልሰን ማንዴላን በፍጹም አላገኘኋቸውም፣ ነገር ግን ብዙ ንግግሮችን ከእርሳቸው ጋ አግኝቻለሁ፡፡ በእርግጥ ሁሉም ምዕናባዊ ነበሩ፡፡ ማንዴላ ግድየላቸውም፣ እንዲህ ብለዋል፣ “በእውኑ ዓለም በእርግጠኝነት ከማየው ይልቅ ራዕይዬ የበለጠ በመጓዝ ምዕናባዊ ኃይሌ ስሜትን/አዕምሮን የሚፈታተን ሀሳብን ይፈጥራል“፡፡ ነገር ግን የኔልሰን ማንዴላን ራዕይ በአዕምሯችን ዓይን ከተመለከትነው የሀሰት ምዕናባዊ ሀሳብ አይደለም፡፡ ከኮሎኒያሊዝም፣ ከኢምፔሪያሊዝም እና ከአፓራታይድ አመድ ነጻ የወጣችውን ጀግና፣ በእራስ የምትተማመን አዲሲቷን የፍቅር አፍሪካ ራዕያቸውን እናያለን፡፡ በኔልሰን ማንዴላ ራዕይ የምትመራዋን አዲሲቷን አፍሪካ ለመገንባት ምዕናባዊ ሀሳባችንን አሁኑኑ መጠቀም አለብን፡፡
አንዳንድ ሰዎች ትልቅ ሆነው ይወለዳሉ፣ ሌሎቹ ደግሞ የትልቅነት እምነትን ይላበሳሉ እየተባለ ይነገራል፡፡ ምንልባትም አንዳንዶቹ ታላቅነትን በአጋጣሚ ይጎናጸፋሉ፡፡ ኔልሰን ማንዴላ ታላቅ ነበሩ ምክንያቱም ይሞክሩ ነበር፣ ይሞክሩ ነበር እና ይሞክሩ ነበር፡፡ ማንዴላ እንዲህ በማለት አስተባብለዋል፣ “እኔ ነብይ አይደለሁም፣ ነብይን ሁልጊዜ እንደሚሞክር ሃጢያተኛ ካልቆጠራችሁት በስተቀር“፡፡ ሁላችንም ሃጢያተኞች ሁልጊዜ እስከሞከርን እና እጃችንን እስካልሰጠን ድረስ የሚሞክር ሃጢያተኛ ነብዮች ብንባል ኔልሰን ማንዴላ ሞተውም ቢሆን ህያው ምስክርነታቸውን ይሰጣሉ፡፡
ለኔልሰን ማንዴላ ከፍተኛ የሆነ ሃዘን እና አድናቆት የሚደረግላቸው ናቸው፡፡ በከፍተኛ የስልጣን እርካብ ላይ ያሉ በዓለም ታላላቅ ከተሞች የሚገኙ መሪዎች ስለ ኔልሰን ማንዴላ የነጻነት ታጋይነት እና የሰብአዊ መብት ተሟጋችነት ያወሳሉ፡፡ የደቡብ አፍሪካ መሪዎች ስለኔልሰን ማንዴላ ከግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ በአፍሪካ ብሄራዊ ኮንግረስ አመራር ሰጭነት እና የማያቋርጠውን እና ኢሰባዊ የነበረውን የአፓርታይድ ገዥ አካል በሰላማዊ እና በትጥቅ ትግል ለመጣል የተጫወቱትን ሚና በማድነቅ ይናገሩላቸዋል፡፡ ተራው የደቡብ አፍሪካ ህዝብ ኔልሰን ማንዴላን በኩራት የሀገራቸው አባት እንደሆኑ አድርገው ይናገራሉ፡፡ ስለኔልሰን ማንዴላ የኖቤል ተሸላሚነት፣ ስለዓለማቀፋዊ የሰብአዊ መብት እና ስልሰው ልጅ ሰብዕና ተከራካሪነት፣ ስለማህበራዊ ፍትህ እና ሰላም ለማስፈን በዓለም አቀፍ ደረጃ ስላደረጉት ያልተቋረጠ ትግል የዓለም ህዝብ አድናቆቱን ይገልጻል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ የማንዴላ ተችዎች ጭቃ ጅራፍ ይዘው ይላሉ፡፡ ለዕርቅና ለሰላም ያላቸው የማይታጠፍ አቋም ለደቡብ አፍሪካ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ሃይል ሚዛን የሚያስፈልገውን አብዮት እንዳይመጣ ይከላከላሉ በማለት ይተቿቸዋል፡፡ ማንዴላ ለአፓርታይድ ጨቋኖች ብዙ ትኩረት በመስጠት ከእነርሱ ግን በመልሱ የወሰዱት ነገር አናሳ ነው በማለት ይታቻሉ፡፡ ከአፓርታይድ አለቆች ጋር በእርቀሰላሙ ጉዳይ ላይ ጥረት በማድረግ የመለሳለስ እና ሃይለኛ ሆነው ያለመውጣት ሁኔታ እንዳለባቸው ይተቻሉ፡፡ ተቺዎቻቸው በመቀጠልም አፓርታይድ አሁንም ቢሆን በኢኮኖሚው በኩል ሃያልነቱን እንደያዘ እና ሙስና በአፍሪካ ብሄራዊ ኮንግረስ የፖለቲካ ህይወት ውሰጥ እየተስፋፋ የመጣ ነቀርሳ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ የማንዴላን ውድቀት በተጨባጭ ሁኔታ ለመተቸት አልቻሉም፣ ነገር ግን እነርሱ በምዕናባቸው ሆኖ የሚታያቸውን በማቅረብ ይተቻሉ፡፡ እንዲህም ይላሉ፣ አፓርታይድ ከሞተ ከሁለት አስርት ዓመታት በኋላ በደቡብ አፍሪካ በከተሞች እና በገጠሮች የሚኖረው ህብረተሰብ ኑሮ ልዩነቱ በጣም ጠባብ ነው፡፡ ማንዴላ ስለዕርቅ ጉዳይ በትጋት የሰሩት ብዙም ለውጥ አላምጣም ይላሉ፣ እንዲያውም ደቡብ አፍሪካ ቀደም ሲል እንደነበረው በዘር ተከፋፍላ ትገኛለች ይላሉ፡፡ ሌሎቹ ተቺዎች ደግሞ ማንዴላ ስህተት ሰርተዋል፣ የገቧቸውን ቃልኪዳኖች አላከበሩም ይሏቸዋል፡፡ በከተሞች የሚገኙት ያጡት እና የነጡት በዕየለቱ የዕለት ዳቦ እየለመኑ የሚተዳደሩት ስለማንዴላ መልካም ነገር አይናገሩም፣ ምክንያቱም ማንዴላ አዲስ በፈጠሯት ደቡብ አፍሪካ እራሳቸውን እንደተቆለፈባቸው አድርገው ይቆጥራሉ፡፡ በገጠሩ የሚኖሩት እና በመገለል ብዛት እየተሰቃዩ ያሉት ህዝቦች ህይወታቸው ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ለውጥ ያላመጣ መሆኑን ይከስሳሉ፡፡
የማንዴላን “የሃጢያት ነብይነት” የተጋነነ ትችት አንድ ነገር ልነግራቸው እፈልጋሉ፣ “እራሳችሁን እረገብ አድርጉ! በማንዴላ ላይ ከባድ ትችት ከመሰንዘራችሁ በፊት 27 ዓመታት ሙሉ በእግር ብረት ታስረው የቆዩትበን የጫማ ጉዞ በመከተል እስቲ አንድ ማይል እንኳ ለመጓዝ ሞክሩ፡፡ በከተማ እና በገጠር ለነጻነታችሁ ስትታገሉ ለቆያችሁት ልጠይቃችሁ የምፈልገው ነገር ማንዴላን ልዩ ኃይል እንዳለው መልዓክ አድርጋችሁ አትቁጠሩ ነገር ግን ማንዴላ እንደማኝኛችሁም ሁሉ ሰው ናቸው፡፡ ማንዴላ ነጻነትን ማጣት ምን ማለት እንደሆነ ብቻ ሳይሆን ክብርን እና ማንኛውንም ለህይወት አስፈላጊ የሆኑ ነገሮችን ሁሉ በሚገባ የሚያውቁ ሰው ናቸው፡፡ ለማናቸውም ባዶ ተስፋዎች እና ተስፋቢስነቶች እንዲሁም ተፈጻሚነትን ላላገኙ ቃልኪዳኖች ኔልሰን ማንዴላን ይቅርታ እንዲያደርጉላቸው እጠይቃለሁ፡፡ ሰዎች ማንዴላን እንደ መላዕክ መቁጥር የለባቸውም፣ ነገር ግን ለሰው ልጅ ጥሩ የሆኑ ነገሮችን ሁሉ ለማድረግ የሚሞክሩ ሆኖም ግን ከፍተኛ ጥረትን ቢያደርጉም ሁሉም ነገር ያልተሳካላቸው ሃጢያተኛ ነብይ ነበሩ፡፡
ማንዴላ ተራ ሰው የነበሩ መሆናቸውን እናገራለሁ፣ ተራ ሰው አስገራሚ ከፍታ ላይ የወጡ፡፡ ማንዴላ የህግ ሰው የነበሩ መሆናቸውን እናገራለሁ፣ የሰብአዊ መብት የህግ ሊቅ፡፡ ማንዴላ ያልተከለሱ እና እውነተኛ አብዮታዊ የነበሩ መሆናቸውን እናገራለሁ፣ ደቡብ አፍሪካውያንን እና አፍሪካውያንን በሙሉ ነጻ ማውጣታቸው ብቻ ሳይሆን በጭቆና ቀንበር ስር ወድቆ የሚማቅቀውን የሰው ልጅ ዘር ሁሉ ነጻነት በማውጣታቸው ጭምር እንጅ፡፡ ማንዴላ ታላቁ የሰብአዊ መብት ተሟጋች የነበሩ ለመሆናቸው እናገራለሁ፣ ለኤች አይቪ በሽታ ሰለባ ለሀኑት፣ ለህጻናት ሰብአዊ መብት ጥበቃ፣ ጥራት ላለው ትምህርት መስፋፋት እና ለገጠር ልማት ስኬታማነት ግንባራቸውን ሳያጥፉ ይታገሉ ነበርና፡፡
የህግ ባለሙያ ለመሆን መረጥኩ ምክንያቱም ማንዴላ ለእኔ ተምሳሌት/ሞዴል አንዱ ነበሩና፡፡ እ.ኤ.አ በኤፕሪል 1964 የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪ በነበርኩበት ጊዜ ለመጀመሪያ ጊዜ ማንዴላ በሪቮኒያ የህግ ሂደት ያሰሙትን ንግግር ከሰማሁ ጀምሬ ንግግራቸው አእ ምሮዬ ዉስጥ ተቀርፅዋል፡፡ እንደ ማርቲን ሉተር ኪንግ “ደብዳቤ ከቢርሚንግሀም እስር ቤት“ ሁሉ የማንዴላ ንግግር በአዕምሮየ ተሰንቅሮ እያቃጨለ እንዲህ በማለት ያሳስበኝ ነበር፣ “በህይወት ዘመኔ ሁሉ ለዚህ ለአፍሪካ ህዝብ ትግል ነጻነት እራሴን መስዕዋት አደርጋለሁ፡፡ የነጮችን የበላይነት ለማስወገድ እታገላለሁ፣ እንዲሁም የጥቁሮችን የበላይነት ለማስወገድ እታገላለሁ፣ ሁሉም ህዝቦች በፍቅር እና በእኩልነት፣ ዴሞክሪያሴያዊ እና ነጻ ህዝቦች ሆነው በጋራ የሚኖሩባትን ዓለም እመኛለሁ፣ ለመኖር ቃልኪዳኔ እና እውን ሆኖ ማየት የምፈልገው ፍልስፍና ይኸ ነው፣ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝም ይህ ፍልስፍና እውን እንዲሆን ህይወቴን ለመስጠት ያለማመንታት የተዘጋጀሁበት ጉዳይ ትልቅ ጉዳይ ነው“፡፡ ኔልሰን ማንዴላ ይህንን ሲሉ በትክክል ምን ማለታቸው እንደሆነ ለመረዳት አስርት ዓመታትን ወስዶብኛል፡፡
ማንዴላ በሪቭኦኒያ የሕግ ሂደት ጥፋተኛ ተብለው የእድሜ ልክ እስራት ተበይኖባቸዋል፡፡ ማንዴላ በቁጥር 46664 የአፓርታይድ እስረኛ ተደርገዋል፡፡ የ27 ዓመታት ቁጥር 46664 እስረኛው ማንዴላ የዕለት ከዕለት ውርደት፣ ኢሰብአዊነት፣ ከባድ እና ጭካኔ የተሞላበት የጉልበት ስራ እንዲሰሩ በማስገደድ ግፍ ተፈጽሞባቸዋል፣ ከቤተሰቦቻቸው እና ከጓደኞቻቸው እንዲለያዩ ተደርጓል፡፡ የልጃቸውን የቀብር ስነስርዓት እንኳ ለመገኘት  አልተፈቀደላቸውም፣ የባለ 46664 ቁጥሩ እስረኛ በአፓርታይድ ጌቶች በሁሉም እይታ እና ተግባር እንዲሞቱ የተወሰነ ነበር፡፡ እስረኛ ቁጥር 46664 ግን አልሞቱም፣ በዚያች እግዚአብሄር በረገማት ደሴት እንዳይታዩ ሆነው ተወረወሩ፡፡ የኔልሰን ማንዴላ የ27 ዓመታት የግዞት እስራት ማንዴላን የሮብን ደሴት ተመላኪ እንዲሆኑ አስችሏቸዋል፡፡ በጊዜ ሂደት በግለሰብ ደረጃ የማይታወቁት ቁጥር 46664 እስረኛ ተስፋ ለሌላቸው ህዝቦች የተስፋ፣ መጠጊያ እና ኃይል ለሌላቸው ለደቡብ አፍሪካ እና ለሌሎች ዓለም ህዝቦች ደግሞ የነጻነት ቀንዲል ለመሆን በቅተዋል፡፡
ቁጥር 46664 እስረኛ በአብዛኛው የ27 ዓመታት የእስር ሂደት በሚያቃጥለው ፀሐያማ ሀሩር የኖራ ድንጋይ ቁፋሮ እንዲቆፍሩ ይገደዱ ነበር፣ ማታ በእስር ቤታቸው ተቀምጠው ሰለወደፊቱ ዕቅዳቸው እና የአሰራር ስልታቸው ንድፍ ያወጡ ነበር፡፡ ሆኖም ግን በእራሳቸው፣ በቤተሰቦቻቸው እና በሌሎች ወገኖቻቸው ዘንድ ለመግለጽ በሚዘገንን መልኩ ስቃይ እና መከራ ሲያደርሱባቸው በነበሩት ጠላቶቻቸው ላይ በቀል እና ቅጣት ለመውሰድ አያስቡም ነበር፡፡ ቁጥር 46664 እስረኛ የአፓርታይድ ጨቋኞቻቸው መጥፎ አካሄዳቸውን እና ሰይጣናዊ ድርጊታቸውን እንዲተው ስትራቴጂ ይነድፉ ነበር፡፡ ቁጥር 46664 ህዝቦቻቸውን ከባስቱንታንስ የአፓርታይድ ደሴት ነጻ ለማውጣት ሌሊት ተጋድመው የወረቀት ላይ ንድፋቸውን በመስራት አርቺቴክት መሆን ጀመሩ፡፡ በደቡብ አፍሪካውያን የፖለቲካ ሰውነት ላይ ተንሰራፍቶ የቆየውን የዘረኝነት ቁስል ለማዳን እና ለመጠገን እዕምሯቸውን ክፍት በማድረግ ጥረት ማድረግ ጀመሩ፡፡ ቁጥር 46664 እስረኛ ከህዝቦች ነቢያትን እና ሃጢያተኞችን ለማውጣት ሌሊቱን በብቸኝነት በያዟት በጠባቧ እስር ቤታቸው ማስፈጸሚያ ዘዴዎችን ማውጠንጠን ጀመሩ፡፡
እ.ኤ.አ ጃንዋሪ 1 1990 እስረኛ ቁጥር 46664 ከሮበን ደሴት እስር ቤት ኔልሰን ማንዴላ ሲወጡ አየን፡፡ በክብር እና ተስፋን በሰነቀ አቀራረብ በጣም ፈገግ የሚሉ ሰው ተመለከትን፡፡ ለሶስት አስርት ተከታታይ ዓመታት ያህል በእስር ቤት ውስጥ የቆየ ሰው ከእራሱ ጋር በሰላም ለመኖር እና እንዲህ በክብር ለመቆየት እንዴት ይችላል? ወዲያውኑም ግልጽ ሆነ፣ የእስረኛ ቁጥር 46664ን እዚያው እስር ቤቱ ውስጥ በመራራው እና በተሰባበረው የእስር ቤት ጓደኝነት የሲኦል በር በሮበን ደሴት ላይ ተውት፡፡ እንዲህም ብለዋል፣ “የእስር ቤቷን በር አልፌ ወደ እስር ቤቱ አጥር ግቢ በር ስራመድ ወደ ነጻነት እየሄድኩ መሆኑን ተረዳሁ፡፡ ጥላቻየን እና ሰቆቃውን እዚያው እስር ቤት ትቸው ካልወጣሁ አሁንም እዚያው እስር ቤት እንዳለሁ አውቃለሁ“፡፡ ማንዴላ እስረኛ አልነበሩም!  እስር ቤቱ አፓርታይድ እራሱ ብቻ ነበር፣ እስረኞቹም የእስር ቤቱ ኃላፊዎች እና የአፓርታይድ ጌቶች ነበሩ፡፡ ኔልሰን ማንዴላ በአፓርታይድ የግንብ አጥር ተከልለው በእውን የሚገኙትን ጥላቻ፣ ፍርሀት እና በቀል በማስወገድ ነጻነትን ለማምጣት ሮቤን ደሴትን ለቀው ወጡ፡፡ ማንዴላ ዊኒ ማንዴላን ከጎናቸው በማድረግ በፊታቸው ታላቅ ፈገግታ እና ፍቅርን እንዲሁም ዕርቅ እና ልባዊ እውነትን  በማሳየት ከሮቤን ደሴት እስር ቤት ወጡ፡፡ “ኃጢያተኛውን ነብይን ተመለከትን! ሲራመዱ ሲናገሩ!  በዚያን ዕለት በአይኖቸ አልቅሻለሁ፡፡ ሌላ ያላለቀሰ ማን ነው?
ማንዴላ ሀሳባዊ አልነበሩም፣ ነገሮችን ሁሉ በአንክሮ የሚመለከቱ ጭምር እንጅ፡፡ የዕርቅን እና የዕውነትን መንገድ መረጡ፣ ምክንያቱም እነዚህ ወደ ፍትህ እና ሰላም ይመራሉና፡፡ ጥላቻ እና በቀል ወደ ሲኦል እንደሚወስዱ ማንዴላ ያውቃሉና፡፡ “ሰው የመሆናችን ተፈጥሯዊ ባህሪ አንዳችን ካአንዳችን እንድንተሳሰር ያደርገናል፣ በማዘን እና በጓደኝነት አይደለም፣ ነገር ግን ሰው እንደመሆናችን መጠን አሁን የሚያሰቃዩንን ነገሮች ለወደፊት ተስፋ ባለው ነገር መለወጥ የሚያስችል ችሎታም ስላለን ነው“፡፡ ማርቲን ሉተር ኪንግ ሲያደርጉት እንደነበረው ሁሉ ኔልሰን ማንዴላም በተመሳሳይ መልኩ ስልፍቅር… በተለይም ስለሰው ልጅ ያልተገደበ ፍቅር “አፋቸውን ከፈት” አድርገው በማስተማር ጥረት ያደርጉ ነበር፡፡ ከአፓርታይድ ጨቋኞች ጋር ዕርቅ ማድረግ የማይቻል ነው ሚሉትን ወገኖች ማንዴላ እንዲህ በማለት አስተምረዋል፣ “ተፈጽሞ አስከሚታይ ድረስ አንድ ነገር የሚሆን አይመስለንም“፣ እንዲህ ሲሉም መክረዋቸዋል፣ “በዚህች ዓለም ላይ ቅጣትን ከመፈጸም ይልቅ ምህረትን በማድረግ ብዙ ነገሮችን ማሳካት ትችላለህ“፡፡ ማንዴላ ትክክል ናቸው፡፡
ማንዴላ “በጎነት እና ይቅርታ አድራጊነት” በሚባሉ ሁለት አውራ ጎዳናዎች ረዥሙን የነጻነት ጉዞ ተጉዘዋል፡፡ ረዥም ጉዞ ነበር ምክንያቱም፣ ብዙ ተለዋጭ መንገዶችን መጓዝ ስለነበረባቸው፡፡ ሰፊውን የጓደኝነት ጎዳና እና ትልቁን የመቻቻል መንገድ መጓዝ ነበረባቸው፡፡ ትንሿን የፍርሀት እና ያለመግባባት መንገድ መጓዝ ነበረባቸው፡፡ በረዥሙ የጉዞ መንገድ ድፍረት፣ ታጋሽነት፣ ፍቅር፣ ጽናት እና ሩህሩህነት በማሳየት ብዙ ቆይታ ማድረግ ነበረባቸው፡፡
ማንዴላ በእስር ቤታቸው ክልል ተወስነው በጊዜ ብዛት ለመለካት በማይቻል መልኩ ታማኝነትን አዳብረዋል፡፡ “ሰዎች በውጭ በሚያከናውኑት መጠን እራሳቸውን ይለካሉ፣ ነገር ግን እስር ቤት ሰውን በውስጥ ጉዳዩች ማለትም ታማኝነት፣ ቅንነት፣ ግልጽነት፣ ሰብአዊነት፣ ለጋሽነት እና የማይለዋወጥ ባህሪ ላይ እንዲያተኩር ያደርገዋል“፡፡ ማንዴላ ወደ እስር ቤት ሲገቡም ሆነ ሲወጡ ቋሚ ጓደኞች ነበሯቸው፡፡ ሮናልድ ሬጋን እና ማጂ ታቸር የአፓርታይድን መንግስት መርዳት ብቻ ሳይሆን ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ማዕቀብም እንዲጣልበት አድርገዋል፡፡ በማንዴላ እና በኤኤንሲ ላይ “የአክራሪነት ባህሪ ዝርዝር ውስጥ“ በማስገባት እ.ኤ.አ እስከ 2008 ድረስ በዘለቀው ሁኔታ ማዕቀብ መጣል አልቸገራቸውም ነበር፡፡ እነዚህ የጊዜው ጥሩ ጓደኞች እና ተመሳሳዮቻቸው ማንዴላ ከፊደል ካስትሮ እና ከሙአማር ጋዳፊ ጋር ጓደኝነት መመስረታቸውን ለመተቸት ጊዜ አልወሰደባቸውም፡፡ ማንዴላ በፍጹም መንገዳቸውን የማይቀያይሩ እና ከአመኑበት ነገር ላይ በቀላሉ የሚያፈገፍጉ አልነበሩም፡፡ ማንዴላ እንዲህም ይሉ ነበር፣ “ጓደኛ ማለት የደስታ ጊዜ ብቻ ሳይሆን በጭንቅ ጊዜም የሚገኝ ነው“፡፡ ወዲያው እንዳዩ ይጣሩ ነበር፡፡ በጊዜ ሂደት አሜሪካ “በዓለም ላይ በቃላት ሊገለጽ በማይችል መልኩ ትፈጽም በነበረው የሰብአዊ መብት ድፍጠጣ“ ላይ ጠንከር ያለ ትችት ያቀርቡ ነበር፡፡ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ደብሊው ቡሽ ወደ ኢራቅ ጦር ባዘመቱ ጊዜ ማንዴላ በዝምታ አልተመለከቱም ነበር፣ እንዲህ አሉ እንጅ፣”ኢራቅን ለነዳጅ ዘይቷ ሲል“ የወረረ እንዲሁም “በትክክል ማሰብ የተሳነው እና አርቆ ማየት የማይችል ፕሬዚዳንት“ በማለት በትችት ወርፈዋቸዋል፡፡
ማንዴላ የአስታራቂነት ጌታ እና የሰይጣን ነብይነት ከመሆናቸው በፊት አማጺ ነበሩ፣ ነገር ግን አማጺነታቸው በጸረ ዘር መድልኦነት ላይ ነበር፡፡ “አሸባሪ“ ነበሩ ነገር ግን የአፓርታይድን ስርዓት በመቃወም ላይ ብቻ፡፡ ለደቡብ አፍሪካውያን በሙሉ የነጻነት ታጋይ ነበሩ፡፡ ለህግ የበላይነት መከበር ቀናኢ ነበሩ፡፡ አሜሪካ ከህግ አግባብ ውጭ በኦሳማ ቢን ላደን ላይ የፈጸመችውን ግድያ ተችተዋል፡፡ ማንዴላ “የኮሙኒስት” ሽምቅ ተዋጊ እና የቀዝቃዛው ጦርነት አብዮታዊ ስለነበሩ አገራቸው የልዕለ ኃያላኑ የጦርነት መፎካከሪያ ሆና ነበር፡፡ ማንዴላ ለሰራተኛው መደብ መብት ተከራካሪ እና በዓላማቸው የጸኑ ታጋይ ነበሩ፡፡ ለዚህም እ.ኤ.አ በ1990 በዴትሮይት የሚገኙትን የአውቶ ሰራተኞች እንዲህ በማለት ነግረዋቸዋል፣ “እህቶች እና ወንድሞች፣ ጓደኞች እና የትግል አጋሮች፣ አሁን ከእናንተ ጋር ንግግር የሚያደርገው ሰው እንግዳ አይደለም፡፡ አሁን ነግግር እያደረገ ያለው ሰው የዩኤደብልዩ/UAW አባል ነው፡፡ እኔ ስጋችሁ እና ደማችሁ ነኝ፡፡“ በሮቤን ደሴት የኖራ ድንጋይ ቁፋሮ ተገደው ሲሰሩባቸው የነበሩትን ዓመታትን  አልረሱም፡፡ ማንዴላ ቡጢያቸውን የሚጠቀሙ ቦክሰኛ ብቻ አልነበሩም፣ ግን በብሩህ አዕምሯቸው በመመራት ጥብብ በተመላበት ዘዴ በመዋጋት ትጥቅ የሚያስፈቱ ጀግና ነበሩ፡፡  ማንዴላ በጣም ተጫዋች ሰው ነበሩ: በራሳቸዉም ላይ ይሰቁ ነበር፡፡ የመጀመሪያ የስልጣን ዘመናቸውን በቢሯቸው ካጠናቀቁ በኋላ የነጮች የንግድ ማህበረሰብ ስብሰባ ላይ በመገኘት እንዲህ ሲሉ ነግረዋቸዋል፣ “እኔ በአሁኑ ጊዜ ደኃ ጡረተኛ ነኝ፡፡ ስራ አጥ ነኝ፡፡ ልትቀጥሩኝ ትችላላችሁን?“
ማንዴላ እስከፈለጉበት ጊዜ በስልጣን መንበራቸው ላይ መቆየት ይችሉ ነበር፡፡ እንደሌላው የአፍሪካ አምባገነን ገዥ ሁሉ በስልጣን ላይ ተጣብቀው መቆየት ይችሉ ነበር፡፡ ከአራት ዓመታት በኋላ ስልጣናቸውን ማስረከብ ነው የመረጡት፡፡ በፍላጎታቸው ስልጣን በሚለቁበት ጊዜ ለደቡብ አፍሪካውያን እና ለአፍሪካውያን በሙሉ ሊተመን የማይችል ቅርስ ነው የሰጡት፣ የፖለቲካ ስልጣን የውልደት መብት እርስት አለመሆኑን ነገር ግን በህዝቦች ፍላጎት የሚሰጥ እና ሲያስፈልግም የሚቀማ ኃላፊነት መሆኑን በተግባር አሳይተዋል፡፡ በዚያ ድርጊት መሰረት ማንዴላ የህግ የበላይነትን በህገመንግስቱ እንዲካተት እና የደቡብ አፍሪካ ሉዓላዊነት እንዲጠበቅ በማድረግ ለሁሉም አፍሪካውያን አርአያ ለመሆን በቅተዋል፡፡
ማንዴላ ስልጣንን የህዝቦች ፈቃደኝነት፣ ፍላጎት ማስፈጸሚያ፣ የዓላማዎች ማሳኪያ ስልት እንጅ በእራሱ የመጨረሻ ግብ እንዳልሆነ አድርገው ነበር የሚመለከቱት፡፡ ጥሩ ነገር ለመስራት ስልጣንን መጠቀም አስፈላጊ እንደሆነ ያምናሉ፣ ኃይል የሌላቸውን ኃይል ካላቸው ለመጠበቅ፣ ስልጣንን አላግባብ መጠቀምን ለመከላከል፣ ስልጣንን በመጠቀም ኃይል የሌላቸውን ኃይለኞች ለማድረግ፣ ኃይልን በመጠቀም ወጣቶችን ኃይል እንዲኖራቸው ለማድረግ የኃይል መጠቀምን አስፈላጊነት ይናገሩ ነበር፡፡ ህዝብ ተስፋ እንዲኖረው የኃይል መጠቀምን አስፈላጊነት ያምኑ ነበር፡፡ ኃይልን መጠቀም ለመግደል ወይም ለመስረቅ ሳይሆን ህዘቦችን ለማዳን መሆን እንዳለበት ያምኑ ነበር፡፡ በሰላም ኃያልነት ያምኑ ነበር፡፡ ከባንቱስታንስ የዘረኝነት ደሴት በማላቀቅ ብሩህ የህዝቦችን ህይወት መመስረት እንዲቻል በደግ ስራ እና በዕርቅ ኃያልነት ያምኑ ነበር፡፡
ማንዴላ የዕርቅ ዋጋው እውነት ነው፡ ብለዋል፡፡  አንድ ሰው ለሰራው ስራ ወይም ላጠፋው ጥፋት በህዘብ ፊት ኃላፊነትን መውሰድ ዕርቅ የሚፈልገው ጉዳይ ነው፡፡ የአፓርታይድ ሰብአዊ መብት ደፍጣጮች አስከ አሁን ድረስ ለፈጸሙት ወንጀል ኃላፊነት በመውስድ ለፈጸሙት ለጥፋታቸው በህዝብ ፊት አምነው ይቅርታ መጠየቅ ይኖረባቸዋል፡፡ የጥፋት ሰለባዎቻቸው እና ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖች የእነዚህን እኩይ ተግባር ፈጻሚዎች እውነተኛ ባህሪ ማወቅ ይኖርባቸዋል፡፡ እውነት እና እውነት ብቻ እርምጃ ከመውሰድ እና የጥላቻ በቀል ከመውሰድ ያድናል፡፡ ማንዴላ አገራቸውን ከአፓርታይድ የሞራል ዝቅጠት ለማጽዳት እና ህዝቡን ከአፓርታይድ የጨለማ መንገድ ለማውጣት እንዲሁም የብዙሀን ፓርቲ ስርዓት እንዲጎለብት በማሰብ የእውነት እና የዕርቅ ኮሚሽን አቋቁመዋል፡፡
ለሶስት አስርት ሩብ ዓመታት ለነጻነት ረዥሙን ጉዞ የተጓዙት ሰው አሁን ማረፍ አለባቸው፡፡ ረዥሙን ጉዞ ተጉዘዋል፣ ምክንያቱም ነጻነትን የመጠበቅ ቃልኪዳን ነበራቸውና፡፡ አሁን አሸልበዋል፡፡ ለዘላለም በሰላም ይረፉ፡፡
ሆኖም ግን ወደ ነጻነት የሚደረገውን ረዥሙን ጉዞ ለማጠናቀቅ ገና ብዙ ማይሎች እና ብዙ ያልተሳኩ ቃልኪዳኖች ይቀራሉ፡፡ የማንዴላን ረዥሙን ጉዞ አሁን የሚጓዘው ማን ነው? የማንዴላን ቃልኪዳኖች የሚፈጽማቸው ማን ነው? ማንዴላ የአፍሪካ ወጣቶች ቀንዲል…
የማንዴላ ስንብት ለአፍሪካ ወጣቶች፡ “ትግላች

Nile basin countries fail to agree on dam construction

December 11, 2013 (KHARTOUM) – Water ministers of Sudan, Ethiopia and Egypt failed to reach an agreement on the disputed Ethiopian Renaissance Dam project and decided to refer the sticking points to a third meeting.
JPEG - 19.2 kb
Planned Grand Ethiopian Renaissance Dam project (file/AP)
The second ministerial meeting which was held in Khartoum on Monday sought to reach an agreement on forming a joint mechanism for implementing the recommendations of the International Panel of Experts (IPoE) regarding the dam.
The IPoE is composed of six representatives each drawn from Ethiopia, Egypt and Sudan, and another four international experts and was established to assess the impact of the dam project on downstream countries.
The report which was submitted by IPoE to the three countries last June is believed to show that the $4.7 billion dam will not have any major effect on lower riparian countries of Egypt and Sudan. However Egypt assert that the deficiencies mentioned by the report need to be addressed before carrying on with the dam project.
The Sudanese water minister, Muattaz Musa Abdallah Salim, told reporters following the meeting that they have addressed a significant part of the issues on the follow-up of the implementation of the IPoE recommendations.
He added that they concluded the second meeting successfully, pointing that remaining issues would be addressed in Khartoum during talks which will be held from January 4 to 5.
The Egyptian water minister, Mohamed Abdel-Mutalab, for his part told reporters that they reached an agreement on some items but others are still pending.
Sources close to the meeting said that Egypt and Ethiopia presented two papers on the points of contention, while Sudan’s paper attempted to reconcile the two positions.
The same sources said that Egypt wanted international representatives on the committee but Ethiopia preferred national delegates.
The Sudanese daily newspaper Al-Ray Alaam quoted sources on Tuesday as saying the Egyptian delegation suggested that Ethiopia should only complete the first phase of the dam to store 14.5 billion cubic meters to produce 1200 MW of hydroelectric power to meet its energy needs.
The member of the Egyptian delegation, Alaa Al-Zawahri, earlier said that Egypt would suggest during the meeting that Ethiopia build a smaller dam and suspends the ongoing construction for six months until the completion of the studies.
He described in an interview with the Egyptian CBC TV the Sudanese stance with regard to the dam as “puzzling”, pointing that Sudan turned from a strategic partner of Egypt into a biased mediator.
Egypt demanded Ethiopia to agree with it and Sudan on the dam’s operating and storage rules through a technical mechanism formed by the three countries besides implementing the necessary projects to avoid the negative effects of the dam.
When the dam project, which will have power generation capacity of 6,000 MW, goes operational, it will generate up to 2 million Euros per day from exporting hydro-electricity.
Egypt believes its “historic rights” to the Nile are guaranteed by two treaties from 1929 and 1959 which allow it 87 percent of the Nile’s flow and give it veto power over upstream projects.
But a new deal signed in 2010 by other Nile Basin countries, including Ethiopia, allows them to work on river projects without Cairo’s prior agreement.
Both Sudan and Egypt have not signed the new Nile Basin deal.
Sudan also relies on Nile resources but has said it does not expect to be affected by the dam.
On Wednesday Sudan and Ethiopia inaugurated a cross-border electricity linkage. Media in Khartoum said Sudan will initially buy 100 MW from Ethiopia through the 321-kilometre (199-mile) line.
(ST)

56 Ethiopian immigrants arrested in Kilimanjaro, Tanzanian

BY JAMES LANKA

11th December 2013
Robert Boaz, Kilimanjaro Regional Police Commander (RPC), Assistant Commissioner of Police (ACP)
Police have arrested 56-illegal immigrants while in transit in Same District, Kilimanjaro Region.
They are suspected to be from Ethiopia and were nabbed hidden in a ‘Fuso’ lorry in Jiungeni village, Ruvu ward following a tip-off to police.
The Kilimanjaro Regional Police Commander (RPC), Assistant Commissioner of Police (ACP) Robert Boaz, said the good samaritans reported the incident around 12:00 midnight saying they had seen suspicious behaviour surrounding a cargo lorry.
The vehicle, registration number T. 118 AYU, was identified as the property belonging to a Moshi-based transport company, Elimo Trans Company Limited.
“We are re grateful with this information as it led to successful intervention… police arrested 56-illegal,” said the RPC.
The lorry, driver Daniel Mfinanga, a Tanzanian who lives in the Himo Town and his two counterparts has been arrested in connection with the incident.
The illegal immigrants, according to the RPC Boaz, were on transit to South Africa and had no legal documents and entered the country through ‘panya routes’ at the Taveta area bordering Tanzania and Kenya.
“The 56-illegal immigrants from Ethiopia were on transit from Kenya they have left their countries due to life hardships and not because of political instability so they don’t need asylum,” the RPC explained.
Kilimanjaro Region is one of Tanzania’s border regions and so it has a high propensity of Illegal Immigrants presence mostly from Ethiopia and Somalia.
“Police in Kilimanjaro Region have established the ‘task force’ which includes regional and district Immigration officers and other security officers to curb the problem…” the Kilimanjaro Police Chief explained.
It is believed that the Tanzanian conduits charge between 100 US dollars (about 110,000/-) and 200 (about 220,000/-) to facilitate the transfer to the next destination within the country (one region to another). From there another agent takes over.
Police sources say that the alleged conduits have their counterparts in Kenya, Ethiopia, Somalia and Europe who have been running the “business” for many years now.
SOURCE: THE GUARDIAN

Wednesday 11 December 2013

በኢትዮጵያ ለሚታየው መብራት መጥፋት መስሪያቤቶች እርስ በርስ እየተካሰሱ ነው

በአዲስ አበባ አንዳንድ አካባቢዎች እና በሰሜን የአገሪቱ ክፍሎች በሚገኙ ከተሞች መብራት በተደጋጋሚ እየተቋረጠ ሲሆን፣ መብራት ሀይል የተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ተናበው ለመስራት አልቻሉም በሚል ወቀሳ አሰምቷል።  በጉዳዩ ዙሪያ ዘጋቢያችን ያነጋገራቸው የኢትዩጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ     40 በመቶ የሚሆነው ኤሌክትሪክ ሃይል መቆራረጥ የሚፈጠረው በሰው ሰራሺ አደጋ ነው ያሉ ሲሆን፣  ከአዲስ አበባ መንገድ እና ትራንስፖርት ባለሰልጣን ጋር ተናበን መስራት ባለመቻላችን በዚህ አራት ወራት ብቻ የኤሌክትሪክ ባቡር መስመር ዝርጋታ በሚል ሰበብ ከ120 ሚልዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ወድሞብናል ብለዋል፡፡
በቅርቡ በቦሌ ሩዋንዳ በኮንክሪት የተገነባው ባለ 33 ኪሎ ቮልት   ትራንስፎርመር እና መሰል እቃዎች የ በአዲስ አበባ የመንገድ ስራ ድርጅት የመንገድ ቁፋሮ ሃለፊነት በጎደለው ሁኔታ ከስሩ በመጣላቸው ከ450 ሺ ብር በላይ ንብረት መውደሙን  ገልጽዋል፡፡
የአዲስ አበባ መንገድ እና ትራንስፖርት ባለስልጣን በሚፈጥረው ችግር ደንበኞችን ማርካት አልቻልም  በዚህም የኤሌክትሪክ ሃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ሮሮ እያሰሙ ነው በማለት ሀላፊው ተናግረዋል።
በተያያዘ ዜናም ከባህር ዳር አምስት ኪሎ ሜትር ርቀት በምትገኝ ይነሴ የገጠር ቀበሌ በ66 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ተሸካሚ ሰባት የብረት ታዎሮች በመዘረፋቸው በዚህ የኤሌክትሪክ መሰመር ሃይል የሚያገኙ በዳንግላ እና ፓዊ ሳብስቴሺን የሚገኙ ደንበኞች ሃይል አጥተዋል ፡፡ ምእራብ ጎጃም በከፊል  መራዊ ፤ ቢኮሎ ፤ ዱርቤቴ ፤ይስማላ ፤ሊበን ፤ቁንዝላ ፤ዲንካራ ፤ በሰሜን ጎንደር  ሻውራ እና አካባቢው ፤ በአዊ ዞን ዳንግላ ፤ቲሊሊ ፤ እንጅባራ  አዲስ ቅዳም ፤ግምጃ ቤት ፤መተክል ፤ ሰከላ፤ በቢንሻንጉል ጉምዝ መተከል ዞን በሙሉ በጨለማ ውስጥ መሆናቸውን አቶ ምስክር ነጋሺ ተናግረዋል፡፡
ኮርፖሬሺኑ ችግሩን ለመፍታት እየሰራሁ ነው ቢልም እስካሁን ድረስ የታየ ለውጥ የለም

ሰመጉ በቤንሻንጉል ጉሙዝ የሰብአዊ መብት ጥሰት መፈጸሙን አስታወቀ

በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በተለያዩ ዞንና ወረዳዎች አማራ ናችሁ ተብለው በተባረሩ በሺዎች በሚቆጠሩ ዜጎች  ላይ የሰብአዊ መብት ጥሰት እና አካላዊ ጉዳት እንደተፈፀመ የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ ባካሄደው ጥናት አረጋግጧል ፡፡
በክልል በተለያዩ ዞንና ወረዳዎች ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ቁጥራቸው ከ10 ሺህ  በላይ የሚገመቱ ዜጐች ለረዥም አመታት ይኖሩበት ከነበረው አካባቢያቸው የዚህ ክልል “ተወላጆች አይደላችሁም” በማለት በሀይልና በግዳጅ ቤት ንብረታቸውን ጥለው ከመጋቢት 15/2005 ዓ.ም ጀምሮ እንዲሰደዱ መደረጋቸውን  ተቋሙ አውስቷል፡፡
በዚህም ምክንያት ህፃናትና ሴቶች እንዲሁም አቅመ ደካማዎች በቂ ምግብና ህክምና ባለማግኘታቸው በከፍተኛ ችግር ላይ ወድቀው እንደነበር ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዞን ቡለን ወረዳ ከአካባቢያቸው የተፈናቀሉ ሰዎች ተወካዮቻቸው አቤቱታና የምስክርነት ቃል ማረጋገጡን የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ ያካሄደው ጥናት አመልክቷል፡፡
ጉባኤው  በአካባቢው በመገኘት የጉዳዩን ስፋትና ተፈናቃዩች በዚህ ጊዜ የሚገኙበትን አጠቃላይ ሁኔታ ለማጣራት መቻሉንም ገልጿል።
ተፈናቃዮቹ አሁን የሚገኙበት ሁኔታ አስቸጋሪ ነው ያለው ሪፖርቱ፤ በአንዳድ አካባቢዎች ለምሳሌ በካማሼ ዞን ተፈናቃዮቹ ወደ ቦታቸው እንዲመለሱ የተደረገ ቢሆንም ከተመለሱ በኃላ ንብረታቸው በመወሰዱና በመጥፋቱ ለመቋቋምና ወደ ነበሩበት የኑሮ ሁኔታ ለመመለስ አልቻሉም ። ለእርሻ ግብዓት የሚሆኑ እንደ ዘር ፣ማዳበሪያ የመሳሰሉትን ለመግዛት አለመቻላቸውን፤ ብድርም ለመውሰድ ሲጠይቁ ብሔረሰባቸው እየተጠቀሰ አድልዎ እየተፈፀሙባቸው እንደሚገኝ የሰመጉ ባለሙያዎች በአካባቢዉ ተገኝተው ባጣሩበት ወቅት ከተጐጂዎቹ አንደበት ለመረዳት ችለዋል፡፡ በመተከል ዞን ቡለን ወረዳ በባሩዳ ቀበሌና በአካባቢው ካሉት ቀበሌዎች የተፈናቀሉት ሰዎች
ብዛት 5 ሺ እንደሆነ የተፈናቃዮዎቹ ተወካዩች የገለፁ ሲሆን እነዚህ ተፈናቃዮች በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ውስጥ በሚገኙት ጓንጓና ቻግኒ ከተሞች ውስጥ በብዛት ይገኛሉ፡፡ ይሁንና በሌሎች አካባቢዎችም በዘመድ ወዳጅ ቤት ውስጥ ተጠግተው እንደሚገኙ የተወሰኑ ተፈናቃዮችና ተወካዮቻቸው ቻግኒ ከተማ ውስጥ ለሰመጉ ባለሙያዎች ለማጣራት በሄዱበት ወቅት አረጋግጠውላቸዋል፡፡ በተለይም ይህንን የማጣራት ስራ በሚሰሩበት ወቅት በቻግኒ ከተማ ውስጥ ብቻ በተለያዩ ቦታዎች ተበታትነው የሚገኙ ተፈናቃዮች ብዛት 500 እንደሚደርስ በአካል ተገኝተው ለመረዳት ችለዋል፡፡
ተፈናቃዮቹ ለሰመጉ እንደሚያስረዱት የደረሰባቸውን ከፍተኛ በደልና እንግልት እንዲሁም የሚገኙበትን አስቸጋሪ ሁኔታ በተለያዩ የሀገር ውስጥ ጋዜጦችና የውጭ ሚዲያ በመናገራቸው ምክንያት እስራት ዛቻና ክትትል እየተፈፀመባቸው እንደሆነና በከፍተኛ ስጋት ላይ እንደሚገኙ በምሬትና የተስፋ መቁረጥ ስሜት በዶቢ፣ ያሶ፣ ባሩዳ ከተማ የተፈናቃይና ተወካዮቻቸው ለሰመጉ ያቀረቡት አቤቱታና የምስክርነት ቃል አስረድቷል፡፡
ለረዥም አመታት ያፈሯቸውን ንብረቶችና የእርሻ መሬታቸውን በአካባቢው ባለስልጣናትና በሌሎች ብሔረሰብ አባላት መነጠቃቸው፣ በባሩዳ ከተማ ህጋዊ በሆነ መንገድ ያፈሯቸው የሚንቀሳቀስና የማይንቀሳቀሱ ንብረቶቻቸውን እንዳያዙበት መደረጋቸው፣ መታወቂያ እንዳያወጡ መከልከላቸው፣ ልጆቻችው በትምህርት ቤቶች ውስጥ ገብተው እንዳይማሩ የተለያዩ አድልኦና ጫና እንዲደርስባቸው መደረጉ፣ በእርሻ ስራ የሚተዳደሩትን አርሶ አደሮችንም የምርጥ ዘርና ማዳበሪያ “የዚህ ክልል ተወላጅ አይደላችሁም” በሚል አድልኦ እንደሚደረግባቸውና እንደሚከለከሉ፣ በጥቅሉም ”እናንተ የዚህ ክልል ባለቤት አይደላችሁም ስለዚህ ለቃችሁ ውጡ” መባላቸውንና ይህንንም በተቃወሙት ላይ ዛቻ፣ ድብደባ፣ ንብረት ነጠቃና ለእሰራት ጭምር እንደተጋለጡ የተፈናቃይ ተወካዮች ለሰመጉ በፃፉት ከ140 በላይ ተፈናቃዮች ፊርማ ያረፈበት ማመልከቻና የተለያዩ ሰነዶች አመልክተዋል፡፡
የባሩዳ ቀበሌ ተፈናቃዮች “  በአካባቢው አስተዳደር አካላትና በሌሎች የክልሉ ብሄረሰብ አባላት የተነጠቁትን የተለያዩ ንብረቶች ተመላሽ አለመደረጉን ፣በአሁኑ ወቅት ከሌሎች ብሄረሰቦች እየተለዩ ማስፈራሪያና ድብደባ እየተፈፀመባቸው  መሆኑ፣ ምንም አይነት እገዛና ማቋቋሚያ አለመደረጉ፣ የእርሻ ግብዓትን እንደ ዘር ማዳበሪያ ያሉ ግብዓቶችን “እናንነተ የዚህ (ብሄር) አባላት ናችሁ” በማለት እየተከለከሉ ነገር ግን ለሌሎች እየተሰጠ እንደሚገኝና በፌዴራል መንግስት አማካኝነት ቢመለሱም የዞንና የቀበሌ አስተዳደር አካላት “እናንተ ከዚህ ክልል ውጪ ናችሁ” በማለት ልዩ ልዩ አድልዎና መገለል እየተፈፀመባቸው እንደሚገኝ ለሰመጉ አመልክተዋል፡፡
ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ የአማራ ተወላጆች ለረዥም አመታት ይኖሩበት ከነበረው ቦታ “ የዚህ አካባቢ ሰዎች አይደላችሁም” በማለት ከተፈናቀሉ በኋላ ወደ ነበሩበት ቦታ ይመለሱ እንጂ ምንም አይነት እገዛ ከመንግስት እንዳልተደረገላቸውና ይባስ ብሎም እንግልትና የተለያዩ አስተዳደራዊ በደሎች እየተፈፀመባቸው እንዳለ ዘጋቢያችን ሪፖርቱን ተከትሎ ባደረገው ማጣራት ለማረጋገጥ መቻሉን ገልጿል።

40 በ 60 እና 10 በ 90 የቤት እቅዶች መንግስትን ፈተና ውስጥ ጥለውታል

መንግስት በውጭ አገር ለሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ሀቅሙ ላላቸው ዜጎች የ40 በ60 እንዲሁም በአዲስ አበባ በአነስተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ ዜጎች ደግሞ የ10 በዘጠና እና የ20 በ80 የቤት ልማት እዶችን ዘርግቷል።
በ10/90 850 ሺ በ 20/80 ደግሞ 350 ሺ የአዲስ አበባ ነዋሪ ተመዝግቦ እድሉን በመጠባበቅ ላይ ሲሆን ከ12 ሺ በላይ በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ደግሞ 40 በ60 በሚባለው ውስጥ ታቅፈዋል።
በመርሀግብሩ ዝግጅት የተሳተፉ የውስጥ ምንጮች እንደገለጹት መንግስት ይህን እቅድ ለማሳካት ከፍተኛ የሆነ ፈተና ገጥሞታል ።
የውስጥ ምንጮች እንደሚሉት እቅዱን ለመተግበር 4 ዋና ዋና ችግሮች አጋጥሟል። የመጀመሪያው ችግር በሁሉም ደረጃዎች የተመዘገቡ ሰዎችን ፍላጎት ለማርካት ወደ 2 ሚሊዮን የሚደርሱ ቤቶች መገንባት ይኖርባቸዋል። ይህን ያክል ቤት ለመገንባት ደግሞ ቢያንስ 30 ሺ ሄክታር መሬት ስፋት ያለው ቦታ ያስፈልጋል። አዲስ አበባ ደግሞ ይህን ያክል ሰፊ መሬት ለማግኘት አትችልም።
የፌደራል መንግስቱ ለአዲስ አበባ ታላቅ የማስተር ፕላን በማዘጋጀት እና በማስተር ፕላኑ ውስጥ የኦሮሚያ ልዩ ዞኖች የሚባሉትን ሱሉልታ፣ ሰንዳፋና ገላንን በማካተት በቂ የቤት መስሪያ ቦታዎችን ለማፈላለግ እቅድ ነድፎ ቢንቀሳቀስም፣ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ” ከእንግዲህ መሬት ለአዲስ አበባ  መስተዳድር  መሬት የምንሰጠው በመቃብራችን ላይ ነው” የሚል አቋም በመውሰዱ እቅዱ ሳይሳካ ቀርቷል።
በኦሮሚያ ክልል አቋም አጣብቂኝ ውስጥ የገባው የፌደራሉ መንግስት ከተለያዩ መስሪያ ቤቶች የተውጣጡ ባለስልጣናትን በመሰብሰብ እና አንድ ኮሚቴ በማዋቀር ወደ ክልሎች ልኳቸዋል። እነዚህ ባለስልጣኖች ወደ ተለያዩ ክልሎች በመውረድ ክልሎች ለዲያስፖራ ኢትዮጵያውያን ቤት መስሪያ ቦታ እንዲያዘጋጁ ለማግባባት ይሞክራሉ። ክልሎች ፈቃደኛ ሆነው ሲገኙ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የዲያስፖራ አባላት ከአዲስ አበባ ወጣ ብለው በክልሎች ግንባታ እንዲያካሂዱ ለማግባባት እንቅስቃሴ ይጀምራሉ።
መንግስት ከዳያስፖራው የሰበሰበውን ገንዘብ ለመመለስ ፈቃደኛ ባለመሆኑ የቀረው ምርጫ የዲያስፖራ ቤተ ሰሪዎችን በክልሎች ሄደው እንዲሰሩ ማግባባት መሆኑን ምንጮች ይናገራሉ። በዘር ላይ የተመሰረተው የፌደራል ስርአት የአንዱ ክልል ወደ ሌላው ክልል ሄዶ ቤት ለመስራት እንቅፋት የሚፈጥር በመሆኑ መንግስትን ለተጨማሪ ራስ ምታት ዳርጎታል።
መንግስትን የገጠመው ሌላው ፈተና የገንዘብ እጥረት ነው። ንግድ ባንክ ለቤቶች ግንባታ የሚሆን 12 ቢሊዮን ብር ብድር መስጠት የሚኖርበት ሲሆን፣ በቅርቡ የንግድ ባንኩ ፕሬዚዳንት ከጠ/ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ ጋር በተገናኙበት ወቅት ባንካቸው ማበደር የሚችለው 6 ቢሊዮን ብር ብቻ መሆኑን ገልጸውላቸዋል። አቶ ሀይለማርያምም ባንኩ ቢያንስ 10 ቢሊዮን ብር ማበደር እንዳለበት ትእዛዝ ሰጥተዋል። ባንኩም ለታዋቂዎቹ የመጠጥ አምራች ድርጅቶች ማለትም ለሀይነከንና ዲያጎ የቢራ አምራች ፋብሪካዎች ፈቅዶት የነበረውን የ3 ቢሊዮን ብር የብድር ውል በመሰረዝ፣ ድርጅቶቹ 560 ሚሊዮን ብር ብቻ እንዲበደሩ በማድረግ ቀሪውን ገንዘብ ለዚሁ ፕሮጀክት ለማዋል  ተስማምቷል። ባንኩ እስካሁን 8 ቢሊዮን ብር ለማሰባሰብ የቻለ ሲሆን፣ የመንግስትን ጥያቄ ለማሙዋላት ተጨማሪ 2 ቢሊዮን ብር ከየት እንደሚያመጣ ግልጽ አልሆነም።
በሌላ በኩል ደግሞ የቤቶች መስሪያ ዋጋ መጀመሪያ ከታቀደበት መጠን እንዲከለስ ተደርጓል። በመጀመሪያ ለ3 መኝታ ቤት መስሪያ የተመደበው ገንዘብ 385 ሺ የነበረ ሲሆን በተከለሰው አዲስ ዋጋ ግን ይህ ዋጋ  በእጥፍ አድጎ 779 ሺ ብር እንዲሆን ተደርጓል። ይህ ዋጋ በቅርቡ እየታየ ያለውን የዋጋ ንረት ግምት ውስጥ በማስገባት ወደ አንድ ሚሊዮን እንደሚጠጋ ምንጮች ገልጸዋል። ዲያስፖራው ይህን ገንዘብ ግማሹን በአንድ ጊዜ ቀሪውን ደግሞ በአንድ ወር ውስጥ እንዲከፍል ይጠበቅበታል። አስገራሚው ነገር ይላሉ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች፣ መንግስት ከሚሰራው ቤት የተሻለ ጥራት ያለው ቤት በ450 ሺ ብር ማግኘት መቻሉ ነው።
ንግድ ባንክ በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ሲመዘግብ ቆይቶ በመጨረሻም ምዘገባው እንዲቋረጥ ማድረጉ ይታወቃል። የኢትዮጵያ ዜግነት ያላቸው የዲያስፖራ አባላት እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ በብር መክፈል ሲገባቸው በዶላር እንዲከፍሉ መገደዳቸው የአገሪቱን ህግ ከመጻረሩም በላይ ፣ መንግስት ራሱ ለሚያትመው ብር ዋጋ እንዳልሰጠ የሚያመለክትና ለብር ውድቀት ሌላ ምክንያት የሚሆን ነው በሚል ምዝገባው ተቋርጧል።
መንግስት ከዳያስፖራው ገንዘብ በዶላር ለመቀበል የፈለገበት አንዱ ምክንያት ከአባይ ግድብ ጋር የተያያዘ መሆኑን ምንጮች ይገልጻሉ። አቶ መለስ በህይወት በነበሩበት ጊዜ ዲያስፖራው ለግድቡ ማሰሪያ 1 ቢሊዮን ዶላር ያዋጣል የሚል እቅድ ዘርግተው ነበር። ይሁን እንጅ እስከዛሬ የተሰበሰበው 19 ሚሊዮን ዶላር ብቻ መሆኑ ያስደነገጣቸው የመንግስት ባለስልጣናት በቤት ግንባታ ስም ለግድቡ ማሰሪያ ተጨማሪ ገንዘብ ለማሰባሰብ ተጨማሪ እቅድ ቢያቅዱም ይህም እቅድ አደጋ ገጥሞታል።
ፕሮጀክቶችን ለማስፈጸም ሌላው ችግር የሆነው ተናቦ ለመስራት አለመቻል መሆኑን የውስጥ አዋቂዎች ይገልጻሉ። ለቤቶች ግንባታ ሃላፊነት በተሰጣቸው ሚኒስትር መኩሪያ ሀይሌ፣ በአዲስ አበባው ከንቲና ድሪባ ኩማ፣ በንግድ ባንክ ፕሬዚዳንትና በውጭ ግንኙነት ሚ/ሩ ቴዎድሮስ አዳህኖም መካከል መናበብ በመጥፋቱ ፕሮጀክቱ ባለበት የቆመ ሲሆን፣በተለይም እያንዳንዱ ባለስልጣን ኢህአዴግን ከመውደቅ ያዳንኩት እኔ ነኝ ለማለት ሁሉም የራሱን እቅድ አውጥቶ ሳይናበብ እየሰራ መሆኑን ምንጮች ተናግረዋል።
በጉዳዩ ዙሪያ አዲስ አበባን ከንቲባ አቶ ድሪባ ኩማን ለማነጋገር ስልክ ብንደውልላቸውም ሌላ ጊዜ ደውሉ ካሉን በሁዋላ በተለያዩ ጊዜያት ብንደውልም ልናገኛቸው አልቻልም። የኦሮሚያ ፕሬዚዳንት አቶ አለማየሁ አቶምሳም ስልክ በደወልንበት ወቅት  ለተጨማሪ ህክምና ወደ ውጭ በመውጣታቸው ልናገኛቸው አልቻልንም። በዚህ ጉዳይ የተሰራውን ዝግጅት በቅርቡ የምናቀርብ መሆናችንን ለመግለጽ እንወዳለን።

Tuesday 10 December 2013

ተከብሮ ያላስከበረ ሕገ-መንግስት

December 8, 2013
ይድነቃቸው ከበደ
ህዳር 29 ቀን 1987 ዓ.ም ሕገ-መንግስቱ የፀደቀበት ቀን ነው፡፡ይህንንም ተከትሎ በመንግስት አሳሳቢነት እልፍ ሲልም አስገዳጅነት ህዳር 29 በየዓመቱ ከተለያዩ ጎሳ የተወጣጡ ሰዎች ተሰባስበው በመንግሰት ሹማምንቶች ፊት በአደባባይ ከበሮ የሚደለቅበት ቀን ነው፡፡ይሁን እንጂ የአብዛኛው ኢትዮጵያዊያን መልካም ፍቃድና ተሳትፎ ባልታየበት የፀደቀው ህገ መንግስት በብዙሃን ዘንድ ተቀባይነቱ ጥያቄ ውስጥ የገባ ነው፡፡በዚህም መሠረት ከቃሉ አጠቃቀም ጀምሮ እስከ አከባበሩ ክብረ በዓል አብዛኛዉ ሰው እኔንም ጨምሮ ግድ አይሰጠንም፡፡Ethiopian political commentator from Addis Ababa, Ethiopia. Ydnekachew Kebede
‹‹ይህ ህገ-መንግስቱን የመነዳ ተግባር ነው!!!›› ከገዢው መንግስት ተደጋግሞ የሚሰማ ለመፈረጅ ወይም ለመከሰስ የሚጠቀሙበት ቃል ነው፡፡ አንድ ወዳጄ እንዲህ አለኝ ‹‹ ይህ ህገ መንግሰት ዝም ብሎ የተደረደረ ብሎኬት ነው እንዴ የሚናደው ?›› በማለት ሲተች ሰምቸዋለው፡፡በመናድ እና ደግፎ በማቆየት ላይ የተመሠረተሁን  ህገ መንግስት እጅግ በጣም ብዙ ነገር ተብሎለታል፡፡
እየተንገዳገደ ያለው ህገ መንግስት ከአፀዳደቁ ጀምሮ የሚቀሩት ድንጋጌዎች መኖራቸው ለማንም ግልፅነው፡፡ ቢሆንም ፀድቆ በተግባር ላይ የሚገኘው ህገ መንግስት ዋጋ እንዳይኖረው እያደረገ ያለው የገዢው መንግስት አካሄድና ተግባር መሆኑ በአጭሩ ለማሳየት እሞክራለው፡፡
1ኛ. መንግስት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም፤ሃይማኖትም በመንግስት ጣልቃ አይገባም የሚለው በሕገ መንግስት አንቀጽ 11 ንዕሱ አንቀፅ 3 ተደንግጎ የሚገኝ ነው፡፡ይሁን እንጂ ገዢው መንግስት በሃይማኖት ላይ ቀጥተኛ ጣልቃ ገብነት እየፈፀመ ይገኛል፤ለዚህም ጥሩ ማሳያ የሚሆነው በእስልምና አይማኖታ እየተፈፀመ ያለው በደል ነው፡፡በደሉ በይፋ የወጣ ሲሆን በተለይ ለእምነታችን እንቢኝ ያሉ ለሞት፣ለእስርና ለእንግልት ተዳርገው ይገኛሉ፡፡ በተጨማሪ በኦርቶዶክስ እምነት ውስጥም ጣልቃ ገብነቱ እንደተጠበቀ ነው፡፡ገዳማትና አድባራት በልማት ስም ፈርሰዋል የተቀሩት ቦታቸው ተጎምዶ ተወስዶል በዚህም ምክንያት የሀይማኖት አባቶችና ጥቂት የማይባሉ የእምነቱ ተከታዮች ለእስርና ለእንግልት ተዳርገዋል፡፡
ከምንም በላይ ደግሞ በሁሉም በተለይ በኦርቶዶክስና በእስልምና የሀይማኖቱ መሪዎች (አባቶች) ሹመታቸው ከሚያመልኩት አምላክ እና ከምዕመናኖ የመነጨ ሳይሆን በመንግስት ቀጥተኛ ጣልቃ ገብነት የተፈፀመ ነው፡፡
2ኛ. የመንግስት አሠራር ለሕዝብ ግልፅ በሆነ መንገድ መከናወን አለበት፡፤ በሕገ መንግስት አንቀጽ 12 ንዕሱ አንቀፅ 1 ተደንግጎ የሚገኝ ነው፡፡ቢሆንም ከታችኛው የስልጣን እርከን ከሆነው ከቀበሌ ጀምሮ እስከላይኛው የመንግስት ባለስልጣናት አማከኝነት የሚከናወኑ የመንግስት አሰራሮች ግልፅነት እጅግ በጣም ጠባብ ነው፡፡በመሆኑም ህብረተሰብ በአገሩ ጉዳይ ቀጥተኛ ተሳታፊ በመሆን በመንገስት አሠራር ላይ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ አልተደረገም፡፡
በዚህም ምክንያት የመንግስት አሠራር ለሙሱና የተጋለጠ ነው፤ሙሱና በአሁን ወቅት በአገራችን ህጋዊ እስከመሆን ደርሷል፡፡በመሆኑም ማናኛውም የመንግስት ኃላፊ ኃላፊነቱን ወይም ስልጣኑን መሠረት አድርጎ ሲበድል እንጂ ለበደሉ ተጠያቂ ሲሆን አልታየም፡፡ስለዚህም የመንግስት አሠራር በየትኛውም ደረጃ ለህዝብ ግልፅ አይደለም ይህ ደግሞ የህገመንግስቱ ድንጋጌ ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ ነው፡፡
3ኛ. ማንኛውም ሰው ሰብዓዊ በመሆኑ የማይደፈርና የማይገሰስ በሕይወት የመኖር፣የአካል ደህንነትና የነፃነት መብት አለው፡፡ተብሎ በህገመንግስቱ አንቀፅ 14 ተፅፎ ይገኛል፡፡ነገር ግን የሰው ደህንነትን ለመጠበቅ የተቋቋመው የደህንነት መስሪያ ቤት በየደኑና በየጫካው የስንቱን ሰው ህይወት እንዳጠፋና የአካል ጉዳት እንዳደረስ የሚያውቀው ያውቀዋል፡፡ በተጨማሪ ይህ የነፃነት መብት ገዢው መንግስት በችሮታ ወይም በፍቃዱ የሰጠን እንጂ ሰው በመሆናችን ያገኘነው መብት እንዳልሆነ በሚያሳብቅ መልኩ በሕይወት የመኖር፣ የአካል ደህንነትና የነፃነት መብት በገዢው መንግስት መልካም ፍቃድ ላይ የተመሠረተ እስከሚመስል ደረስ ተደርሷል፡፡
4ኛ. ማንኛውም ሰው ጭካኔ ከተሞላበት ፣ኢሰብዓዊ ከሆነ ወይም ክብሩን ከሚያዋርድ አያያዝ ወይም ቅጣት የመጠበቅ መብት አለው፡፡የሚለው በህገመንግስቱ አንቀፅ 18 ላይ ይገኛል፤ ይህ የህገመንግስት ድንጋጌ መሸራረፍ ሳይሆን መገርሰስ የሚጀምረው በህገመንግስቱ በተቋቋመው በህግ አስፈጻሚው አካል ነው፡፡
በመሆኑም ክብርን ለማወረድና ጭካኔን ለማሳየት የሰለጠኑ አሰቃዮችና ማሰቃያ ቦታዎች መኖራቸው የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡ ነገሩን ለማነፃፀር እንዲረዳ  ፖለቲከኛ ወይም በህግ ጥላ ስር ያለ ሰውን ይቅርና ስታዲዮም እግር ኳስ ለመመልከት ወራፋ የሚጠብቅ በወረፋ ምክንያት ለተነሳ አለመግባባት ፖሊስ እንዴት አድርጎ እንደሚቀጠቅጥ ዱላውን የቀመሰ ያውቃል፡፡
5ኛ. በጥበቃ ሥር ያሉና በፍርድ የታሰሩ ሰዎች ሰብዓዊ ክብራቸውን በሚጠብቅ መልኩ የመያዝ እና ከሰዎች ወይም ከጠያቂዎቻቸው የመገናኘት መብት አላቸው፡፡ በማለት በህገመንግስቱ አንቀፅ 21/1እና2 ተፅፎ ይገኛል፡፡ይሁን እንጂ ነፃ ጋዜጠኞች እና የፖለቲካ እስረኞች አያያዛቸው ክብርን ከመንካት አልፎ በህይወታቸው ላይ አደጋ የሚያስከትል ነው፡፡በተጨማሪ ከቤተሰብ፣ከወዳጅ መጠየቅ የማይሞከር ነገር ነው፤ የመጠየቅ እድል ያላቸው እስረኞች እድላቸው በቅድመ ሁኔታ ላይ የተመሠረተ ነው፡፡
6ኛ. ማንኛውም ሰው ያለማንም ጣልቃ ገብነት የአመለካከት እና ሐሳብን በነፃ የመያዝና በማንኛውም የማሰራጫ ዘዴ የመግለፅ ነፃነት አለው፡፡የሚለው በህገመንግስቱ አንቀፅ 29 ተፅፎ ይገኛል፡፡ በእርግጥ ይህ መብት ገደብ ሊጣልበት እንደሚችል በህገ መንግስቱ ላይ ተገልፆ የተቀመጠ ሲሆን ገደብ ግን መሠረታዊ የሆነውን መረጃን የመስጠት እና የማግኘት እንዲሁም አስተሳሰብ ላይ ወይም አመለካከት ላይ ውጤት እንደማይኖረው በህገመንግስቱ ተገልፆ ይገኛል፡፡
ይሁን እንጂ አሳብን በነፃ ማሰብና ማንሸራሸር በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ እጅግ አዳጋች ነው፡፡ነፃ አሳብ የሚንሸራሸርባቸው ነፃ ጋዜጦችና መፅሔቶች ምን ያህል አሉ ? እርግጥ ነው ገብያውኑ መሰረት ያደረጉ መዝናኛ ላይ ያተኮሩ መፅሔትና ጋዜጣ ለቁጥር በዝተው ይሆናል፡፡ ግን ሁሉ ነገር በአገር ነው የሚያምረው! ታዲያ ስለ አገር በነፃ አሳብ የሚንሸራሸርበት መፅሔትና ጋዜጣ ምን ያኸል ነው ? ጋዜጠኞችን በማሰቃየት፣በማሰር እና እንዲሰደዱ በማደረግ ኢትዮጵያ በዓለም ላይ መጥፎ ሪከረድ አስመዝግባለች፡፡መንግስትን ተችቶ የፃፈና ፁሁፉ የወጣበት ጋዜጣ ወይም መፅሔት ጨምሮ ሁሉም ተጠራርጎ ቃሊቲ የሚገባበት ወይም አደገኛ ዛቻና መስጠንቀቂያ የሚሰጥበት ደረጃ ላይ ተደርሷል፡፡
7ኛ. ማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋር በመሆን መሣሪያ ሳይዝ ሠላማዊ ሠልፍ እና ስብሰባ የማድረግ ነፃነትና አቤቱታ የማቅረብ መብት አለው፡፡ ተብሎ በህገመንግስቱ አንቀፅ 30/1 ላይ ይገኛል፡፡ ለዚህ ማሳያ የሚሆን የቅርብ ጊዜ አይን ያወጣ የህገመንግስት ጥሰት ማቀረብ ይቻላል፡፡በሳውዑዲ በሚገኙ ወገኖቻችን ላይ እየተፈፀመ ያለው ግፍና በደል ይቁም፣ይህንንም የፈፀሙ ለፍርድ ይቅረብ በማለት አቤቱታ ለማቅረብ የተጀመረው ሠላማዊ ሠልፍ በፖሊስ ዱላ እና እስራት ነው የተጠናቀቀው፡፡ በተጨማሪ በመንግስት እየታየ ያለው የአስተዳደር ብሉሹነት ለማመልከት እና ምላሽ ለማገኘት የተጠሩ የተለያዩ የተቃውሞ ሰልፎች እና ስብሰባዎች በመንግስት ቀጥተኛ ትእዛዝ ተከልክሏአል፡፡ሠላማዊ ሰልፍ ማድረግ እና አቤቱታ ማቅረብ መብት ነው! በማለት ክልከላውን ወደ ጎን በመተው አደባባይ ለመውጣት የሞከሩ ለእስርና ለድብደባ ተዳርገዋል፡፡በመሆኑም የተቃውሞ ሠልፍና ስብሰባ በማድረግ አቤቱታ በኢትዮጵያ ማድረግ የሞት ሽረት ትግልና ጥያቄ ከሆነ ሰንብቷል፡፡
8ኛ. የዳኝነት አካል ከማንኛውም የመንግስት ባለስልጣን ሆነ አካል ተፅዕኖ ነጻ በመሆን በሙሉ ነፃነት ከህግ በስተቀር በሌላ ሁኔታ አይመሩም፡፡በማለት በህገመንግስቱ አንቀፅ 79 እና በተከታዮቹ ንዑስ አንቀፅ ሰፍሮ ይገኛል፡፡ ይሁን እንጂ በየትኛውም ደረጃ የሚገኙ ዳኞች የመንግስት አስፈፃሚ አካል ከሆነው ነው ሹመታቸውን የሚያገኙት፡፡በመሆኑም ከመንግስት ጋር ቀጥተኛ ግኝኙነት ያላቸው የፍርድ ውሳኔዎች ምንያኽሉ በህግ እና በህሊና ላይ የተመሠረቱ ናቸው ? በተለይ የህሊናና የፖለቲካ እስረኞች የፍርድ ሂደታቸው ምን ይመስል ነበር ? እነዚህን እና መሰል ዳኝነቶችን ከግምት ውስጥ በማስገባት በህገመንግስቱ የሰፈረው ነጻ ዳኝነት ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ ነው፡፡
9ኛ. የሀገሪቱ የመከላከያ ሠራዊት የጎሳዎች ሚዛናዊ ተዋጽኦ ያካተተ ይሆናል፡፡ ተብሎ በህገመንግስቱ አንቀፅ 87/1 ተደንግጎ ይታያል፡፡ነገር ግን በየድንበር እና በተልኮ ጭዳ ከሚሆነው ውጪ አብዛኛው የሠራዊቴ አባል እና አዛዥ የአንድ ጎሳ ስብስብ ነው፡፡ ስለዚህም ሠራዊቱ የማነው የኢትዮጵያ ወይስ ወደሚል ጥያቄ እያመራ ይገኛል፡፡
10ኛ. በየደረጃው ትክክለኛ ምርጫ እንዲካሄድ ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ይቋቋማል፡፡የሚለው በህገመንግስቱ አንቀፅ 102 ላይ ይገኛል፡፡ይሁን እንጂ የምርጫ ቦርድ ሃላፊዎች ሹመታቸው ከመንግስት መልካም ፍቃድ የመነጨ ሲሆን አሰራራቸውም ለገዥው መንግስ በእጅጉ በጣም ያደላ ነው፡፡ስለዚህም ምርጫ ቦርድ ህገመንግስቱን መሠረት አድርጎ ነጻ እና ገለልተኛ ነው ለማለት ከበድ ድፍረትን የሚጠይቅ ነው፡፡
በመሆኑም እነዚህ እና መሰል የህገመንግስቱ ድንጋጌዎች ጥሰት ወይም በእነሱ ቋንቋ የመንድ ተግባር እየተፈፀመ ያለው በህገመንግስቱ በየወንዙ ዳር የሚማማለው ገዥው መንገስት ነው፡፡ ህገመንግስት የበላይ ህግ ነው፡፡ማንኛውም ህግ፣ልማዳዊ አሰራር እንዲሁም የመንግስት ባለስልጣን አሰራር ከህገመንግስቱ የሚቃረነረ ከሆነ ተፈፃሚነት አይኖረውም ፡፡ የሚለው አንቀፅ 9 ንዑስ አንቀፅ 1 የገዥው መንግስት ደራሽ ዉሃ ጠራርጎ ወስዶታል፡፡ ስለዚህም የብሔሮ፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን የሚለውን መጠሪያ ስም በመስጠት ከበሮ ተይዞ የሚደለቅለት እና የሚከበረው ህገመንገስት መልሶ ካላስከበረ ፌሽታው እና ቀረርቶው ከምን የመነጨ ነው  ?

Doctor Arkebe Oqubay flying like a pig

December 9, 2013
by Abebe Gellaw
Until recently, Arkebe Oqubay was known to have spent much of his life on projects of bloody conflicts, corruption, tyranny or gross violation of human rights. It was a  total surprise when one of TPLF’s topguns was introduced as a record-breaking scholar.
It emerged that Arkebe has been bragging to friends, relatives and admirers since last October that he got a Ph.D from the University of London’s School of Oriental and African Studies (SOAS) with great honor and distinction. He claimed that he shattered academic records, an achievement that guaranteed his name a special place in the honor list of the school. That is good for him, but why is SOAS contradicting this amazing scholar who claims to be the first to hold his PhD in record time and first for his unblemished dissertation?Arkebe Oqubay was known to have spent much of his life on projects of bloody conflicts
On November 8th, Isayas Astebeha Abaye, a well-known apologist and flunkey of the dictatorship in Ethiopia, published a “breaking news” story on Aigaforum.com trumpeting Arkebe’s miraculous and unique intellectual prowess.
According to Isayas Astebeha Abaye, who got the story from the horse’s mouth:
This week Dr. Arkebe Oqubay was recognized as an outstanding Scholar in the Academic [sic] circles of London. He broke the academic record of doctoral school in the University of London (School of Oriental and African Studies) for the first time by finishing the four year program within 23 months with high honor and great distinction. In this century old institution (established in 1916), the doctoral program is set for four years maximum to defend and finish the doctoral thesis. Most of the candidates defend and finished with difficulties and hardship (if they are lucky and extraordinary).Arkebe has finished [sic] within 23 months and surprised the department of Development Studies, the university professors and students altogether [sic]. Never heard of such great achievements in such short period of time, what a person!!!!!!! His external examiners from Cambridge and other well known [sic] academic institutions awarded him “PASS WITH OUT [sic] CORRECTION” on the spot; which means great distinction with great honor (never happened and never heard of).Arkebe did it!!!! His name and his country’s name is in the history book of this famous University [sic]. What an achievement!!! We are proud of him!!! Congratulations to Dr. Arkebe Oqubay. [That was Isayas Abaye’s badly scripted story, which not only breaks all the basic rules of news reporting but also published online WITHOUT CORRECTION or verification.]
The brazen “story” about Arkebe’s amazing accomplishments in London trended well on the social networking sites creating buzz and excitement among TPLF’s faithful drones who danced and ran victory laps to Isayas Abaye’s song: “Dr Arkebe breaks the record in a century old Academic Institution [sic].”
The big trouble with Arkebe’s “record-breaking” academic achievement is that it was manifestly false. As the story was evidently dubious and nonsensical, we had to send a copy of Aigaforum’s story to SOAS and the University of London for fact-checking and verification. The school’s Directorate of External Relations spent almost three weeks digging through its records trying to verify the identity of the phenomenal scholar “whose name and his country’s name” were said to have entered the “history books”, just to borrow the words of the amateur reporter.
After careful and lengthy investigation, Vesna Siljanovska, SOAS’s communication officer, verified that Arkebe Oqubay Metiku had indeed completed his doctoral studies at SOAS in October 2013. While trying to avoid some of the most awkward questions about the newmint scholar, she disclosed that his dissertation focused on the “industrial policy of Ethiopia”. Siljanovska also indicated that the school never heard of the “scholar’s” record-breaking feats.
SOAS communication officers also tried to explain that the so-called record-breaking achievement is common not only at SOAS but also in other UK universities. “Like many other UK universities, a PhD is usually at least three years in length but candidates can apply to submit after two years of full – time enrolment subject to the approval of the Supervisory Committee and the Associate Dean (Research) of the relevant Faculty. While the majority of candidates studying for a PhD in the UK complete within three years, there are a number of students who complete in a longer or shorter time period,” SOAS said in a carefully crafted statement.
Prof. Christopher Cramer, who teaches in the Department of Development Studies at SOAS, also declined to discuss details about Arkebe’s miracles due to the university’s privacy policy. But Cramer wrote in an email that Arkebe achieved nothing extraordinary or unprecedented as claimed in the Aigaforum story. Prof. Cramer was clearly amused by the claim the first “no corrections thesis,” but he declared that the pompous claim was “completely untrue”.
Asked what Arkebe’s new research finding could be on “industrial policy in Ethiopia” that he and his TPLF tyrannical clique formulated and imposed on the poor nation that they have brutalized and robbed for over two decades, Prof. Cramer, who was apparently the good doctor’s adviser, also declined to comment. It should be remembered that Arkebe was one of the architects of the Endowment Fund for the Rehabilitation of Tigray (EFFORT), the illegal TPLF-controlled business conglomerate that is widely accused of symbolizing apartheid-like crony capitalism sucking the blood and gnawing the bones of the poor people of Ethiopia
One of Ethiopia’s leading rights advocates, Prof. Alemayehu Gebremariam, finds the revelation quite interesting. He says  the fact that Arkebe was approved to do his dissertation on “industrial policy in Ethiopia”, a policy paper that he and his TPLF sidekicks had been toying around since TPLF took power in 1991, raises legitimate questions.
“If Arkebe had indeed finished his dissertation in “record time”, it is because he was copyediting his old policy papers instead of doing original research, which is what a doctoral dissertation is supposed to be,” the professor said.
“If Arkebe’s dissertation is of such an exceptional scholarly and scientific quality sufficient to shift paradigms, why is it not published in whole or in part in the leading scholarly journals of the world?” he asked.
Arkebe has a history of being a clumsy publicity hog. When he was the mayor of Addis Ababa, he once plastered his mugshot on huge promotional billboards under the guise of raising awareness on the HIV/AIDS epidemic. Azeb Mesfin, wife of the late dictator Meles Zenawi and Arkebe’s arch foe, reportedly ordered the removal of his outsize images from the city centers just within a few days. She reportedly felt that Arkebe would say and do anything for self-promotion and self-aggrandizement.
Prof. Alemayehu wonders why TPLF’s tyrannical midgets seek to puff themselves up as intellectual giants. “Those who aspire to achieve terminal degrees do so because they love research, discovery of new knowledge, truth and make significant contributions to the body of knowledge in their field of study. Conferring a Ph.D. on the unenlightened is like dressing a hoodlum in a designer suit. It looks good but everyone knows that the man under the suit is still a hoodlum,” he commented.
Isaias Abaye and his bosses should take their own advice. He recently warned us about Member of the European Parliament and a great friend of Ethiopia, the Honorable Ana Gomes, who reduced the late tyrant Meles Zenawi into dust with her sharp commentary. To the dismay of Zenawi’s worshippers like Isayas, she bluntly stated that the demise of the cruel and deceitful dictator was a good opportunity for Ethiopia.
In his silly tantrums against the respected MEP, Isayas lamented:   “Unlike the early days of the online media, we have all learned not to be easily shocked, surprised, or overly excited by what we read online. Mostly, we try to verify the reliability and reputation of the source. When we read Ana Gomez’s [sic] interview with a journalist from a local private media, we didn’t even doubt the authenticity of this story knowing it is the angry Hana Gobeze….
Perhaps Isaias and Arkebe do not realize that in  the Information Age liars, cheats, con artists and fibbers do not last a nano second without being exposed. Maybe the entire pack of TPLF’s liars, robbers and tyrants can take a lesson from this amusing episode. They should know, “Three things cannot be long hidden: the sun, the moon, and the truth.” If Arkebe must be extolled for breaking records, it should be for “record breaking lies” and for telling lies with disgrace. But he must know that his lies will NOT PASS WITHOUT CORRECTION.
It is said that old habits die hard. Sadly Arkebe miserably failed to learn that knowledge must be based on truth. It also appeared that SOAS also failed to equip its windbag graduate with the basic skills of researching at least easily detectable and verifiable facts. Yet SOAS can be forgiven as neither PhD nor professorship changes the character of pigs that are identical with the ones in George Orwell’s Animal Farm. .
In the footsteps of their fallen demigod Meles Zenawi, TPLF’s dictators, robber barons, torturers and their heartless accomplices such as Arkebe and pedler of lies Isayas Abaye have a guaranteed place, not in honor books, but in the trashbin of history. No unimpressive PhD, professorship or self-imagined glories and trophies will change the fate of these dictatorial fibbers.
In the world of Aigaland’s Animal Farm, pigs may soar and fly in the skies. But in the real world we all live in, TPLF’s pigs can only dream of being eagles or falcons. Whatever any pigs dream of, they have to live with the fact that they are just pigs. This is the inconvenient truth that no genius pig with a PhD from SOAS, Harvard or Stanford can change and refute.
Speaking of stellar academic achievement, a recent true story about a truly outstanding Ethiopian scholar has filled our hearts with joy and pride. It was disclosed a couple of weeks ago that Dr. Mulatu Lemma, an award-winning mathematicsDr. Mulatu Lemma, an award-winning mathematics professor professor at Savannah State University, was honored as the 2013 Georgia Professor of the Year by the Carnegie Foundation for Advancement of Teaching and the Council for the Advancement of Support of Education (CASE).His name and his country’s name is in the history book of academia for being one of the top mathematics professors in the United States. What an achievement!
It should be noted that Arkebe’s record-breaking tall tales of being the most outstanding PhD holder in the entire history of SOAS, even if his dream for academic grandiose has now fallen apart, must be recognized at least for the effort. The “scholar”, who has not yet published a single academic paper or a mini-newspaper article, must be honored namedDoctor Arkebe Kedadaw!
While the warriors of truth and freedom such as Eskinder Nega, Reeyot Alemu, Andualem Aragie, Bekele Gerba and Ustaz Abubakir, are languishing in TPLF dark dungeons, Arkebe had the luxury of jetting to Europe in search of academic grandiose. Quite certainly Arkebe is unlikely to get the honors and accolades he craves badly while he is alive. So just like Zenawi, he deserves to be honored with a state funeral!

አቶ ሙሐመድ ኢብራሒም ማእከላዊ እስር ቤት ዉስጥ በደረሰባቸው ድብደባ ህይወታቸዉ ማለፉ፤ ሆድ-እቃቸዉ ተከፍቶ ኩላሊታቸዉ መሰረቁ ታወቀ

December 9, 2013

“አስክሬን ምንሊክ ሆስፒታል ሄደን እንድንወስድ ስልክ ተደወለልን፤ ለሞቱ ከደነገጥነዉ በላይ አስክሬኑን ስንመለከት ፍጹም ተረብሸናል፤ ከአዉሬ አፍ የተረፈ አስክሬን ነበር ሚመስለዉ…ሰዉነቱ ተቦጫጭቋል!” ጓደኞች

ዋሽንግተን ዲሲ፤ ህዳር 30/2006 (ቢቢኤን) ፦ በአዲስ አበባ ዉስጥ በቦሌ ክፍለ ከተማ ነዋሪ የነበሩት አቶ ሙሐመድ ኢብራሒም ቀደም ሲል በጥቅምት 4/2006 በአካባቢዉ ላይ ፈንድቶ ከነበረዉ ቦንብ ጋር በተያያዘ መልኩ ለምርመራ ማእከላዊ እስር ቤት መግባታቸዉ እና በማእከላዊ ቆይታቸዉ ምግብ እንዳይገባላቸዉ ቤተሰብ እንዳይጠይቃቸዉ መከልከሉም ለማወቅ ተችሏል።TPLF, EPRDF latest victim
እንደ አቶ ሙሐመድ ጓደኛ አገላለጽ ግለሰቡ ለተጠረጠሩበት ወንጅል የሚያበቃቸዉ ጉዳይ ባይኖርም፤ከገቡበት ማእከላዊ እስር ቤት በደረሰባቸዉ ከፍተኛ ድብደባ በህይወት መዉጣት አልቻሉም።
ለሐያ ዘጠኝ ቀናት ማእከላዊ እስር ቤት የታሰሩት አቶ ሙሐመድ ምን ያህል ድብደባ እንደደረሰባቸዉ ባይታወቅም ጭንቅላታቸዉ በጣም መጎዳቱን፣ሰዉታቸዉ እንደበለዘ፣ብዙ ሰንበሮች መታየታቸዉ፣ሆድ እቃቸዉ ተከፍቶ ኩላሊታቸዉ መሰረቁን ለአስራ ሁለትአመታት የሚያዉቋቸዉ ጓደኛቸዉ በሐዘን ይገልጻሉ።የዱር አዉሬ ቦጫጭቆ የገደለው ይመስላል በማለት ሁናቴዉን የሚገልጹት ጓደኛ ከመንግስት አካላትም ይሁን አስክሬኑ ከመጣበት የሚኒሊክ ሆስፒታል ስል አቶ ሙሐመድ አሟሟት የተሰጠ መረጃ አለመኖሩን፤ በደም በተጨማለቀ ከፈን የተከፈነ አስክሬን ብቻ መመለሱን ገልጸዋል።
ቤተሰቡ ጉዳዩን ለሰብአዊመብት ተሟጋች ለሆኑ ድርጆቶች እንዳያመለክት ከፍተኛ ዛቻ ደርሶበታል፤በቅርበት የሚያዉቋቸዉ እንኳ በሞታቸዉ ከማዘን በስተቀር ስለ አሟሟታቸዉ ከፍርሃት የተነሳ መናገር አይችሉም በማለት የሚያስረዱት ጓደኛቸዉ ሁሉም ለሞቱ ከደነገጠዉ በላይ አስክሬኑን በማየት ተሸማቋል ይላሉ።
በጥሩ ስነምግባራቸዉ የሚታወቁት አቶ ሙሐመድ ኢብራሒም ሐማኖትን ተግባሪ፣ የቤተሰብ አስተዳዳሪ ከመሆን በስተቀር አገርን ወገንን ሊጎዳ በሚችል የአሸባሪ ተግባር የሚጠረጠሩ አይደልም በማለት በሐዘን የሚናገሩት ጓደኛ ሟቹ የሰባት ልጆች አባት እንደነበሩ ቤተሰቡም ለአደጋ መጋለጹንም አስረድተዋል።
በጥቅምት 4/2006 መንግስት በቂ መረጃ ለህዝብ ማቅረብ ባልቻለበት፤ የመንግስት ደህነነቶች አለም አቀፋዊ ትኩረትን ለመሳብና ፖለቲካዊ ጥቅምን ለመጎናጸፍ በቦሌ ክፍሌ ከተማ አደርሰዉታል ተብሎ በሚነገረዉ የቦንብ ፍንዳታ፤ ማመካኛን ለማግኘት የሱማሌ ብሔር ተወላጅ የሆኑትን የአቶ ሙሐመድ ህይወትን መንግስት መስዋዕት አድርጓል በማለት አስተያያት የሚሰጡ ወገኖች አሉ።በትላንትና እለትዉ የብሔር ብሔረሰቦችን ቀን በጅጅጋ ከተማ ድረስ ባሸበረቀ መልኩ አከበርኩ ለሚለዉ መንግስት፤ የአገሩን ዜጋ በብሔር ነጥሎ ማእከላዊ እስር ቤት አስገብቶ መግደሉ ለመንግስቱ አሳፋሪ ከመሆኑም ባሻገር የስርዓቱን መላሸቅ አመላካች ነዉ የሚሉም አሉ።
የአቶ ሙሐመድ ኢብራሒም ታስሮ ለህልፈት መብቃት፤ የሆድ እቃቸዉ ተቀዶ የኩላሊታቸዉ መሰረቅ ከፍተኛ ምርመራ የሚያሻዉ ቢሆንም፤በሟች አስክሬን ላይ የተፈጸመው ወንጀል ስርዓቱ በህይወት ባሉ ብቻ ሳሆን በሙታንም ላይ ግፍ እንደሚፈጽም የሚያረጋግጥ ነዉ፤ በሐሰት አስሮ በመደብደብ፣በመግረፍ፣እስር ቤት ዉስጥ ከማሰቃየት አልፎ፤ ታሳሪዎች እስር ቤት ዉስጥ ሲሞቱ ሆድ እቃ ተከፍቶ የሰዉነት አካል መቸርቸር ተጀምሯልና!.. ኢትዮጵያ ወዴት እያመራች ነዉ? የሚለዉ ጥያቄ የብዙሐኑ ነዉ።

The man who taught Mandela to be a soldier

In July 1962, Col Fekadu Wakene taught South African political activist Nelson Mandela the tricks of guerrilla warfare – including how to plant explosives before slipping quietly away into the night. Mr Mandela was in Ethiopia, learning how to be the commander-in-chief of Umkhonto we Sizwe – the armed wing of the African National Congress (ANC).
The group had announced its arrival at the end of 1961 by blowing-up electricity pylons in various places in South Africa.
His mission was to meet as many African political leaders as possible and garner assistance for the ANC, including money and training for its military wing.
And to be moulded into a soldier himself.
During this trip, he visited Ethiopia twice and left a deep impression on those who met him during his stay in the Ethiopian capital, Addis Ababa.
‘Made others laugh’
Col Fekadu said Mr Mandela was a good student
“Nelson Mandela was a very strong and resilient student, and he took instruction well and was really very likeable,” Col Fekadu said.
“You couldn’t help but love him.”
Col Fekadu was a corporal when he trained Mr Mandela. He was a member of a specialist police force – the riot battalion – based in the suburbs of Kolfe, in barracks which are still used today.
He remembers a “happy, cheerful person” who “concentrated on the task in hand”.
“He was polite, always happy and you never saw him lose his temper,” he said.
“He laughed easily and made others laugh as well.”
Col Fekadu says he was responsible for training Mr Mandela in sabotage and demolitions and how to stage hit-and-run attacks.
The day’s theory lessons were put into practice during night-time exercises.
Mr Mandela was a good student, hardworking and physically strong – but sometimes too robust and too enthusiastic for his own good, the colonel recalls.
“Physically he was very strong and well-built. But sometimes during the training he would get ahead of himself.
Col Fekadu had been told to train Mr Mandela by his commanding officer, General Tadesse Birru, the assistant police commissioner who had played a key role in crushing an attempt at the end of 1960 to overthrow Emperor Haile Selassie. He was later executed by the Derg regime of Mengistu Haile Mariam.
Back in 1962, Col Fekadu did not realise the significance of the South African politician he had been instructed to turn into a soldier.
“All we knew was that he was our guest from abroad and that he would spend some time with us,” he said.
“Everything was kept very secret. We were kept in the dark.”
Mr Mandela was in Ethiopia at the invitation of the emperor, an ardent supporter of Africa’s decolonisation and African unity.
At the time, Ethiopia had one of the strongest armed forces on the continent.
Its troops were part of the UN peacekeeping operation during the Congo crisis in 1960 and a decade earlier Ethiopian soldiers had fought in the Korean war.
And the emperor had invited many other African liberation struggle fighters to be trained on Ethiopian soil.
As well as learning how to commit acts of sabotage, Mr Mandela’s military training also included briefings on military science, how to run an army and how to use a gun.
He was also taken on long treks carrying his knapsack, rifle and ammunition.
This was one of Mr Mandela’s favourite activities during his military training, and he writes about it with affection in his Long Walk to Freedom autobiography: “During these marches I got a sense of the landscape, which was very beautiful… people used wooden ploughs and lived on a very simple diet supplemented by home-brewed beer. Their existence was similar to the life in rural South Africa.”
‘Talkative’
He was much taller and broader than most of the police cadets.
And, as well as going on fatigue marches through the countryside, he would exercise out in the open in the grounds of the barracks.
One person who took a particular interest in the tall stranger in his midst was Tesfaye Abebe, who was working in Kolfe as the head of the battalion’s music and drama department.
He recalls Mr Mandela running around a big field in the compound – which today doubles up as a running track and a parade ground.
“He would do squats and jumping jacks. He followed that exercise routine religiously every morning.”
A curious Mr Tesfaye snatched conversations with Mr Mandela when he and his trainer came into the canteen for lunch.
“Security was quite tight and we weren’t really allowed to approach him.”
But, he says, Mr Mandela was “very friendly and talkative” and explained apartheid to him and how the ANC intended to fight it with guerrilla warfare and political activism.
On a couple of occasions, the police band – in which Mr Tesfaye was the pianist – played for Mr Mandela in the officer’s club.
“He really enjoyed that. He was really happy when we played for him.”
Mr Mandela’s military training in Ethiopia was supposed to last six months – but after only two weeks he was called back to South Africa by the ANC.
He had already spent seven months out of the country – and he was needed back home.
As Mr Mandela left Ethiopia, Gen Tadesse presented him with a pistol and 200 rounds of ammunition – a gun that is thought to be buried somewhere on Lillesleaf Farm, where in 1963 other ANC leaders were arrested and sentenced to life alongside Mr Mandela in the famous Rivionia trial.
Mr Mandela himself had been arrested on 5 August 1962 – for leaving the country illegally , shortly after his return from his trip around Africa – and still in the military fatigues in which he had been trained in Ethiopia.
http://www.bbc.co.uk/

ከሳውዲ ተመላሽ ዜጎች ንብረታቸው በጉምሩክ እንደተወሰደባቸው ተናገሩ

ህገወጥ ናችሁ ተብለው ከሳውዲ አረቢያ ወደ አገራቸው የተመለሱ ኢትዮጵያዊያን፤ ለበርካታ አመታት ለፍተን ያፈራነውን ንብረት ይዛችሁ መግባት አትችሉም ተብሎ ተነጥቀናል፡፡ የፍተሻ ሰራተኞች ሻንጣዎቻቸውን በመፈተሽ፣ ሞባይል ከአንድ በላይ ከያዙ ትርፉን በማስቀረት፣ አዳዲስ አልባሳት እና ኤሌክትሮኒክስ ቁሰቁሶች የተወሰኑትን ብቻ በመፍቀድ እና ያመጡትን ወርቆች ግራም በመቀነስ ንብረታቸውን እየወሰዱባቸው እንደሆነ ተመላሾቹ ገልፀዋል፡፡ መሃመድ አባመጫ የተባለ የሳኡዲ ተመላሽ፤ ከሳውዲ ስድስት ሻንጣ ይዞ መምጣቱን ገልፆ፤ ቦሌ አውሮፕላን ማረፍያ ሲደርስ ግን ከሁለት ሻንጣ በላይ ይዞ መግባት እንደማይችል፣ ከአምስት ሞባይሎችም ሁለቱ ብቻ እነደተፈቀደለት ለአዲስ አድማስ ተናግሯል፡፡ የሳውዲ መንግስት ከአንድ ኪሎ በላይ ወርቅ ይዛችሁ መውጣት አትችሉም የሚል መመሪያ ማሳለፉን የጠቆመው ተመላሹ፤ ንብረቱን እዚያው ጥሎ ለመመለስ መገደዱን ገልጿል፡፡ የሳኡዲ መንግስት እንኳን ከወርቅ በስተቀር ሌላ ንብረታቸውን ሁሉ ይዘው እንዲወጡ መፍቀዱን የገለፀው መሃመድ፤ በአገራቸው ንብረታቸውን እንዳያስገቡ መከልከላቸው እንዳሳዘነው ይናገራል፡፡
ኤሌክትሮኒክስና ለቤተሰቦቹ ያመጣውን ልብሶች ቀረጥ ከፍለህ ነው የምትወስደው በመባሉ፣ ለሁለት ቀን በስደት ተመላሾች በተዘጋጀው ድንኳን ውስጥ ያለምንም ፍራሽና ልብስ ተኝቶ ንብረቱን ቢጠብቅም ማግኘት እንዳልቻለ ገልጿል፡፡ “ሳዑዲም እዚህም ሀገራችን ስንደርስ እየበደሉን ያሉት ሃበሾች ናቸው” ያለው መሃመድ፤ መንግስት በሚዲያ በተሟላና በተደላደለ መንገድ እንደሚቀበለን ቢገልፅም እዚህ የጠበቀን ግን ሌላ ነው ሲል ቅሬታውን ገልፆ “ሌላው ቢቀር እስካሁን ተመላሾቹን የሚያመላልሰው እንኳን የሳዑዲ እንጂ የኢትዮጵያ መንግስት አይደለም” ብሏል፡፡ ከሳኡዲ ካመጣችው ወርቅ ላይ ሃምሳ ግራሙን ብቻ እንደምትወስድ የተነገራት ተኪያ ሙሃመድን ያገኘናት በቁጭት መሬት ላይ እየተንከባለለች ነበር፡፡
ተኪያ እያለቀሰች እንደነገረችን፤ ለ14 ዓመት ሰርታ ከሶስት መቶ ሃምሳ ግራም በላይ ወርቅ እንዳጠራቀመች ገልፃ፤ በተፈጠረው ችግር ምክንያት ከሳውዲ እንድትወጣ ከመገደዷ በፊት ሙሉ ንብረቷን አስቀድማ ብትልክም እስካሁን እንዳልደረሰላት ትናገራለች፡፡ አሁንም፤ ከተመለሰች በኋላ የያዘቻቸውን ሻንጣዎች ለመውሰድ እንዳልቻለች የምትገልፀው ተኪያ፤ በፍተሻ ስም ሰራተኞቹ ሻንጣዋን በርብረው በማየት፣ ያመጣቻቸውን የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችና ሶስት ሞባይሎች መውሰዳቸው ሳይንስ፣ ሶስት መቶ ግራም የሚመዝን የወርቅ ንብረቷን እንዳታስገባ መከልከሏን በጩኸት ትናገራለች፡፡ ለምን ንብረቷን እንደከለከሏት ስትጠይቅም “እናንተ ነጋዴዎች ናችሁ፤ በስደተኞች ስም ያለቀረጥ ንብረት ለማስገባት ትፈልጋላችሁ” በማለት ሰራተኞቹ እንደመለሱላት ገልፃ፤ ጉዳዩን ለአለቆቻቸው ለማመልከት ብትፈልግም የሚያናግራት ሰው አለማግኘቷን ጠቁማለች፡፡ በዚሁ ስፍራ ያገኘናቸው በርካታ ተመላሾች፤ የንብረታቸው ጉዳይ እንዳሳሰባቸው ይናገራሉ። ንብረታቸውን ሳይዙ ወደቤተሰቦቻቸው ላለመቀላቀል በሚል የተሰበሰቡበት ካምፕ፣ ምንም ለማረፊያ የተመቻቸ አገልግሎት ባለመኖሩ መቸገራቸውንም ገልፀዋል፡፡ መንግስት የሚሰጣቸውን 900 ብር፣ በትራንስፖርትና በስልክ አገልግሎት እንደሚጨርሱ አክለው ተናግረዋል፡፡
በርካቶች በእቃዎቻቸው መታገድ በመበሳጨታቸው ጭቅጭቅና አላስፈላጊ ውዝግብ ውስጥ ለመግባት መገደዳቸውን ተመላሾቹ ይናገራሉ፡፡ “ስንመጣ የሚሰጠንን ሊሴ ፓሴን አይተው ማስተናገድ ሲገባቸው እነሱ ግን ንብረታችንን እየወሰዱብን ነው” በማለት የሚናገሩት ተመላሽ ዜጎቹ፤ “ምናልባትም ንብረት የላቸውም ብለው አስበውን ይሆናል፤ ነገር ግን በርካታ አመታት ስንቆይ መቼም ባዶ እጃችንን አንመጣም” በማለት በምሬት ይናገራሉ፡፡ “ዛሬ እቃችንን የከለከሉን ነገ ምን ተስፋ ይዘን ነው ተደራጅታችሁ ስራ ስሩ ለሚሉን?” የሚሉት እነዚህ ተመላሾች፤ “በመንግስት ላይ አመኔታ የጣልነው ሳውዲ ድረስ በተወካዮቹ አማካኝነት መጥቶ ባናገረን መሰረት ነበር፤ ነገር ግን የተገባልን ቃል ታጥፏል” ይላሉ፡፡ መንግስት ለጉዳዩ ትኩረት ባለመስጠቱ እና ለቤተሰብ መርዶ ባለመነገሩ፣ ለሚያውቋቸው ቤተሰቦች መርዶ ለመንገር ጭንቀት ላይ መሆናቸው ሌላ ችግራቸው እንደሆነ የተናገሩት ተመላሾች፤ አሁንም ቢሆን ሳውዲ ላይ ሃበሻዎችን በመኪና እየገጩ መግደል የሳውዲ ፖሊሶች የቀን ተቀን ስራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ታዲያ በዚህ አጣብቂኝ ውስጥ አምልጠው የሚመለሱ ዜጐችን ንብረት መቀማት ምን የሚሉት ተግባር እንደሆነ አልገባንም፤ በማለት አማርረዋል-ተመላሾቹ፡፡ ምናልባትም የፖለቲካ ማራመጃ ሊያደርጉን ነው በማለትም ስጋታቸውን አንፀባርቀዋል፡፡
ተመላሾቹ የተሟላ መጠለያ ተዘጋጅቶላችኋል በተባለበት ቦታ ሳይቀር፣ መተኛ ሥፍራ እንኳን እንዳልተዘጋጀ ሲረዱ ተስፋ መቁረጣቸውን እና ንብረታቸውን እንዳያስገቡ ሲከለከሉ፣ ተመልሰው በህገወጥ መንገድ ለመሰደድ ሙከራ መጀመራቸውን ይገልፃሉ፡፡ በጉዳዩ ላይ መልስ እንዲሰጡን የጠየቅናቸው የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በበኩላቸው፤ “ተመላሾቹ ስለንብረት የሚያነሱትን ጥያቄን በተመለከተ፤ እኛ ተመላሾች በሙሉ ንብረት እንደሌላቸው ነው የምናውቀው“ በማለት ተናግረዋል፡፡ አምባሳደሩ አልፎ አልፎ ባዶ እግራቸውን ከሳዑዲ የተመለሱ እንዳሉ ጠቁመው፤ በሳኡዲ መንግስት ጓዛችሁን ይዛችሁ እንዳትወጡ ተከልክላችኋል በመባላቸው፣ መጀመሪያውኑም ንብረት ይዘው ባለመምጣታቸው ነው፤ ብለዋል፡፡ እነዚህ ዜጎች ከመደበኛ የአየር መንገዱ ተጓዦች እኩል እንደማይስተናገዱና ለብቻቸው ተጠብቀው እንደሚስተናገዱ ገልፀው፤ ምናልባት ከነዚህ ዜጎች ጋር ተቀላቅለው የሚመጡ ሌሎች ሰዎች ስለሚኖሩ እሱን ለማጣራት ንብረታቸው ይፈተሻል እንጂ ማንም የእነሱን ንብረት የሚወስድ እንደሌለ የተናገሩት አምባሳደሩ፤ እንኳን በሀገር ውስጥ የገባ ንብረት፣ ሳዑዲ ያለውንም የላባቸውን ውጤት ለማስመጣት እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡
የሟቾችን ቁጥር እና ለቤተሰቦቻቸው መርዶ አለመንገርን በተመለከተ አምባሳደሩ በሰጡት ምላሽ፣ አሁን ሙሉ በሙሉ ትኩረታችን በህይወት ያሉ፣ ንብረታቸውን ያጡ እና ጉዳት የደረሰባቸው ላይ ነው፤ ብለዋል፡፡ የሟቾቹን ቁጥር በተመለከተ ግን መንግስት ከገለፀው በኋላ፣ የተፈጠሩ ነገሮች መኖራቸውን አምነው፤ ነገር ግን ቁጥሩ ላይ ተመላሾች የሚሉትና አንዳንድ ሚዲያዎች የሚያወሩት ትክክል ሊሆን ቢችልም የተጣራ ነገር እስካላገኘን ድረስ የሞቱበትን ሁኔታ ለማወቅ ያስቸግራል፤ ብለዋል፡፡ የሳውዲ አየር መንገድ እንጂ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመመለሱ ሂደት ምንም አስተዋፅአ ለስደተኞቹ አላደረገም ለተባለው አምባሳደሩ መልስ ሲሰጡ፡- የሳውዲ አውሮፕላን የሚያመላልሰው እራሱ በማባረሩ ምክንያት ነው፤ ወጪውን የሚችለውም እራሱ ነው ብለዋል፡፡