Tuesday 3 February 2015

አይዟችሁ ወረዱ… ምንም አይላችሁም… ወረዱ…. ኧረ… ውረዱ… – አቤ ቶኮቻው

ባቡሩ… የሚያገናኝ ነው የሚያለያይ!
10362622_883898291654914_6274989687573869809_nድሮ ድሮ ድልድይ በሌለባቸው የገጠር አካባቢዎች በክረምት ሰዎች እርስ በርስ ለመገናኘት ዙሪያ ጥምጥም ይዞሩ ነበር። የአንድ ቀኑን መንገድ ውሃ ሙላት በሚሆንበት የክረምት ወቅት ሶስት እና አራት ቀን ይፈጅባቸዋል።
አሁን በመሃል አዲሳባ ማዶ ለማዶ ሆነው ቡና ይጣጡ የነበሩ ሰዎች ባቡሩ አቆራርጧቸዋል። የተሰራልን ባቡሩ የከተማ ቀላል ባቡር /ትራም ሲሆን መንገዱ ደግሞ በምኒሊክ ዘመን የሚሰራው አይነት ለከባድ ባቡር የሚሆን ከከፍለ ሀገር ክፍለ ሀገር የሚያገናኘው ነው።
ለምሳሌ ያክል፤ እኔ በምኖርባት ማንችስተር ፕራም ወይም የከተማ ቀላል ባቡር ሲሄድ እንዳትጠጉኝ፤ ብሎ መንገድ አጥሮ ሰውን ከሰው አለያይቶ አይደለም።
10556307_883898258321584_6333053641612783708_nለማነጻጸሪያ ይሆን ዘንድ እነሆ የሁለቱም ቀላል ባቡር ሰዕሎች።
እኔ የምለው መሃንዲሱ አዲሳባዬን እንዲህ ግርድፍድፏን ከማውጣቱ በፊት ምናለበት ደውሎ ቢጠይቀኝ፤ ቢያንስ ቢያንስ ይቺን የማንችስተር ቀላል ባቡር ፎቶግራፍ አንስⶬ የማልከለት ሆኜ ነው! የምር ግን እንዲህ ሰፈርተኛውን ማዶ ለማዶ የሚያለያይ ባቡር ግንባታ ከመስራት በፊት ምናለበት የሌሎች ሀገሮችን ልምድ… ቀላል ባቡር አሁን ያለበት ቴክኖሎጂን ቃኘት ቃኘት ማድረግ ቢችሉ!
በመጨረሻም፤
ዛሬ ባለስልጣኖቹ በባቡሩ ላይ ተሳፍረው ሲመርቁ ስመለከታቸው ግን አንድ ነገር ጭንቅቅቅ አለኝ። ሰዎቹ ወራጅ ማለት ስለሚጨንቃቸው እዛው ባቡሩ ላይ ቁጭ በለው ይቀሩ ይሆን… ወይስ ደፍረው ወራጅ ይሉ ይሆን… እኔ የባቡሩ ሹፌር ወይም አስተናጋጁ ብሆን … ልክ ሲወረዱ… አይዟችሁ ወረዱ… ምንም አይላችሁም… ወረዱ…. ኧረ… ውረዱ… እያልኩ አበረታታቸው ነበር!
- See more at: http://satenaw.com/amharic/archives/4305#sthash.m8fdQ5mV.dpuf

ሰማያዊ ፓርቲ የምርጫ ቦርድ የፓርቲዎች ሚዲያ አጠቃቀም ድልድል ፍትሃዊ አለመሆኑን አስታወቀ

February 2, 2015
ሰማያዊ ፓርቲ የምርጫ ቦርድ ያወጣው ረቂቅ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ውድድር የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ሰዓት አጠቃቀም ድልድል ፍትሃዊና በእኩልነት ላይ የተመሰረተ አለመሆኑን አስታወቀ፡፡Ethiopia's Semayawi (Blue) party logo
ዛሬ ጥር 25 ቀን 2007 ዓ.ም የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሀገር አቀፍ ፓርቲዎችን በረቂቅ የሰዓት ድልድሉ ላይ ጊዮን ሆቴል ጋብዞ ውይይት አድርጓል፡፡ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢብኮ) ኃላፊዎች ረቂቁን ለውይይት ያቀረቡ ሲሆን፣ የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ እና ሌሎች ኃላፊዎችም በውይይቱ ተገኝተዋል፡፡
የኢብኮ ኃላፊዎች ባቀረቡት የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚዲያ አጠቃቀም ረቂቅ ድልድል መሰረት 55 ፐርሰንት በፓርላማ መቀመጫ ወንበር ላላቸው ፓርቲዎች፣ 20 ፐርሰንት ፓርቲዎቹ በሚያቀርቧቸው ዕጩዎች ብዛት እንዲሁም ቀሪ 25 ፐርሰንቱ ለሁሉም ፓርቲዎች በዕኩል የሚከፋፈል እንደሆነ ተገልጹዋል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲን በመወከል በውይይቱ ላይ የተገኙት የፓርቲው የህግ ጉዳይ ኃላፊ አቶ ይድነቃቸው ከበደ ለነገረ ኢትዮጵያ እንደገለጹት፣ ረቂቅ የሚዲያ አጠቃቀሙ ድልድል ሲወጣ እንደ መስፈርት የተጠቀሙባቸው ነጥቦች ችግር ያሉባቸው ናቸው፡፡
‹‹በእኛ እምነት መስፈርቱም ልክ አይደለም፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ የሚዲያ ሰዓት አጠቃቀም ድልድል ሲወጣ ሁለት መስፈርቶች በቂና ትክክለኛ ናቸው ብሎ ያምናል፡፡ እነዚህ ነጥቦች በሚቀርቡ እጩዎች ብዛት እና በእኩልነት የሚከፋፈል የድልድል መስፈርት መሆን አለባቸው›› ብለዋል አቶ ይድነቃቸው፡፡
በእርግጥ ረቂቁን ያቀረበው ኢብኮ እንደ መመዘኛ መስፈርት የተጠቀመው ‹‹እኩልነትና ፍትሃዊነት›› የሚሉ መርሆዎችን ነው፡፡ ‹‹ኢብኮ በቃላት ደረጃ የገለጻቸው ‹ፍትሃዊነትና እኩልነት› በተግባር ረቂቅ ድልድሉ ላይ አልታዩም፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ በእኩልነትና ፍትሃዊነት መርሆዎች ላይ ችግር የለበትም፡፡ መርሁን መሰረት አድርጎ ወጣ የተባለው የሚዲያ ድልድል መጠን ግን በትክክል መርሁን የተከተለ አይደለም፡፡ ስለሆነም ለውጥ ሊደረግበት ይገባል›› ብለዋል አቶ ይድነቃቸው፡፡
አቶ ይድነቃቸው የሰዓት አጠቃቀም ድልድሉ ላይ ስንወያይ ነጻ ሚዲያ በሌለበት፣ ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት በተገደበበት፣ ጋዜጠኞች በታሰሩበትና በተሰደዱበት፣ አማራጭ የሚዲያ ተቋማት በሌሉበት በዚህ አጣብቂኝ ወቅት ላይ በህዝብ ሀብት በሚተዳደሩ ሚዲያዎች ላይ የፍትሃዊነት ችግር ይዘን መወያያታችን አሳዛኝ ነው ብለዋል፡፡ ‹‹ሳንሱር በህገ-መንግስቱ ተነስቷል፤ ይሁን እንጂ ኢብኮ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተለያዩ ጊዜያት ለህዝብ የሚያስተላልፏቸው አማራጭ ሀሳቦችና ፖሊሲዎቻቸውን በቆርጦ ቀጥል ሲያዛባ እናስተውላለን፤ ይህ ሁኔታ መወገድ ያለበት ነው፡፡››
በውይይቱ ላይ ኢህአዴግ የድልድሉ መስፈርት ላይ እንደሚስማማ በመግለጽ፣ በፐርሰንቱ የተቀመጠው መጠን ላይ ግን መሻሻል እንዲደረግ እንደሚፈልግ መግለጹ ታውቋል፡፡