Thursday 26 December 2013

የፍርሃት ባህልን እያነገሰ ያለው የኢትዮጵያ ፖለቲካ አንድ እርምጃ ወደፊት ሁለት ወደ ኋላ

ክፍል አንድ
ፍርሃት የግለሰቦች ባህሪ መገለጫ ስለሆነ በማኅበረሰብ ደረጃ የሚኖረውን ገጽታ እና ትርጓሜ ማስቀመጥ ያስቸግራል። አንዱ ሰው የሚፈራውን ነገር ሌላው ላይፈራው ስለሚችል ፍርሃት እንደ የግለሰቡ ባህሪ እና ጥንካሬ ወይም ስነ-ልቦናዊ ሁኔታ የተለያየ መልክ ይኖረዋል። ይሁንና በአንድ ማኅበረሰብ ውስጥ የሚገኙ ሰዎች የሚጋሩት ባህልና ስነ-ልቦናዊ ሁኔታ እንደመኖሩ ሁሉ የሚጋሩትም ፍርሃት ወይም ደስታ ወይም ሃዘን ወይም ድፍረት ወይም ሌሎች ባህሪያት ይኖራል። በዚህም ምክንያት አንዳንድ ሰዋዊ ባህሪያት ለአንድ ማህበረሰብ ወይም ለበርካታ ሰዎች የወል መገለጫ ተደርጎ ሲገለጽ ይስተዋላል። ‘የዚህ አካባቢ ሰዎች ጀግኖች ወይም ጸብ ፈሪዎች ወይም እሩህ ሩህዎች ወይም ጨካኞች ወይም ቂመኞች ወይም ገራገሮች ወይም ተንኮለኖች ወይም ጎጠኞች ወይም ሌላ ባህሪ ያላቸው ናቸው’ የሚል አገላለጽ የተለመደ ነው። ይህ አይነቱ አነጋገር ሳይንሳዊ መሰረት ያለው ባይሆንም በአካባቢው ላይ ጎላ ብለው በሚታዩ ሰዎች ላይ ተደጋግሞና ተዘውትረው የሚታዩ ተመሳሳይ ባህሪያት የአካባቢው ሰው ሁሉ መገለጫ ተደርገው ስለሚወሰዱ ድምዳሜው ለስህተት የተጋለጠ ሊሆን እንደሚችል ከወዲሁ ለመግለጽ እወዳለሁ። ከዚህ መንደርደሪያ በመነሳት በዚህ ጥልቅ ጥናት ባላካሄድኩበት ነገር ግን ደጋግሜ ሳብሰለስለው በቆየሁት የፍርሃት ባህል እና በኢትዮጵያ የፖለቲካ ድባብ ዙሪያ ያለኝን ምልከታ ለአንባቢያን ለማካፈልና በጉዳዩም ላይ ለመወያየት ወሰንኩ።
በአንድ ማኅበረሰብ ውስጥ የፍርሃት ድባብ እንዲሰፍን እና ከዚያም አልፎ ባህል እንዲሆን ምክንያት ከሆኑት በርካታ ነገሮች መካከል የተወሰኑትን ልጥቀስና በእኛ ማኅበረሰብ ውስጥ ያላቸውን ገጽታ በመጠኑ ለመዳሰስ እሞክራለሁ። በስነ-ልቦና ጠበብቶች ከሚጠቀሱት ዋና ዋና የፍርሃት ምንጮች መካከል፤ ነፃነትን ማጣት፣ ነገ የሚሆነውን ማወቅ አለመቻል፣ የህሊና እና የአካል ቁስልን ባስከተሉ ትላንቶች ውስጥ ማለፍ፣ የማያቋርጥ ብስጭት ወይም ንዴት፣ ድህነት በሚያስከትለው ስቃይ ውስጥ መማቀቅ፣ አጋር እና አለኝታ ማጣት፣ በሌሎች ክፉኛ መነቀፍ፣ መንጓጠጥ፣ መጠላት እና መገለል፣ በሚኖሩበት ማኅበረሰብ ዘንድ ተቀባይነትን ማጣት፣ የሞት አደጋን ማሰብ፣ ሽንፈት ወይም ስኬት አልባ ሆኖ መቆየት፣ እና ሌሎችም ይገኙበታል። ከእነኝህ መክንያቶች ውስጥ የአንዱ መከሰት አንድን ሰው ወደ ፍርሃት ውስጥ ሊከት እንደሚችል ጥናቶች ይጠቁማሉ። እነኝህ ምክንያቶች ተደራርበውና በአንድ ጊዜ በአንድ ሰው ወይም በአንድ ማኅበረሰብ አባላት ላይ ሲከሰቱና ዕልባት ሳያገኙ እረዘም ላለ ጊዜ ሲቆዩ ደግሞ አደጋቸው የከፋ ነው የሚሆነው። ከዚህም በመነሳት ወደ እኛ ማህበረሰ ስንመለስ በግላችንም ሆነ በጋራ ህይወታችን ከላይ ከተጠቀሱት የፍርሃት መንሰዔዎች መካከል ስንቶቹ በህይወታችን ውስጥ ተከስተዋል፣ ስንቶቹን በአሸናፊነት አለፍናቸዋል፣ ስንቶቹስ ዛሬም ድረስ አብረውን ይኖራሉ፤ የሚሊቱን ጥያቄዎች እያንዳንዱ ሰው እራሱን እንዲጠይቅ እየተውኩ በወል በምንጋራቸው ጥቂት የፍርሃት መንሰዔዎች ላይ ላተኩር።
የነፃነት ማጣት
ሰብአዊ መብቶች በገፍ በሚጣሱበት እና ዜጎች የሰውነት ክብራቸው ተገፎ፣ ተዋርደውና ነፃነታቸውን ተነጥቀው በሚኖሩበት አገር ሁሉ ፍርሃት ትልቁ ገዢ ኃይል ነው። በእንዲህ ያለው ማህበረሰብ ውስጥ የፍርሃት ሰለባ የሆኑት እና ነፃነት አልባ ሕይወትን የሚገፉት ተጨቋኞቹ ብቻ ሳይሆኑ ጨቋኞቹም ጭምር ናቸው። ተጨቋኖቹ በግፍ ልንገደል፣ ልንታሰር፣ የስቃይ ሰለባ ልንሆን፣ ታፍነን ልንሰወር፣ ከሃገር ልንሰደድ፣ ከሥራ ልንባረር፣ ንብረታችን ሊወረስ፣ በግዞት ከቦታ ቦታ ልንዛወር፣ ከቅያችን ልንፈናቀል፣ በሃሰት ክስ ልንወነጀል፣ ደሞዛችንን ልንነጠቅ፣ ከሥራ ደረጃችን ልንቀነስ፣ ወዘት … እያሉ አደጋዎችን እያሰቡ በሽብርና በፍርሃት ቆፈን ተይዘው ‘ጎመን በጤና’ በሚል የማፈግፈጊያ ስልት መብቶቻቸውን አሳልፈው በመስጠት የግፍ እንቆቋቸውን እየተጎነጩ መራራ ሕይወታቸውን ይመራሉ። ጨቋኞቹም ይህን በነፍጥ እና በሕግ አንበርክከው ነፃነቱን የነጠቁትና ለስቃይ የዳረጉት ሕዝብ በአንድ አይነት ተአምር በቁጣ ገንፍሎ ከተነሳ አንድም ቀን እንደማያሳድራቸው ጠንቅቀው ስለሚያውቁ እያንዳንዱን ደቂቃና ሰዓታት ልክ እንደ ተጨቋኙ በፍርሃት እና በሽብር ነው የሚያሳልፉት። ከቦታ ቦታ ሲንቀሳቀሱም፣ የእለት ሥራቸውንም ሲያከናውኑ፣ ሲተኙም ሆነ ሲዝናኑ በሠራዊትና በመሣሪያዎች ጋጋታ ታጅበው ነው። ምናልባትም ከተጨቋኞቹም በባሰ ፍርሃት ውስጥ ነው የሚኖሩት።
ዛሬ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ሁኔታ በቅጡ ያጤንን እንደሆነ ገዢና ተገዢ እርስ በእርስ የሚፈራሩበት፤ መንግሥት ተቃዋሚ ፓርቲዎችን፣ ተቃዋሚዎች መንግሥትን የሚፈሩበትና አንዱ ሌላውን የማያምንበት ሁኔታ ነው የተፈጠረው። የመንግሥት ፍርሃት ከተቀናቃኝ የፖለቲካ ኃይሎች አልፎ የሲቪክ ማኅበረሰቡን፣ የሙያ ማኅበራትን፣ ነጋዴውን፣ ምሁራኑን፣ ገበሬውን፣ ወጣቱን እና ሌላውንም የኅብረተሰብ ክፍል ክፉኛ የሚፈራበትና በቁራኛ የሚከታተልበት፤ እነሱም መንግስትን እንደ ተናካሽ አውሬ የሚፈሩበት ሁኔታ ተፈጥሯል። በመንግሥትና በሕዝቡ፣ በተቃዋሚ ፓርቲዎችና በመንግሥት፣ በሕዝቡና በተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል ካለመተማመን የመነጨው ይህ ጥልቅ ፍርሃት በአገሪቱ የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካ እና ማኅበራዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ጥቁር ደመናን ጋርዷል። በገዢው ኃይል በኩል ያለውን የፍርሃት ድባብ ለመመልከት በየጊዜው መንግሥት የሚወስዳቸውን የኃይል እርምጃዎች፣ የሚያወጣቸውን የማፈኛ ሕጎች፣ እያጠናከረ የሄደውን የሥለላና የአፈና መዋቅር፣ በመገናኛ ብዙሃን የሚያሰራጫቸውን ሕግን ያልተከተሉ እና በሽብር መንፈስ የተዋጡ መግለጫና ዘገባዎችን መመልከት በቂ ነው። በተለይም የ1997ቱን ምርጫ ተከትሎ የተቀሰቀሰው የሕዝብ ቁጣ ያስደነበረው የወያኔ መንግሥት ከላይ የጠቀስኳቸውን እና አጥብቆ የሚፈራቸውን የኅብረተሰብ ክፍሎች ቀፍድዶ ለመያዝና እንቅስቃሴዎቻቸውን ለመገደብ ባወጣቸው የጸረ-ሽብር፣ የሲቪክ እና የበጎ አድራጎት ድርጅቶች መተዳደሪያ፣ የፕሬስ እና የፖለቲካ ፓርቲዎችን ምዝገባ፣ የፀረ-ሙስና እና ሌሎች አዋጆች ሥርዓቱ የአፈና  እና የመብት እረገጣ ተግባሩን ሕጋዊ ወደማድረግ ሂደት የተሸጋገረ መሆኑን ያሳያሉ። ፍጹም ሰላማዊ እና ሕጋዊ በሆነ መልኩ የመብት ጥያቄዎችን ባነሱ ዜጎች ላይ፤ አቅመ ደካሞችን እንኳን ሳይለይ ‘የፈሪ በትሩን’ ሲያሳርፍ በተደጋጋሚ ተስተውሏል።
ባለፉት ሃያ አመታት የአገዛዝ ሥርዓቱ የፈሪ በትሩን በተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ላይ አሳርፏል። ብዕርና ወረቀት በያዙ ከከፍተኛ ደረጃ ተማሪዎች እስከ አንደኛ ደረጃ ትመህርት ቤት ሕፃናት ጋር ሳይቀር በተደጋጋሚ ጊዜያት ተላትሟል። በርካቶችን ገድሏል፣ አስሮ አሰቃይቷል፣ ደብድቧል፣ ከትምህርት ገበታቸው ላይ አፈናቅሏል፣ ከአገር አሰድዷል፣ በሃሰት ወንጅሎ አስፈርዷል። በእምነት ቤቶች ውስጥ ገብቶ ከአማኞች፣ ከመንፈሳዊ አባቶች እና ይህን አለም ሸሽተው በገዳም ከከተሙ መነኮሳት ጋር ሳይቀር ተላትሟል። የኃይማኖት ተቋማት እንዲከፋፈሉና በገዢው ፓርቲ የፖለቲካ ተሿሚዎች ቁጥጥር ስር እንዲወድቁ ተደርገዋል። ምእመናን በመስጊዶችና በቤተክርስቲያን ውስጥ እያሉ በታጠቁ ኃይሎች ተገድለዋል፣ ተደብድበዋል፣ ተዋርደዋል። ቀሳውስት ጥምጥማቸውን እንዲያወልቁ እና መስቀላቸውን እንዲጥሉ ተደርጎ በማጎሪያ ካምፖች ውስጥ የማሰቃየት ተግባር ተፈጽሞቻቸውል። ኢማሞች ጺማቸው እየተጎተተ ተወስደው ተደብድበዋል፣ ታስረዋል። ይህ ሕዝብን የማዋረድ እና የማሸበር ተግባር የመነጨው እንደ እኔ እምነት የገዢው ኃይል እየተባባሰበት ከመጣው የፍርሃት እና የመሸበር ስሜት የተነሳ በራስ የመተማመን ስሜቱ እየተቦረቦረ በመሄዱ ነው። ዛሬ ሥርዓቱ የገዛ ጥላውንም የሚፈራበት፣ አባላቱ ላይ እንኳን እምነት ያጣበት ደረጃ ላይ ደርሷል። ለእዚህም አንዱ ማሳያው በነጋ በጠባ ቁጥር ማቆሚያ በሌለው የግምገማ ስብሰባ አባላቱን ሲያስጨንቅ መታየቱ እና ለዚሁ የሚያባክነው ጌዜ እና የሕዝብ ገንዘብ፣ የባለሥልጣናት ተደጋጋሚ  ሹም ሽር እና ከአገር ከድተው የሚወጡ ባለሥልጣናት እና የወያኔ አባላት ቁጥር መጨመሩ ነው።
ይህ የገዢው ኃይል የሕግን ልጓም በመበጣጠስ የፈረጠመ ክንዱን ይቀናቀኑኛል ባላቸው ግለሰቦች፣ ጋዜጠኞች፣ የፖለቲካ ኃይሎችና የሙያ ማኅበራትና አባላቶቻቸው ላይ ሁሉ ማሳረፉ ቀሪውን የኅብረተሰብ ክፍል ክፉኛ እንዲደነብርና በፍርሃት ቆፈን እንዲሸማቀቅ አድርጎታል። ዛሬ ኢትዮጵያ ውስጥ የሰብአዊ መብቶች መከበር፣ የዴሞክራሲ ጥያቄዎች እና የሕግ የበላይነት መረጋገጥ የሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍል የዕለት ተዕለት ሕይወት የሚነካ ቢሆንም የጥቂቶች ጉዳይ ተደርጎ ተወስዷል። በእነዚህ ጉዳዮች ላይ ጥቂት የሲቪክ ማኅበራት፣ ጥቂት ጋዜጠኞች፣ የተቃዋሚ ፓርቲዎች እና በጠአት የሚቆጠሩ ግለሰቦ ብቻ ናቸው ባላቸው ውሱን ጉልበት እና አቅም ሲወያዩ፣ የምንግሥትን መጥፎ ተግባራት ሲቃወሙ፣ ለዜጎች መብት ሲሟገቱ እና ባደባባይ ሲጮሁ የሚስተዋለው።
በድህነት አረንቋ ውስጥ ተዘፍቆ መቆየት
ሌላው እና ትልቁ የፍርሃት ምንጭ በከፋ ድህነት ውስጥ ለረዥም ጊዜ እየማቀቁ መቆየት እና ድህነቱ ባስከተለው የስቃይ ህይወት አካላዊና መንፈሳው አቅም ተሸርሽሮ ክፉኛ መጎዳት እና መዳከም ነው። ሕዝብን በድህነት ውስጥ አምቆ በማቆየት ለሰው ልጅ ከሚገባው ክብር ወርዶና ከእንስሳ ያልተሻለ ሕይወት እንዲኖር በማድረግ ቅስሙን መስበር የአምባገነኖች አንዱ የሥልጣን እድሜአቸውን ማራዘሚያ ሥልት ነው። የድህነት ክፋቱ ኪስን ብቻ ሳይሆን የሚያራቁተው ክብርንም ጭምር ነው። አንድ ሰው በመንገድ ላይ ቆሞና እራሱን ከመጽዋቾቹ ሥር ዝቅ አድርጎ ቁራሽ ምግብ ወይም ቤሳ ሲለምንና ሲማጸን በኩራትና በደስታ ስሜት ውስጥ ሆኖ አይደለም። እያፈረ እና እየተሸማቀቀ በተሸናፊነትና በዝቅተኝነት ስሜት ውስጥ ሆኖ ነው። ይህ ክስተት በሙሉ ጤንነት እና በወጣትነት ወይም በጉልምስና እድሜ ላይ ባሉ ሰዎች ውስጥ ሲሆን ደግሞ ያለው የውስጥ ሕመም እና የሕሊና ቁስል እጅግ የከፋ ነው። የድህነት ክፋቱ ያፈሩትን ቅሪት ብቻ ሳይሆን የሚያሳጣው ወይም ኑሮን ለማሸነፍ የሚያስችል አቅምን ብቻ ሳይሆን የሚሸረሽረው መንፋሳዊ ወኔንም ጭምር ነው ከላያችን ገፎ የሚወስደው። ከሰውነት ደረጃ ላይ የሚያቆመንን መንፈሳዊ ልዕልና ካጣን በኋላ ቁሳዊ ድህነቱን ብናሸንፈው እንኳን መንፈሳዊ ድህነቱ ይከተለናል። እዚህ ላይ ለማሳሰብ የምወደው ነገር ድሃ ሁሉ ፈሪ ነው ወይም በፍርሃት ቆፈን የተተበተበ ነው የሚል የተሳሳተ ግንዛቤ እንዳይወሰድ ነው። በከፋ የኢኮኖሚ ድህነት ውስጥ እየኖሩ ክብራቸውን አስጠብቀውና እና በላቀ የመንፈሳዊ ወኔያቸው እራሳቸውንና አገራቸውን አስከብረው ያለፉ ድሃ አያት ቅድመ አያቶቻችንን ማሰብ የግድ ይላል። ዛሬም የገንዘብ እጦትና ድህነት ያላላሸዋቸውና መንፈሳዊ ልዕልናቸውን አስጠብቀው በክብር የሚሞቱ ወገኖች አሉን፤ ትቂቶች ቢሆኑም።
የዚህ ጽሁፍ ትኩረት ግን በቁሳዊውም ሆነ በመንፈሳዊ  ማንነታቸው ውስጥ ድህነትና ፍርሃት ተረባርበው ወይም ከሁለቱ በአንዱ ተጠልፈው ስብእናቸው ፈተና ውስጥ የወደቀባቸውን ሰዎች የሚመለከት ነው። በተለይም በዚህ ግለኝነት በነገሠበት እና ገንዘብ በሚመለክበት የአለም ወቅታዊ  ሁኔታ ውስጥ መናጢ ድሃ ሆኖ ለዘመናት መቆየት መዘዙ ብዙ ነው። ብዙዎች ከዚህ መቋጫው ከጠፋው የድህነት አረንቋ ለማምለጥ ስደትን አማራጭ አድርገው በተለያዩ አቅጣጫዎች አገሪቷን ለቀው ለአረብ አገራት ባርነት ተሰደዋል። ቀሪዎች ደግሞ የአገዛዝ ሥርዓቱ ሎሌ በመሆን ነፃነታቸው በቤሳ መሸቀጥን ቀጥለዋል። ለሁለቱም እድሉን ያጡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ድሆች ደግሞ በየጎዳናው ላይ ተበትነው ዝናብ፣ ውርጭና ፀሃይ እየተፈራረቁባቸው የመጽዋቾቻቸው ደጅ ጠኞች ሆነዋል።
ከተወሰኑ አሥርት አመታት በፊት አንድ ሰው በድህነቱ ምክንያት እራሱንና ልጆቹ የትምህርት፣ የጤና አገልግሎት፣ መሰረታዊ የሆን አልባሳትና መጠለያ ጎጆ ባለቤት ለማድረግ የሚገጥመው ፈተና ቢኖርም ይህን ያህል የመረረ አልነበረም። ዜጎች በወር ከሁለት ብር አንስቶ እንደ የአቅማቸው የቀበሌ እና የኪራይ ቤቶችን ቤቶች ተከራይተው የመጠለያ ችግራቸውን ይቀርፉ ነበር። በአገሪቷ ውስጥ የነበሩ በርካታ የሕዝብ ትምህርት ቤቶች ከመመዝገቢያ ያልዘለለ አነስተኛ ገንዘብ እየተቀበሉ ተማሪዎችን በነጻ ያስተናግዱ ነበር። ብዙ ምሁራንንም አፍርተዋል። በየቀበሌው ከተደራጁ ጤና ጣቢያዎች አንስቶ በተለያዩ የመንግሥት ሆስፒታሎች ዜጎች በነፃና እጅግ ተመጣታኝ በሆነ ክፍያ ጥሩ ሕክምና የማግኘት እድል ነበራቸው። በአንድ ብር በሚገዛው አስር ትንንሽ ዳቦ ወላጆች ልጆቻቸውን አብልተው ያሳድሩ ነበር። ዛሬ አገሪቱ በልማት እየገስገሰች እንደሆነ በሚነገርበት በዚህ ወቅት ዜጎች በኑሮ ውድነትና ዋስትና ማጣት በጨለማ  ህይወት ውስጥ እየተደናበሩ ይገኛሉ።
መንግሥት በኢኮኖሚውም፣ በፖለቲካውም ሆነ በሌሎች ኃይማኖታዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች ያሻውን ቢያደርግ  በሕዝብ በኩል መላሹ ዝምታ ሆኗል። አብዛኛው ሕዝብ ከተዘፈቀበት የድህነት አረንቋ ሳይወጣ በርካታ ነገሮች ተቀይረዋል። በመቶና በሁለት መቶ ይገዛ የነበር ጤፍ በሺዎች ሲያወጣ ምላሹ ዝምታ ሆኗል። ቲማቲም እንኳን ባቅሟ በኪሎ ከሁለት ብር ወደ ሃያ ብር ስትጠጋ አንዳንዴም ስትዘል ዝምታ፣ የቤት ኪራይ ከመቶዎች ወደ ሺዎች ሲንር ዝምታ፣ የነዳጅ ዋጋ በየጊዜው ሲያሻቅብ ዝምታ፣ የመብራት፣ የውሃ፣ የስልክ እና የኢንተርኔት አገልግሎቶች በሰአታት፣ ከዚያም ለቀናት አንዳንዴም በተወሰኑ ቦታዎች ለሳምንታት ሲጠፉ ዝምታ፣ መነኮሳት እና አድባራት ሲዘረፉና ሲዋረዱ ዝምታ፣ መስጊዶች እና ኢማሞች ሲዋክቡና ሲታሰሩ ዝምታ፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞች እና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ሲደበደቡ፣ ሲታሰሩና ሲሳደዱ ዝምታ፣ የንግዱ ማኅበረሰቡ ሲዋክብና ሲጉላላ ዝምታ፣ ገበሬዎች በማዳበሪያ እዳ ንብረታቸውን ሲነጠቁና ከዛም አልፎ ከትውልድ ትውልድ ያቆዩትን ይዞታቸውን እየተነጠቀ ለውጪ ቱጃሮች ሲቸበቸብ ዝምታ፣ ወንዶች ሚስቶቻቸውና ሴት ልጆቻቸው እፊታቸው ሲደፈሩና ሲጠቁ እያዩ ዝምታ፣ እናቶች ልጆቻቸውና ባሎቻቸው በየወጡበት ሲቀሩ እያዩ ዝምታ፣ በየከተማው የሚገኙ ነዋሪዎች ቤታቸ በላያቸው ላይ እንዲፈርስ እየተደረገ ከነልጆቻቸ በየሜዳው ተበትነው ይዞታቸው ለስግብግብ ባለሃብቶች ሲሰጥ ዝምታ፣ የሙያ ማኅበራት ሲጠቁ ዝምታ፣ መምህራኖች ሲዋከቡ ዝምታ፣ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ሠራተኞች ከሥራ ገበታቸው ‘በድህነት ቅነሳ እስትራቴጂ’ ስም ሲፈናቀሉና ለርሃብ ሲዳረጉ ዝምታ፣ ባለሥልጣናት የከፋ ሙስና ውስጥ ተዘፍቀው ሲንቦጫረቁ ዝምታ፣ ሕፃናት ሳይቀሩ በየአደባባዩ ግንባራቸው በጥይት እየተቦደሰ ሲረሸኑ ዝምታ፣ የአገሪቷ የትምህርት ሥርዓት ክፉኛ አቆልቁሎ ትውልድን ወደማክሰም ደረጃ ላይ ሲደርስ እየተመለከትን ዝምታ፣ መንግሥት ድህነትን ሸሽተው ከሃገር የሚሰደዱ ወጣቶችን መንገዱን ጨርቅ ያድርግላችው እያለና ገንዘብ እየቃረመ ለዘመናዊው ባርነት እያዘጋጀ ፓስፖርት ሰጥቶ ሲያሰድድ ዝምታ፣ በየጎዳናው የወደቁ  ሕፃናቶችን በጉዲፈቻ ስም መንግስት ለውጪ ዜጎች በብዙ ሺ ዶላር ሲቸበችብ እያየን ዝም፣ መንግስት የራሱን ሕገ-መንግስት እየናደ የፈቀደውን ሁሉ በዜጎች ላይ ሲፈጽም የህዝብ ምላሽ ዝምታ፣ ዝምታ፣ ዝምታ…..። ስንቱ ተጠቅሶ ይቻላል?
አንድ ሕዝብ ይህ ሁሉ ውርጅብኝ ያለፋታ ሲዥጎደጎድበት እና መገለጫ የሌልውን ግፍ እና ጭቆና በጫንቃው ላይ ሲጫንበት ውስጥ ውስጡን እያጉረመረመ፣ እያለቀሰና ልቡ እየደማ እንዴት ነህ ሲሉት ደህንነቱን ለመግለጽ ‘እግዚያብሄር/ አላህ ይመስገን’ እያለ የውሸት ሳቅ እየሳቀ እንዲኖር ያስገደደው ምንድን ነው? መንፈሱና አካሉ በቁሙ ተሸርሽረው እያለቁ ባልሞትኩም ባይነት የአያቶቹን ገድል በህሊናው እያመነዥከ በዘመኑ ለተጋረጡበት ፈተናዎች፤ በተለይም ድህነት፣ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ጭቆዎችና በገዛ አገሩ ተዋርዶ መኖርን ለመሸሽ ስደትን ወይም ልመናን ወይም ሕሊናን ቀብሮ ለሥርዓቱ አገልጋይ መሆንን ከማን ተማረ? ይህ ጥልቅ የሆነው ዝምታችን የፍርሃት? ወይስ የትእግስት? ወይስ በፍርሃትና በትእግስተኛነት መካከል ሌላ ደሴት ወይም መንጠልጠያ ስፍራ አለ? እራሳችንን እንጠይቅ!
(ክፍል ሁለት)onetwo
የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሂደት በኢትዮጵያዊያን ላይ እያሰፈነ ስላለው የፍርሃት ባህል ቀደም ሲል ባሰራጨሁት የዚህ ጽሑፍ የመጀመሪያ ክፍል ውስጥ ባለሙያዎች በአንድ ማኅበረሰብ ውስጥ ለፍርሃት ባህል መስፈን መንሰዔዎች ያሏቸውን ነጥቦች ዘርዝሬ ነበር። በክፍል አንድ ጽሑፌ መግቢያ ላይ እንደገለጽኩት ምንም እንኳን ፍርሃት የግለሰቦች ባህሪ መገለጫዎች መካከል አንዱ ቢሆንም የዚህ ጽሑፍ ትኩረት በወል የምንጋራቸውና በማኅበረሰብ ደረጃም በሚንጸባረቁት የፍርሃት ምልክቶች ላይ ብቻ ያተኮረ ነው። በመሆኑም በዚህ ክፍል ውስጥ የህሊና እና የአካል ቁስልን ባስከተሉ ትላንቶች ውስጥ ማለፍ የሚፈጥረውን የፍርሃት ቆፈንና የሚያስከትለውን መዘዝ በመቃኘት ፅሑፌን ልደምድም።
በአለማችን ታሪክ ከሰው ልጅ አዕምሮ ተፍቀው የማይወጡና እጅግ አሰቃቂ በመሆናቸው ሲታወሱ የሚኖሩ በርካታ ጦርነቶችና የእርስ በርስ እልቂቶች ተከስተዋል። የመጀመሪያውና የሁለተኛው የአለም ጦርነቶች፣ የኦሽዊትዝ ጭፍጨፋ፣ የአፓርታይድ የግፍ አገዛዝ፣ የሩዋንዳው የዘር ማጥፋት እልቂት፣ እንዲሁም በተለያዩ የአፍሪቃ እና የመካከለኛው ምስራቅ አገራት ውስጥ የተከሰቱትና የሚሊዪኖችን ሕይወት የቀጠፉት እልቂቶች በዋነኝነት ተጠቃሾች ናቸው። እነኚህ በክፉ ክስተትነታቸው በታሪክ የሚወሱት አጋጣሚዎች ካስከተሉት እልቆ መሳፍርት የሌለው ሰብአዊ ቀውስ እና የንብረት ውድመት ባሻገር ከትውልድ ትውልድ የሚወራረስ ትምህርትንም አስተምረው አልፈዋል። በተለይም የምዕራቡ አለም በራሱም ሆነ በርቀት በሌሎች ላይም የተፈጸሙትን እነዚህን መሰል መጥፎ ክስተቶች በአግባቡ በመመርመር፣ መረጃዎችን ሰብስቦና አደራጅቶ በማስቀመጥ፣ በመጽሐፍ ከትቦና እና በፊልም ቀርጾ በማኖር ቀጣዩ ትውልድ እነኚህን መሰል አደጋዎችን ከሚያስከትሉ የፖለቲካ፣ የማኅበራዊ፣ ኃይማኖታዊና ኢኮኖሚያው ቀውሶችና ቅራኔዎች እራሱን በማራቅ ችግሮችን እጅግ በሰለጠነና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እንዲፈታ ማድረግ ችለዋል። ዛሬ ላይ ያለው ትውልዳቸውም እነ ናዚ እና ሌሎች አንባገነኖች በታሪካቸው ውስጥ ያደረሱትን ሰቆቃና ግፍ እያሰብ የሚሸማቀቅ ወይም በፍርሃት የሚርድ ሳይሆን ታሪክን በታሪክነቱ ትቶ ሙሉ አቅሙንና ጊዜውን ከሳይንስና ተክኖሎጂ ጋር አዋህዶ በዚህ ምድር ላይ ያሻውን ሁሉ ለማድረግ የሚያስችል አቅም በመገንባት ላይ ይገኛል።
ወደ አገራችን ስንመለስ ኢትዮጵያም ዛሬ ያለችበትን ጂዮግራፊያዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊም ሆነ ሌሎች ገጽታዎች ለመላበስ ያበቋት እጅግ በርካታ ክፉ እና በጎ ተበለው የሚጠቀሱ የታሪክ ክስተቶችን አስተናግዳለች። ምንም እንኳን ከላይ ከተጠቀሱት የአለማችን አሰቃቂ ታሪኮች ጋር ባይወዳደርም አገራችንም ከውጭ ወራሪዎች በተሰነዘረባት ጥቃትም ሆነ በልጆቿ መካከል በተከሰቱ የእርስ በእርስ ግጭቶች በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ውድ ልጆቿን አጥታለች። ድህነትን ጠራርጎ ሊያስወግድ ይችል ከነበረው አቅም በላይ በብዙ እጥፍ የሚገመት አንጡራ ሃብቷን በጦርነቶች፣ በግጭቶችና በዘራፊዎች ተነጥቃለች። ይህ እና ሌሎች በርካታ ምክንያቶችም ተደራርበው አገሪቱን ከድሃም ድሃ ተብለው ከሚጠቀሱት አገሮች ተርታ አሰልፈዋታል። እንግዲህ ትልቁ ጥያቄ እኛስ እንደ ሌላው ዓለም ሕዝብ አገራችን ካለፈችበት የረዥም ዘመን ታሪክ እና በየወቅቱ ከተከሰቱ መጥፎና በጎ የታሪክ ክስተቶች ምን ተማርን? ተምረንስ ለዛሬ እኛነታችን ምን አተረፍን? በአያቶቻችን እና በእኛ መካከል በኢኮኖሚ፣ በማኅበራዊ እና በፖለቲካ ተክለ አቋማችንም ሆነ አመለካከታችን ዙሪያ ለውጦች አሉ ወይ? ለውጣችን ቁልቁል ወይስ ካለፉት ወገኖቻችን የህይወት ተመክሮ ትምህርት ወስደን የደረስንበት የላቀ የአስተሳሰብና የኑሮ ደረጃ አለ? የታሪክ መዛግብቶቻችንስ ያለፉ ነገስታቶችን እና የጦር አበጋዞቻቸውን ከማወደስና ገድላቸውን ከመተረክ ባለፈ በቀጣዩ ትውልድ ሕይወት የጎላ ሚና ሊኖራቸ በሚችል መልኩ ተዘጋጅተዋል ወይ? ወይስ ‘እኔ የገሌ ዘር’ እያለ እንዲያዜምና በአያቶቹ ገድል እንዲያቅራራ ብቻ ተደርገው ነው የተዘከሩት? እንደ እኔ እምነት ከምዕራቡ አለም እኛንና ብዙዎች የአፍሪቃ አገራትን ከሚለዩን ነገሮች መካከል ጥቂቶቹ ከነዚህ ጥያቄዎች ምላሽ የሚመነጩ ይመስለኛል።
የዛሬ መቶ እና ሁለት መቶ አመት በፊት የተፈጠሩ የታሪክ ክስተቶችን ፍጹም በተዛባ መልኩ እያጣቀስን ልክ የእኛ የልፋት ውጤት አስመስለን እስኪያልበን የምንፎክርና የምንጨፍር እኛ ነን። ታሪክን እና ጀግኖችን ማወደስ ተገቢ ቢሆንም የኛን ድርሻ እነሱን በማወደስ ብቻ ስንገታው አደጋ ላይ ይጥለናል። እንደ አያቶቻችን ታሪክን መስራት ሲያቅተን ታሪክ ሰሪዎችን በማውሳትና በዜማና በግጥም ማወደስ ብቻ ብንኮፈስ የዛሬውን ማንነታችንን አይሸፍነውም። ይህ በአያቶቻችን ታሪክ ውስጥ ተደብቀን ‘በኢትዮጵያዊነቴ እኮራለሁ’ እያሉ ማዜም፣ መፎከር፣ ማቅራራትና ያዙኝ ልቀቁኝ ማለት ዛሬ ከተጣቡን የድህነት፣ የፖለቲካ ጭቆና እና ማኅበራዊ ቀውስ የማያስጥለን እና ነፃ የማያወጣን እሰከ ሆነ ድረስ ኩራታችን ከድንፋታ አያልፍም። አገሬን እወዳልሁ፣ በኢትዮጵያዊነቴ እኮራለሁ እያሉ ባንዲራ ለብሶ ማቅራራት በተግባር ካልታገዘ የውሸት ወይም ባዶ ኩራት (false pride) ነው የሚሆነው። እውነተኛ ኩራት የሚመነጨው ከራስ ነው፤ የራስን ማንነትን በማወቅና በመቀበል ላይ የሚመሰረት ነው። ማንነትን አምኖ መቀበል አቅማችንንም አብረን እንድፈትሽ ይረዳል። የዛሬ ባዶነታችንን በአያቶቻችን የታሪክ ገድል እንድንሞላ ወደሚያስገድድ የሞራል ክስረት ውስጥም እንዳንገባ ይረዳናል። የዛሬ ውርደታችንን በአድዋ ድል እና በሌሎች የአያቶቻችን ተጋድሎዎች በተገኙ ስኬቶችን ልንሸፍነው ከመጣር ይልቅ ታሪክ እንድንሰራ ብርታት ይሆነናል።
በሌላ በኩል የአውሮፓ ቅኝ ገዢዎች ያሳቀፉንን የዘረኝነት መርዝ እያራባን በታሪክ ተፈጽመዋል የተባሉ አንዳንድ ክስተቶችን እየመነዘርን ‘ያንተ ቅም ቅም አያትህ የእኔን ቅም ቅም አይታቶች በድሎ ነበር፤ ስለዚህ በቅም ቅም አያቶቼ ላይ ያንተ ዘሮች ላደረሱት በደል ኃላፊነቱን አንተ ትወስዳለህ እያልን ድርጊቱን ዛሬ ላይ እንደተፈጠረ በመቁጠር የምንጋጭና ለመነጣጠል እንቅልፍ አጥተን የምናድርም አለን። እራስን እንደተበዳይ ሌላውን የኅብረተሰብ ክፍል እንደ በዳይ በመቁጥርና የተዛባን ታሪክ በመተንተን ለዛሬው በዘረኝነት መርዝ ለተለወሰው የፖለቲካ አጀንዳቸው ማሳኪያነት ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ካፈር የሚለውሱ ኢትዮጵያዊያኖችም (እነሱ ኢትዮጵያዊ አይደለንም ቢሉም) ልብ ሊገዙ ይገባል። በአገሪቱ ውስጥ ያሉ የተለያዩ ጎሣዎች በገዛ አገራቸው እኩል መብትና ጥቅም እንዲረጋገጥላቸውና የሁሉም አገር እንድትሆን ከመጣር ይልቅ በዘረኝነት ስሜት ውስጥ ተወጥሮ ኢትዮጵያዊነትን መካድና ከራስ ጎሣ ውጭ ያለውን የኅብረተሰብ ክፍል እንደ ጠላት መቁጠር መዘዙ ብዙ ነው። ይህን ለመረዳት ብዙ ምርምር አያስፈልገውም። በቅርባችን ካለችው ከሩዋንዳ ትምህርት መውሰድ ይቻላል። ይህን የዘረኝነት እሳት እየተቀባበሉ የፖለቲካ መታገያቸው ያደረጉ ኃይሎችም ከዚህ እኩይ ተግባራቸው እንዲታቀቡ በስሙ የሚነግዱበት ሕዝብ ሊያወግዛቸው ይገባል።
እርቀን ሳንሄድ የቅርብ ጊዜ ታሪካችንን እንኳን ብንፈትሽ ዛሬ ለምንገኝባቸው እጅግ ውስብስብ እና ፈታኝ ችግሮች መንስዔ የሆኑትን ነገሮች በቀላሉ ልንገነዘብ እንችላለን። የችግሮቻችንን ምንጮች እና ያስከተሉብንን መዘዝ በቅጡ መረዳት ከቻልን ከተዘፈቅንበት አረንቋ ውስጥ ለመውጣት ጊዜ ላይወስድብ ይችላል። መወጣጫውም ላይርቀን ይችላል። ትልቁ ጥያቄ ችግሮቻችንን ከመዘርዘር ባለፈ ምንስዔዎቻቸውንም በቅጡ ተረድተነዋል ወይ? እንደ አንድ አገር ሕዝብ በችግሮቻችን እና በችግሮቹ ምንጭ ዙሪያ የጠራ የጋራ ግንዛቤ አለን ወይ? በፖለቲካ እና በሌሎች ማኅበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ስንደራጅስ ከነዚህ ግንዛቤዎች ተነስተን ነው ወይ? የጋራ የሆኑ ችግሮች ሰዎችን ያስባስባሉ፣ ለድርጅቶች መፈጠርም መንስዔ ይሆናሉ፣ ችግሮቹንም ለመቋቋም እና ለማስወገድ “ከአንድ ብርቱ …” እንደሚባለው ኃይልን ይፈጥራሉ። ይሁንና ስብስቡ ወይም የተደራጀው ኃይል ፊት ለፊት ከተጋረጡት ችግሮች ጋር ከመፋለም ባለፈ በድጋሚ እንዳይከሰቱ ምንጮቻቸውን ለማድረቅ የሚያስችል እይታ ከሌለው እና አቅሙንም በዚያ ደረጃ ካላሳደገ ይህ አይነቱ ማኅበረሰብ ሁሌም ለተመሳሳይ አደጋዎች የተጋለጥ ነው። የችግሩን መንሰዔ አጥንቶ ምንጩን ለማንጠፍ ከሚያወጣው ጉልበት፣ ገንዘብና ጊዜ የበለጠ አዳዲስ ችግሮች በተከሰቱ ቁጥር ከተኛበት እየባነነ ተነስቶ ችግሮቹን ለመቋቋም የሚያስችሉ ድርጅቶችን ለመፍጠርና ለማፍረስ የሚያወጣው ጊዜ፣ ገንዘብና ጉልበት እጅግ የላቀ ነው። በእንዲህ አይነት ማኅበረሰብ ውስጥ ጠንካራ የሆኑና ልምድ ያካበቱ ድርጅቶችን መፍጠር አይቻልም። ብዙዎቹ ድርጅቶች ሳይጎረምሱ፣ ሳይጎለምሱ እና ሳያረጁ በጨቅላነታቸው ይሞታሉ ወይም ደንዝዘው ስማቸውን ብቻ ይዘው ይቀራሉ። ይህ አይነቱ ማህበረሰብ አውራ የሚሆኑና በምሳሌነት ሊጠቀሱ የሚችሉም የፖለቲካ፣ የኃይማኖት እና የማኅበራዊ ህይወት መሪዎችን የመፍጠር አቅም የለውም፤ አይፈጥርምም፤ በራሳቸው ጥረት ቢፈጠሩም ጎልተው እንዲታዩ እድሉን አይሰጥም። ትላንት ያነገሳቸውን በማግስቱ አፈር ከድሜ ሲደባልቃቸው ምንም አመክንዮ አይፈልግም። ሲያከብርም፣ ሲሾምም፣ ሲያዋርድም ሆነ ሲኮንን በስሜት ነው። በተለይም እንደኛ በብዙ ውስብስብ ችግሮች ውስጥ ተተብትቦ ግራ ለተጋባ ማኅበረሰብ ልምድና በእውቀት የጎለበቱና የሕዝብ አመኔታን ያገኙ ባለ ዕራይ ድርጅቶችና ግለሰቦች መኖር እጅግ ወሳኝ ነው።
የፖለቲካም ሆነ ሌሎች ልዩነቶቻችንን የምንይዝበት መንገድ ሊፈተሽ ይገባዋል። የቀዝቃዛው የአለም ጦርነት ማብቂያን ተከትሎ የፈረሰውና ጀርመንን ለሁለት ከፍሏት የነበረው ግንብ ሲናድ ምስራቅና ምዕራቡን ወደ አንድ አገር ከመለወጥ ባለፈ መላው አውሮፓን አንድ ያደረገ ክስተትን ፈጥሯል። የሰብአዊ መብቶች እና የዲሞክራሲ ጽንሰ ሃሳቦች የልዩነት ማጦዣ ምክንያቶች ከመሆን ወጥተው ጀርመንን ብቻ ሳይሆን አውሮፓን ያዋሃዱ ተጨባጭ እውነታዎችን ፈጥረዋል። ይህን ተከትሎም ከታሪክ ለመማር ዝግጁ በሆኑ በበርካታ የአለማችን አገራት በመሬት የተገነቡም ሆነ በሰዎች አዕምሮ ውስጥ የተካቡ የልዩነት ግንቦች ሁሉ ፈርሰው ዜጎች ለጋራ ራዕይ በጋራ የመቆም ጽናትን አሳይተዋል። ሕዝባቸውንም ነጻ አውጥተዋል። ሌሎች እንደ ኢትዮጵያ ያሉ የተለያዩ አገሮች (አብላጫዎቹ የአፍሪቃ አገራት) የልዩነቶቻቸውን ግንቦች አጠንክረውና አዳዲስ ግንቦችን በአይምሯቸው ውስጥም ገንብተው የተሰበጣጠረና የሚፈራራ የኅብረተሰብ ክፍልን በመፍጠር ጉዞዋቸውን ቀጥለዋል። የጎሣ ግንቦች፣ የሥልጣን ግንቦች፣ የኃይማኖት ልዩነት ግንቦች፣ የድሃና የሃብታም ግንቦች፣ የጨቋንና የተጭቋኝ ግንቦች፣ ሌሎች ማኅበረሰቡን በአንድ ላይ እንዳይቆም እና ድህነትና አንባገነንነትን አሽቀንጥሮ እንዳይጥል አቅም የሚያሳጡ በርካታ የልዩነት ግንቦች ተገንብተዋል።
ድርጅቶችን እና መሪ የሚሆኑ ግለሰቦችን እየፈጠርንና መልሰን እየደፈጠጥን የመጣንበትን የ50 ዓመታት የፖለቲካ ጉዞ ወደ ኋላ መለስ ብለን ብንቃኝ ይህንን እውነታ ያረጋግጥልናል። ባለፉት 50 ዓመታት ውስጥ ለቁጥር የሚታክቱ የፖለቲካ፣ የሙያና በማኅበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ያተኮሩ ድርጅቶች ተፈጥረው ብዙዎች ካለሙበት ሳይደርሱ ከስመዋል። ጥቂቶችም ባልሞት ባይ ተጋዳይነት በመኖርና ባለመኖር መካከል ሆነው ቀጥለዋል። በከሰሙትም እግር ሌሎች በርካቶች ተተክተው በተመሳሳይ አዙሪት ውስጥ ወድቀው የኅብረተሰቡን ቀልብ ለመሳብ ደፋ ቀና ሲሉ ይስተዋላል። እዚህ ላይ ልብ ልንለው የሚገባው በዚህ ዘመን ውስጥ ብቅ ብለው በከሰሙትም፣ ተውተርትረው ቆይተው በተዳከሙትም፣ አዳዲስ ስም እየያዙ በተፈጠሩትም ድርጅቶች ውስጥ ዋነኛ ተዋናዮቹና የድርጅቶቹ ፈጣሪዎችም ሆኑ አጥፊዎቹ አንድ አይነት ሰዎች መሆናቸው ነው። ትላንት በአንድ ድርጅት ጥላ ስር ሆነው ሌሎችን እንደ ጠላት ይፈርጁ የነበሩ ሰዎች ዛሬ የብዙ ድርጅቶች ፈጣሪዎች ሆነዋል። ትላንት በጠላትነት የሚፈራረጁ ድርጅቶች አባል የነበሩ ሰዎች ቂማቸውን እንዳረገዙ ዛሬ በአንድ ድርጅት ጥላ ሥር የተሰባሰቡበትንም ሁኔታ እናያለን። በድርጅቶቹ መካከል እጅግ ጠባብ የሆኑ የርዕዮታለም ልዩነቶች ከመኖራቸው ውጭ አብዛኛዎቹ የመጨረሻ ግባቸው አንድ እና አንድ ነው። ዲሞክራሲ የሰፈነባት፣ የሕግ ልዕልና የተረጋገጠባት፣ ሰብአዊ መብቶች የተከበሩባት እና ድህነትን ያሸነፈች ኢትዮጵያን ማየት፣ መፍጠር ነው። በነዚህ መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ የሚለያዩ ድርጅቶች ያሉ አይመስለኝም፤ ሊኖርም አይችልም። ልዩነቱ እነዚህ ግቦች ላይ ለመድረስ ድርጅቶቹ በሚከተሉት አቅጣጫና መንገድ ቅየሳ ላይ ነው።
በዚህ የ50 ዓመት ጉዞ ውስጥ በሽብር መንፈስና በነውጥ ተግባራት የተሞላው የኢትዮጵያ ፖለቲካ በድርጅቶች መካከል እርስ በርስ አለመተማመንንና መካካድን ፈጥሯል። ይህም አለመግባባቶቹ ከጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት አልፈው እልቂትን አስከትለዋል። በዚያም የተነሳ አገሪቷ በፍርሃት እንድትዋጥና ሕዝቧም በስጋት እንዲኖር፤ የፍርሃት ባህልም እንዲጎለብት ከፍ ያለ ሚና ተጫውቷል። ዛሬ በእያንዳንዳችን አዕምሮ ውስጥ በርካታ የልዩነት ግንቦች ተፈጥረዋል። በፖለቲካ ፓርቲዎች፣ በሲቪክ ማኅበራት፣ በኃይማኖት ተቋማት፣ በማኅበረሰብ ድርጅቶች መካከልም የበርሊን ግንብ አይነት ግዙፍ የልዩነት ግንቦች ተፈጥረዋል። የዛሬዎቹ ኃይሎች ከገዢው ፓርቲ በስተቀር በትጥቅ የተደራጁ ስላልሆኑ ነው እንጂ ለመጠፋፋት ቅርብ ናቸው። ትልቁና እያንዳንዳችን እራሳችንን ልንጠይቅ የሚገባን፤ እነዚህን ግንቦች ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እንዴት ንደን እና በላያቸው ላይ ተረማምደን ልብ ለልብ እንዋሃዳልን? እንዴት እንደ አንድ ሕዝብ የጋራ ዕራይ፣ የጋራ መዝሙር፣ የጋራ ህልም፣ የጋራ መፈክር፣ የጋራ መድረክና የጋራ አገር እንፈጥራለን? እንዴት ከቂም፣ ከበቀልና ከቁርሾ ሽረን ከታይታና ከቧልት ፖለቲካ ወደ እውነተኛ የፖለቲካ ሕይወት እንመለሳለን?
ለማጠቃለል ያህል በእኔ እምነት ከተተበተብንበት ውስብስብ ችግሮችና ከተጫነን የፍርሃት ድባብ ለመላቀቅ፤ አልፎም ጤናማ የሆነ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና ማኅበራዊ ሥርዓት ባለቤት የሆነ ማኅበረሰብ ለመፍጠር የሚከተሉት ተግዳሮቶች ቢቀድሙ ይበጃል እላለሁ::
  • ዛሬ ለፖለቲካ ንትርክና  እርስ በርስ መፈራራት እንደ ምክንያት የሚነሱት የታሪካችን ክፍሎች ከፖለቲካ፣ ከኃይማኖት እና ከሌሎች ወገንተኝነት ነጻ በሆኑ ምሁራን በአግባቡ የሚጠኑበት ማዕከል ቢኖረን። የመወዛገቢያ ነጥብ የሆኑትም ታሪካዊ ኩነቶችን በአግባቡ ቢጠኑ እና በተለያዩ መንገዶችም ተደግፈው ለማስተማሪያነት ቢውሉ በድንቁርና ላይ ከተመሰረቱት ታሪክ ጠቀስ የሆኑና በጥላቻ መንፈስ የተሞሉ ክርክሮች ወጥተን እውቀትን በዋጁ ውይይቶች ላይ እናተኩራልን።
  • የሩቁን ለታሪክ ምሁራን እንተወና ባለፉት አምሣ ዓመታት ከ1960 ዎቹ የተማሪዎች ንቅናቄ ጀምሮ በፖለቲካ ትግል ውስጥ ዋነኛ ተዋናይ የሆኑ ኃይሎች ዛሬም በአገሪቷ የለት ተዕለት የፖለቲካ ህይወት ውስጥ በግራና በቀኝ ሆነው እና በመቶ ድርጅቶች ጉያ ውስጥ መሽገው በአገሪቷና በድሃው ሕዝብ እጣፈንታ ላይ ወሳኞች ሆነው ቀጥለዋል። በተለይም ‘ያ ትውልድ’ በሚል የሚታወቀው የኅብረተሰብ ክፍል ከልጅነት እስከ አዋቂነት ክቡር ሕይወቱን፣ ጊዜውን፣ ገንዘቡን እና እውቀቱን ያለምንም ስስት የዛችን አገር እጣ ፈንታ ለማቅናት መስዋዕትነት ሲከፍል ቆይቷል፤ ዛሬም ዋነኛ ተዋናይና አድራጊ ፈጣሪ ሆኖ ቀጥሏል። ይህ ትውልድ ትላንትናም ሆነ ዛሬ በገዢና በነጻ አውጪዎቻች ቡድኖች ተፈራርጆ እርስ በርሱ ተጨራርሷል፣ ቂምና ቁርሾም ተጋብቷል፣ ተሰዷል አሰድዷል። ዛሬም በልቡ ቂም ይዞና በቀልን አርግዞ በተለያዩ ድርጅቶች ውስጥ መሽጎ የጎሪጥ ይተያያል። ባገኘው አጋጣሚም ሆሉ ይናቆራል። ‘ቂም ተይዞ ጉዞ’ እንዲሉ ትላንት በተለያዩ ድርጅቶች ውስጥ ሆነው በጠላትነት ይፈራረጁና ሊገዳደሉ ይፍላለጉ የነበሩ ሰዎች ይህን ሸክማቸውን በንስሃ እና በይቅር ባይነት ከላያቸው ላይ ሳያራግፉ ውስጥ ውስጡን እየተብሰከሰኩና እየተፈራሩ ገሚሶቹ በልጅነታቸው በቆረቡባቸው ድርጅቶች እየማሉ ቀሪዎቹም ዘመኑ በወለዳቸው አዳዲስ ድርጅቶች ውስጥ ሆነው የለበጣ ውህደት እየመሰረቱ በዋዜማው ይፈረካከሳሉ። እንደ እኔ እምነት ከዚህ የእርስ በርስ መፈራረጅ፣ መፈራራትና የቆየ ቂምና ጥላቻ ሳንሽር የምንክበው ካብ ሁሉ የእምቧ ካብ ነው የሚሆነው። እየሆነ ያለውም ይሄው ነው። ከዚህ አዙሪት ወጥተንና ከቂም ተላቀን የጋራ ራዕይ እንዲኖረን እያንዳንዱ ግለሰብ እራሱን ለይቅርታ ማዘጋጀት አለበት። ከልብ የበደላቸውን ይቅርታ ለመጠየቅና ይቅርታ ለመቀበል። ከድርጅታዊ ወገንተኝነትም እራሱን ነጻ አውጥቶ በሱና በድርጅቱ ላይ የተፈጸመውን በደል ብቻ ሳይሆን እሱም ጠላት ብሎ በፈረጃቸው ሰዎችና ድርጅቶች ላይ ያደረሰውን ግፍና በደል ለመናዘዝና ለደረሰውም ሁሉ አቀፍ ጥፋት ድርሻቸውን በድፍረት በማንሳት የተጠታቂነት ባህልን ‘ሀ’ ብለው ሊጀምር ይገባዋል።
  • ይህ ሁኔታም የደረሰውን የጉዳት መጠን በቅጡ እንድናውቅ ከማድረጉም ባሻገር እርስ በርስ የመወነጃጀሉን ታሪክ እንድንገታውና ልባችንንም በፖለቲካ ንስሃ አንጽተን የሚነገርለትን ያህል የተሳካ ባይሆንም እንኳ ልክ እንደ ደቡብ አፍሪቃው ‘በእውነት’ ላይ ወደ ተመሰረተ የእርቅ እና የሰላም መድረክ እንድቀርብ እድል ይፈጥርልናል።
  • የልጆቹን እርስ በርስ መጨራረስ እየተመለከት ፓለቲካ እንዲህ ከሆነ አርፎ መቀመጥ ይበጃል፤ እርም የፖለቲካ ነገር በሚል አይምሮውን ጥርቅም አድርጎ ዘግቶ የለት ጉርሱን ብቻ እየቃረመ የአገሩን የፖለቲካ እጣፈንታ ለእዝጌሩ ትቶ ደግ ቀንና መልካም አስተዳደርን እንደመና ከሰማይ እንዲወርድለት የሚጠባበቀውም የኅብረተሰብ ክፍል አይኑን ይገልጣል፤ ከመጠፋፋት ወደ ሰለጠነ የውይይት ባህል በሚሻገረው የፓለቲካ ኃይልም ላይ እምነት ያሳድራል፤ እራሱንም ከፍርሃት ነጻ አውጥቶ በሙሉ ልብ በአገሩ ጉዳይ ባለቤት ይሆናል።
  • ስለዚህም የገዢው ኃይል ወያኔ ካለበት ጥልቅ ፍርሃት እና የሥልጣን ጥም የተነሳ ለእንዲህ ያለው ለውጥም ሆነ የሰላምና የእርቅ ጎዳና ገና ዝግጁ ባይሆንም የተቀሩት የፖለቲካ ሃይሎች መንገዱን በመጀመር ለዘመናት በመካከላቸው የቆየውን ቁርሾና ቂም ከአዕምሯቸው በማውጣት ከልብ የመነጨ እርቅ በማድረግ የልዩነት ግንቦችን ማፈራረስ ይጠበቅባቸውል። የሰላም፣ የእርቅ እና የእውነት አፈላላፉ ጉባዔ ያስፈልገናል።
በእውነት ላይ ተመስርተው ተቃዋሚዎች በቅል ልቦና ከታረቁ አብረው ከሠሩ በኢትዮጵያዊና በኢትዮጵያዊያን ላይ ለዘመናት እንደ መዥገር ተጣብቀው ደማችንን የሚመጡትን፣ ክብራችንን ገፈው እርቃን ያስቀሩንን፤ ድኅነት፣ እርዛት፣ አንባገነናዊ ሥርዓትና ጭቆና፣ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት፣ ጦርነትና የእርስ በርስ ግጭቶች፣ ድንቁርና፣ ጨለምተኝነት፣ ፍርሃት፣ ሙስና እና ጥላቻን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ነቅለን መጣል እንችላለን። ቅን ልቦና ይኑረን! ለዘመናት የተጫነንን ሸክማችንንም እናራግፍ። ያኔ ለፍቅር በፍቅር፣ ለሰላም በሰላም፣ ለነጻነት በነጻነት፣ ለአንድነታችን በአንድነት የምንሰራበትና ታሪክ ዘካሪ ብቻ ሳንሆን ታሪክ ሰሪ የምንሆንበት ጊዜ እሩቅ አይሆንም።
ቸር እንሰንብት!

አንድነትና የሚሊየንም ድምጽ ለነጻነት ንቅናቄ – አማኑኤል ዘሰላም

ታህሳስ 15 ቀን 2006 ዓ.ም
 
የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር፣ አቶ ይልቃል ጌትነት፣ በዉጭ አገር የሥራ ጉብኘት እያደረጉ እንደሆነ በስፋት እየተዘገበ ነዉ። ታዲያ «ስለ ሰማያዊ ብዙ እየሰማን፣ የአንድነት ፓርቲ ድምጽ ግን ምነዉ ጠፋ። የሚሊየነሞች ድምጽ ለነጻነትስ ወዴት ገባ ?» ብለን የምንጠይቅ ልንኖር እንደምንችል አስባለሁ። በዚህም ረገድ በአንድነት ፓርቲ ዙሪያ አንዳንድ ሃሳቦች ለአንባቢያን ለማካፈል እሞክራለሁ።
በቅድሚያ አንድ መረዳት ያለብን ነገር አለ። የአንድነት ፓርቲና እና ሰማያዊ ፓርቲ፣ ሁለቱም ተመሳሳይ የፖለቲካ ፕሮግራም ቢኖራቸውም ፣ ሁለቱም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለዉጥ ለማምጣት ቢታገሉም፣ የአሰራር ልዩነቶች አሏቸው። የአንድነት ፓርቲ፣ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ የትግሉ አካል እንደሆነ ቢያውቅም፣ መሰለፍ ብቻ በራሱ ምንም ሊያደርግ እንደማይችል ጠንቅቆ የተረዳ ደርጅት ነዉ። በዚህም ምክንያት ግብታዊ የሆኑ እንቅስቃሴዎችን ከማድረግ ብዙ ይቆጠባል። ሰልፎችም ሆነ ማናቸዉም አይነት ሰላማዊ እንቅስቅሴዎች ተጠንተዉ፣ በጥንቃቄና ዉጤት በሚያመጣ መልኩ መደረግ አለባቸው ብሎ ያማናል። ካለፈው የቅንጀት ስህተቶች ብዙ የተማረ ነው።
በመሆኑም ሰልፍ አልተደረገም ማለት እንቅስቃሴ የለም ማለት አይደለም። የአንድነት ፓርቲ በአሁኑ ወቅት እያደረጋቸው ያላቸዉን አራት በጣም አስፈላጊና መሰረታዊ ጉዳዮች እንዳካፍል ይፈቀድልኝ፡
1. አንድነት፣ ከሰኔ እስከ መስክረም የተደረገዉን የሚሊየኖችም ድምጽ ለነጻነት እንቅስቃሴዎች፣ እንዲሁም የፓርቲዉ ጠቅላላ ስራዎች፣ ወደ ኋላ ተመልሶ ግምገማ እያደረገ ነዉ። «የቱ መስተካከል አለበት ? የቱ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ? ..»እየተባለ ፣ ጠቃሚ ትምህርቶችን ለማሰባሰብ እየተሞከረ ነዉ። ዝም ብሎ መሮጥ አይደለም። ቆም ብሎም ማሰብና እራስን መመርመር፣ ካለፉትን ተግባራት መማር ያስፈልጋል።
2. ፓርቲው በቅርቡ የአመራር አባላትን ይመርጣል። አብዛኞቹ አገር ዉስጥም ሆነ በዉጭ ያሉ ድርጅቶች አንድ መሪ ነው ለዝንተ አለም የሚመራቸው። የአንድነት ፓርቲን መጀመሪያ ብርቱካን ሚደቅሳ፣ ከዚያም ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራዉ፣ ከዚያም ዶር ነጋሶ ጊዳዳ መርተዋል። አሁን ደግሞ ዶር ነጋሶን ለመተካት ሶስት እጩዎች የምረጡኝ ዘመቻ ላይ ናቸው። እነርሱም የፓርላማ አባል የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ፣ ቀድሞ ፓርቲዉን ሲመሩ የነበሩትና በበርካታ አባላት እንደገና እንዲወዳደሩ ግፊት እንደተደረገባቸው የሚነገረዉ፣ አንጋፋው ኢንጂነር ግዛቸው እንዲሁም ኮንሴንሰን ቢልድ በማድረግና በአስተዋይነታቸው የሚታወቁት፣ በአሁኑ ወቅት ፓርቲዉን በፋይናንስ ሃላፊነት የሚመሩት፣ አቶ ተክሌ በቀለ ናቸው።ይህ በአንድነት ዉስጥ እየተደረገ ያለው ፉክክር ፣ በማንም የአገራችን ድርጅቶች ያልታየ ዴሞክራሲያዊ  ፉክክር ነዉ።
3. እርግጥ ነዉ ከአሁን ለአሁን ሕብረት ያስፈልጋል ተብሎ፣ ወደ ኋላ ከሚጎትትና ስራን ከማያሰራ ድርጅት ጋር ሕብረት አይፈጠርም። ሕብረት ሲፈጠር ለዉጤት መሆን አለበት። በዚህም ረገድ አንድነት ከዚህ በፊት አካል ከሆናቸው እንደነ መድረክ ካሉ ስብስቦች ጋር ያለዉን ግንኙነት እየፈተሸ ነዉ። በአንጻሩም ደግሞ ፓርቲውን ሆነ ትግሉ ወደፊት እንዲሄድ ሊረዱ የሚችሉ ፣ ከሌሎች ድርጅቶች ጋር ፣ የላይ ላይ ትብብር ሳይሆን የዉህደት እንቅስቃሴ እያደረገ ነዉ። ከዚህ በፊት እንደ ብርሃን ፓርቲ ያሉ ድርጅቶች ከአንድነት ጋር መዋሃዳቸው ይታወቃል። አሁን ደግሞ አንድነት ፓርቲ ከአንጋፋዉ መኢአድና በአሁኑ ወቅት አስደሳች እንቅስቅሴ በሜዳ ላይ አያደረገ ካለው ከአረና ጋር ለመዋሃድ ትልቅ ሥራ እየሰራ ነዉ።
4. ሰላማዊ ሰልፍ ሆነ ሌላም ሌላም እንቅስቅሴዎች እንዲሁ በግብታዊነት አይሰሩም። ጥናት፣ ጥንቃቄ፣ ዝግጅት ያስፈልጋል። የስሜት ትግል የትም አያደርሰም። ትግሉ የሰከነ፣ የበሰለና ዉጤት የሚያመጣ መሆን አለበት። የአንድነት ፓርቲ የሚሊየነም ድምጽ ለነጻነት በሚል ስም የጀመረው እንቅስቃሴ ክፍል ሁለት፣ ከአመራር አባላት ምርጫ በኋላ፣ ይታወጃል። ይህ እንቅስቃሴ አዲስ አበባ ዉስጥ ብቻ ያተኮረ ሳይሆን፣ በመላ አገሩቷ ያተኮረ፣ ትግሉን አንድ እርምጃ ወደፊት የሚወስድ እንቅስቃሴ ይሆናል። ለዚህም እንዲረዳ አባላት በሰላማዊ ትግል ዙሪያ የተለያዩ ስልጠናዎች እየወሰዱ ናቸው።
እንግዲህ አገር ዉስጥና ከአገር ውጭ ለምትኖሩ ኢትዮጵያዊያን እንዲህ እላለሁ። በአገራችን ሙስና የመስፋፋቱ፣ ዘረኝነት የመብዛቱ፣ የሕግ ስርዓት ያለመኖሩ፣ የኑሮ ዉድነቱ፣ የሰባአዊ መብት ረገጣዉ ፣ ኢትዮጵያ ለብዙሃኑ ሲኦል፣ ከገዢው ፓርቲ ጋር ግንኙነት ስላላቸው ብቻ በአጭር ጊዜ ዉስጥ ሚሊየንር ለሆኑት ለጥቂቶች ገነት ለመሆኗ ምክንያቱ የፖለቲካዉ ችግር ነው። የፖለቲካ ችግርን ለማስተካከል ደግሞ የፖለቲክ ትግል ይጠይቃል። የአንድነት ፓርቲ ይህ ለሰላምና ለፍትህ የሚደረገዉን የፖለቲክ ትግል ለመምራት እየሰራ ነዉ።
የአንድነት ፓርቲ ከሁለት ወራት በፊት ባደረጋቸው አገረ ሰፊ፣ የሚሊየም ድምጽ ለነጻነት እንቅስቃሴዎች፣ በአዲስ አበባ፣ በመቀሌ፣ በጎንደር፣ በባህር ዳር፣ በደሴ፣ በጂንካ፣ በአርባ ምንጭ፣ በወላይታ ሶዳ፣ በባሌ/ሮቢ ፣ በፍቼና በአዳማ ሰላማዊ ሰልፎች አድርጓል። በመቀሌ ሰልፉ ሊደረግ አንድ ቀን ሲቀረዉ የሕወሃት ባለስልጣናት «እንኳን አንድነት፣ ቅንጅትም መቀሌን አልደፈረም»በሚል የቅስቀሳ መኪናዎችን እና ማይክሮፎኖችን በማገታቸውና የአመራር አባላትን በማሰራቸው፣ ከአሥር አምስት ቀናት ቅስቀሳ በኋላ ሰልፉ ሊሰረዝ ችሏል። በባሌ/ሮቢ፣ ኦሕድዶች ሰልፉ ከመደረጉ አንድ ቀን በፊት፣ «ሰልፉን ካደረጋቸው ከፍተኛ ደም መፋሰስ ይሆናል» የሚል ዛቻ በመሰንዘራቸው ፣ ሕዝብን አደጋ ላይ ላለመጣል ሲባል፣ ሰልፉ ሳይደረግ ቀርቷል።
የአንድነት ፓርቲ በአዋሳ፣ በጋምቤላ፣ በወሊሶ፣ በድርደዋና በአሳሳም ሰልፎች ለማድረግ እቅድ ነበረዉ። ነገር ግን በገንዘብ ማነስ ምክንያት እነዚህ ከተሞች ሰልፍ ማድረግ እንዳልተቻለ ነው።
አሁንም ፓርቲዉ የተቻለዉን ለማድረግ የወሰነነ የቆረጠ ቢሆንም፣ ፓርቲዉ የሕዝብ ድጋፍ ከሌለዉ ሊያደርግ የሚችለው የተወሰነ ነዉ። በተለይም የገንዘብ አቅም ላይ ትልቅ ትኩረት መስጠት እፈልጋለሁ። እንዲሁ ለዉጥ ስለተመኘን ለዉጥ አይመጣም። አገር ቤት ያሉ ኢትዮጵያዉያን በጓዳና በሹክሹክታ ብሳታችንን መግለጽ ማቆም ይኖርብናል። ትግሉ የእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊን ተሳትፎ ይጠይቃል። ጠንካራ ፓርቲ ሲመጣ መቀላቀሉ ሳይሆን፣ አሁን ያሉትን፣  እንድ አንድነት ፓርቲ አይነቶችን ጠንካራ እንዲሆኑ ማድረጉ ይበጃል።
ዉጭ አገር ያለነው ፣ ምን እንኳን የመገደል፣ የመታሰር፣ የመዋከብ አደጋ ባያገኝንም፣ ቢያንስ ስራችን እና አፋችን መገናኘት ያለባቸው ይመስለኛል። «አገር ቤት ካሉት ድርጅቶች ለዉጥ ለምን አያመጡም» ብለን መናገርና መጠየቅ ሳይሆን፣ ለዉጥ እንዲያመጡ የነርሱ አካል ሆን ድጋፋችንን መስጠት ይጠበቅበናል። ሕዝቡ ካልተነሳና ካልተነቃነቀ በምን ሁኔታ ለዉጥ ሊመጣ አይችልም። ህዝቡ እንዲነሳ ሕዝቡ መሃከል ሆኖ ትልቅ ድርጅታዊ ሥራ መስራት ያሰልጋል። ይህን አይነት ድርጅታዊ ሥራ ለመስራት፣ ሕይወታቸው ለዚህ ሥራ አላልፈው ከሰጡ አገር ቤት ካሉ ጀግኖች ጎን መቆም ይኖርብናል።
እንግዲህ ለሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት እንቅስቃሴ ክፍል ሁለት ከወዲሁ ሁላችንም እንዘጋጅ። ፓርቲዉን በገንዘባችን እንደግፍ። በገንዘብ ለመርዳትና ከሚሊዮኖች አንዱ ለመሆን የሚፈልጉ ከሆነ የሚከተለዉን ድህረ ገጽ ይጎብኙ !
http://www.andinet.org/

የቁጫ ህዝብ ጥያቄ የሚፈታው የዜጎች መብት ሲከበር ነው!!አንድነት ፓርቲ ልዩ ጠቅላላ ጉባኤውን ታህሳስ 19እና20/2006ዓ.ም ያደርጋል – ከአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት)የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

ኢህአዴግ በሚከተለው የዘረኝነት ፖሊሲና የከፋፍለህ ግዛው አገዛዝ መርህ ዛሬ በሃገራችን የአንድ አካባቢ ህዝብ በሌላው አካባቢ በነፃነት ሰርቶ የመኖር ህገ-መንግስታዊ መብት በገዢው ፓርቲ አመራር አባላት ሴራ ሲጣስ ይታያል፡፡ ባሳለፍናቸው አመታት በማንነታቸውና በእምነታቸው ምክንያት ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸው ተረግጠው በአስርና በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ተወልደው ወልደው ሃብት ንብረት ካፈሩበት መሬት ተፈናቅለውና በዚሁ ሳቢያ ለስደትና ለልመና የመዳረጋቸው ሚስጢር በማናቸውም መልኩ የኢህአዴግ አምባገነናዊ አገዛዝ ድምር ውጤት ነው፡፡
ካለፈው አመት መጨረሻ አካባቢ በደቡብ ክልል በጋሞ ዞን በቁጫ ወረዳ ህዝብና ነዋሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን እስራት፤ ስደት፤ ወከባና እንግልት እንዲሁም ሞት በተለያየ የመገናኛ ብዙሃን ድህረ ገፆች መረጃው በስፋት መቅረቡን ተከትሎ ፓርቲያችን በዚህ ጉዳይ ላይ የፖለቲካ አቅዋም ለመያዝ እንዲያስችለው አንድ በፓርቲው ከፍተኛ አመራር የሚመራ ቡድን ወደ ቦታው በመላክ የተሰበሰበውን መረጃ የፓርቲው ብሄራዊ ምክር ቤት ታህሳስ 13ቀን 2006ዓ.ም በጠራው አስቸካይ ስብሰባ በቁጫ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን የፖለቲካ አለመረጋጋት መርምሮ ውሳኔ አስተላልፉዋል፡፡
የቡድኑ የመስክ ጉብኝት መረጃ እንዳመለከተው የቁጫ ህዝብና ነዋሪዎች ጥያቄ ማቅረብና ህዝባዊ የተቃዉሞ እንቅስቃሴ የጀመሩት በወረዳዉ ምንም አይነት ልማትና ህዝቡም በፖለቲካውና በኢኮኖሚው ዘርፍ ለመሳተፍ የተሰጠው እድል ዝቅተኛ ወይም የለም በሚል ቁጭት ደረጃ በደረጃ የመብት ጥያቄ በማንሳት ነው፡፡ በተለይ ከሰኔ ወር 2005ዓ.ም ጀምሮ የህዝቡ ብሶት እየተባባሰ በመምጣቱ መንግስት ተመጣጣኝ ያልሆነ ኃይል እርምጃ መውሰዱ በሪፖርቱ ተመልክቱዋል፡፡ 1015 የሚሆኑ ሰዎች በወረዳው ፖሊስ ጣቢያ፤ በአርባ ምንጭና በጨንቻ ወህኒ ቤቶች መታሰራቸው፤ አቶ ዛራ ዛላ የተባሉ የሁለት ልጆች አባት ህዳር 14ቀን 2006 ኮዶ ኮኖ ቀበሌ ውስጥ በጥይት ተመተው ሞተዋል፤ ሰውየው በጥይት ሲመቱ በቦታው የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ሶጋት ሳንታ፤ አቶ አሸብር ደምሴ የገዢው ፓርቲ የወረዳው ድርጅት ጉዳይ ሃላፊ እና አቶ አያኖ መሰና የወረዳው የፀጥታ ሃላፊ መኖራቸው ደግሞ የመንግስት ኃላፊዎችን ተባባሪ ወይም አስተኩዋሽ ያደርጋቸዋል፡፡ ከዚህም በቀር ህዝቡ በገዢው ፓርቲ ካድሬዎችና ፀጥታ ኃይሎች ማስፈራራት፤ ማዋከብና ሰርቶ የመኖር ነፃነቱ እንደሌለው እንዲሁም ያለመረጋጋትና የፀጥታ ስጋት ስላለ በርካታ ሰዎች ወደ ጎረቤት አካባቢዎች እየተሰደዱ መሆናቸውን ሪፖርቱ ይገልፃል፡፡
በተጨማሪም የወረዳው ህዝብ በሚጠራባቸው ስብሰባዎች ሁሉ የአንድነት ፓርቲ በወረዳው የዘረጋው ጠንካራ መዋቅር እንዲበተን በአንዳንድ የስብሰባው ተካፋዮች “አንድነት ፓርቲ እያለ ልማት አይኖርም፤ እንዴት አንድነትን መንቀል አቃታችሁ፤ የእኛው አካባቢ የፓርቲውን ሰዎች እንዴት ይዛችሁ ማሰር አቃታችሁ” የሚል አስተያየት በተሳታፊዎች የቀረበ በማስመሰል ኢህአዴግ የተለመደውን ድራማ እየሰራ ስለመሆኑ በቡድኑ ሪፖርት ተመልክቱዋል፡፡
እንዲሁም የልዑካኑን መሪ አቶ ትዕግስቱ አወሉ የብሄራዊ ምክር ቤት ዋና ጸሃፊን ጨምሮ ሰባት አባላት “እንዴት መጣችሁ፤ መንግስት በፀጥታ ችግር ላይ ነው፤ ይህንን ለመፍታት በሚደረገው ታላቅ ህዝባዊ ኮንፈረንስ እለት መገኘታችሁ አፋራሽ ተልእኮ ይዛችሁ የመጣችሁ ሰለሚሆን እንጠረጥራችኃለን” በሚል በፖሊስ ቁጥጥር ስር ከአራት ሰዓት በላይ በማዋል በፀጥታ ኃይሎች የማዋከብ ተግባር ተፈፅሞባቸዋል፡፡ የአንድነት ፓርቲ ብሄራዊ ምክር ቤቱ በቀረበው ሰፊ ሪፖርት ላይ ውይይት ካደረገበት በኃላ የሚከተለውን የፖለቲካ ውሳኔ አስተላልፉዋል፡፡
1. በቁጫ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለው የሰብአዊ መብት ረገጣ በአስቸካይ እንዲቆምና ስለደረሰው ሰብአዊና ቁሳዊ ጉዳት የሚያጣራ በገለልተነኛ ወገን እንዲጣራ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲወሰን፤
2. የቁጫ ህዝብ ጥያቄ የስራዓቱ አምባገነናዊነት እንዲቆም በመሆኑ የህገ መንግስታዊ መብቶቻቸው ተከብረው ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያዘ የታሰሩት ዜጎች በአስቸካይ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ፤
3. ቁሳዊና ስነልቦናዊ ጉዳት የደረሰባቸው ዜጎች የሞራል ካሳ እንዲሰጣቸው፤
4. በዜጎች ላይ ጉዳት ያአደረሱት ግለሰቦች ለህግ እንዲያቀርቡ፤
5. የገዢው ፓርቲ ካደሬዎች በየስብሰባው ፓርቲያችንን አሉታዊ በሆነ መልኩ ከመፈረጅ ይልቅ የዘጎችን ጥያቄ በህግና በዴሞክራሲያዊ መንገድ ለመፍታት መንግስት ጥረት ያድርግ፤
6. የቁጫ ወረዳ ተወላጅ የሆነው የፓርቲያችን ከፍተኛ አመራር አባላትን ማሳደድና ማወከብ እንዲቆም፤
7. ይህ ሁኔታ የማይሻሻል ከሆነ በመዋቅራችን በመጠቀም በከፍተኛ ሰላማዊ ሰልፍ ህዝባዊ ተቃውሞ ፓርቲው በአካባቢው እንደሚጠራ፤ የፓርቲያችን ብሄራዊ ምክር ቤት ወስናል፡፡
በዚህ ጋዜጣዊ መግለጫ ማንሳት የምንፈልገው ጉዳይ የኢህአዴግ አምባገነናዊ ስርአት በህዝብ ሙሉ ተሳትፎ በማስወገድ በአገራችን ዴሞክራሲያዊ ስርአት ለመገንባት አንድነት ፓርቲ እንደ አንድ የፖለቲካ አማራጭ ታግሎ ለማታገል ከተደራጀ አምስት አመት አልፎታል፡፡ በዚህ ጊዜ ውስጥ ታህሳስ 19እና20 2006ዓ.ም የሚደረገውን ስትራቴጂካዊ ጠቅላላ ጉባኤን ጨምሮ ሶስት ጠቅላላ ጉባኤዎችን አድርጉዋል፡፡
የአሁኑን ጉባኤ ከአንድ ወር በፊት ለማድረግ ታቅዶ ለስብሰባ የሚሆነንን አዳራሽ ለማግኘት ከፍተኛ ፈተና ገጥሞናል፡፡ የአዳራሾቹ አከራዮች በምንፈልገው ቀን አዳራሹ አለመያዙን ይነግሩንና ለአንድነት ፓርቲ ለስብሰባ ነው የፈለግነው ሲባሉ አንዳንዶቹ እንደውልላችኃለን ሲሉን አንዳንዶቹ ደግሞ በግልጽ “እንስራበት ተውን” ይሉናል፡፡ የምርጫ ቦርድን አዳራሽ እንካን ጠይቀን የተሠጠን ምልሽ “ለስልጠና ፕሮግራም ተይዞበታል” ነው የተባልነው፡፡ በመጨረሻ ፈቅደው ያከራዩን ሰዎችንም ቢሆን ከፍተኛ ጫና ተደርጎባቸዋል፡፡ ከዚህ ሁኔታ መረዳት የሚቻለው ገዢው ፓርቲ ተቃዋሚዎችን ፈርቶ የንግዱን ህብረተሰብ ማሸበር እንደሆነ ነው፡፡
በጉባኤችን እስከ 500 የሚደርሱ የድምፅ ተሳታፊዎች፤ እስከ 150 ሚደርሱ ተጋባዥ የፖለቲካ መሪዎችና እንግዶች እንዲሁም የሚዲያ ባለሞያዎች ይገኙበታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ጉባኤው የፓርቲውን ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ፤ የብሄራዊ ምክር ቤት አባላትን፤ የኦዲትና ቁጥጥር ኮሚሽን ሪፖርቶችን ያዳምጣል ውሳኔም ያስተላልፋል፡፡እነዲሁም የፓርቲውን ፐሬዚደንት፤ የብሄራዊ ምክር ቤትና የኦዲትና ቁጥጥር ኮሚሽን አባላትን ይመርጣል፡፡ የፓርቲውን ፕሮግራምና ደንብ የማሻሻያ ረቂቆችን መርምሮ ያፀድቃል፡፡ ሌሎች ከተሰናባቹ ምክር ቤት የሚቀርቡለትን የውሳኔ ሃሳቦችን መርምሮ ያፀድቃል፡፡
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ(አንድነት)
ታህሳስ 17ቀን 2006ዓ.ም
አዲስ አበባ

Monday 23 December 2013

በእስር ላይ የሚገኙት የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ አባላት በእስር ቤት ስቃይ እንደተፈጸመባቸው ገለጹ

በማእከላዊ እስር ቤት ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የስነልቦናዊ እና አካላዊ ስቃይ አድርሰውብናል የሚሉት በእስር ላይ የሚገኙት የሙስሊሙ የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት፣ የደረሱባቸውን በደሎች ዘርዝርው አቅርበዋል።  ” ከአስራ አራት ሰአት በላይ ያለ እረፍት ቀጥ ብለን እንድንቆም በማድረግ፣ ጀርባችን ሰንበር እስኪያወጣ እና እስኪገሸለጥ ራቁታችንን በሽቦ በመግረፍ፣ በሰንሰለት በማሰር እና አይናችንን በጨርቅ በመሸፈን የውስጥ እግራችን እስከሚላጥ ገልብጦ በመግረፍ፣ ቀንና ማታ አሰቃቂ በሆነ ምርመራ እና ድብደባ እንቅልፍ በመንሳት፣ ሃይማኖታችንንና ክብራችንን በመንካት፣ ጺማችንን በመንጨትና እንድንላጭ በማስገደድ፣ እንዲሁም ሶላት በመከልከል፣ ቤተሰብ፣ ጠበቃ ፣ሀኪምና ሀይማኖት አባት እንዳናገኝ በማድረግ፣ ከአቅም በላይ የሆነን ስፖርት በግድ በማሰራት፣ ብልት በመግረፍ፣ ” ልጅህን እንገለዋለን! ሚስትህን አስረን በፊትህ ቶርች እናደርጋታለን! ብልትህ ላይ ሀይላንድ በማንጠልጠል ማሀን እናደርግሀለን” ሲሉ በማስፈራራት ከፍተኛ ስቃይ አድርሰውብናል ብለዋል።
በህገመንግስቱ አንቀጽ 18 ንኡስ አንቀጽ 1 ” ማንኛውም ጭካሄ ከተሞላበት፣ ኢሰብአዊ ከሆነ ወይም ክብርን ከሚያዋርድ አያያዝ ወይም ቅጣት የመጠበቅ መብት አለው” ቢልም፣ እኛ ግን ” ዜጎች መሆናችንን ጥርጣሬ ውስጥ በሚከት መልኩ ከያዙን በሁዋላ በማእከላዊ በክረምት ቀርቶ በበጋ እንኳን ቅዝቃዜው በማይቻለው ” ሳይቤሪያ” ተብሎ በሚጠራው ጨለማ ክፍል ለ3 ዋር አገሩው መቋቋም የሚአዳግተውን የማሰቃያ ስልታቸውን በመጠቀም አላሰብነውንና ያልሰራነውን ” እመኑ! ተናገሩ! ፈርሙ! ብለው አስገድደውናል”  ሲሉ በመግለጫቸው ጠቀስዋል።
ፍርድ ቤት ስቃዩን እንዲያስቆምልን ብንጠይቅም፣ ያገኘነው ውጤት ግን ወደ ማእከላዊ ስንመለስ ከመርማሪዎቹ በቀልና ተጨማሪ ስቃይ ነበር፣ የሚሉት ኮሚቴዎቹ፣ አሰቃዮቻችን ስለህገመንግስቱ እና መብት ስንናገር ” ህገ-መንግስቱን ቀደህ ጣለው፣ እኛ መስዋትንት ከፍለን ነው እዚህ የመታነው በማለት ለህግም ሆነ ለሰው ክብር ዴንታ እንደሌላቸው አሳይተውናል” ሲሉ አክለዋል።
ከቤተሰብ፣ ከጠበቃና ከሀኪም ጋር እንዳንገናኝ አድረገው የፈጸሙብን የህግ ጥሰት እና አስገድደው በማስፈረም እና ድምጽና ምስላችንን በመቅረጽ የፈጸሙብን በደል በወንጀለኛ መቅጫ ህግ ቁጥር 424 መሰረት እስከ አስር አመት የ አስቀጣ ኢ-ሰብአዊ ተግባር ቢሆንም የፖሊሱም፣ አቃቢህጉም ፣ የፍርድ ቤቱም አለቃ በሆነውና የፍትህ ስርአቱን ሰብስቦ በያዘው ገዢው ፓርቲ አምባገነንነት በተቃራኒው እኛ ተከሳሽ ሆነን ጉዳያችን በፍርድ ቤት በመታየት ላይ ይገኛል ብለዋል።
መንግስት በአግባቡ ሊተውነው ያልቻለውን አሳፋሪ የፍርድ ቤት ድራማውን ህዝብ እንዳያይበት ለመሸሸግ በመገደዱ የተከሰሱ ሰዎች ክስ ከቀረበባቸው በሁዋላ ተገቢ በሆነ አጭር ጊዜ ውስጥ በመደበኛ ፍርድ ቤት ለህዝብ ግልጽ በሆነ ችሎት የመስማት መብት አላቸው የሚለውን ህገመንግስታዊ መብት በመጣስ ችሎቱ ዝግ እንዲሆን ተደርጎ ቆይቷል የሚሉት የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት፣  በዝግ ችሎቱ የምስክር መስሚያ ጊዜ ብዙ አስገራሚ ድራማዎችን አይተናል፣ አቃቢ ህግ ዳኞች የሚሰጡትን ብይን እንደማይቀበሉ እስከመግለጽ የደረሱበትን እና ምስክሮችን ማለት ያለባቸውን አሰልጥነዋቸው እንደሚያመጡ አምልጧቸው የተናገሩበትን አጋጣሚ ” መታዘባቸውን ይገልጻሉ።
የኮሚቲው አባላት ” በሙስሊሞች መካከል እና በሙስሊሙና በክርስቲያኑ መካከል የታየውን አንድነትና መከባበር በጋራ መጠበቅ እንደሚያስፈልግ መክረዋል።  በጽናት ሰላማዊ የመብት ትግሉን የሚቀጥሉ መሆናቸውንና የሚያስከፍለውን መስዋትንት ሁሉ ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውንም ተናግረዋል። ለቀጣዩ ሰላማዊ የመብት ትግል እርከንም  በሙሉ ዝግጅት ላይ መሆናቸውን” ገልጸው፣ መንግስት በማእከላዊ እስር ቤቶች የሚፈጸሙትን ኢ-ሰብአዊ ድርጊቶች እንዲያስቆምና የህሊና እስረኞችን እንዲለቅ ጠይቀዋል።

በቀብሪ ቤያህ እስር ቤት ውስጥ የሞቱ ሰዎች የሉም ሲል የክልሉ ፖሊስ አዛዥ አስተባበሉ

የክልሉ ጽህፈት ቤት ፖሊስ አዛዥ  ከጅጅጋ 25 ኪሜ ገደማ በምትገኘዋ ቀብሪበያህ እስር ቤት ውስጥ የሞቱ ሰዎች ስለመኖራቸው ሪፖርት እንዳልደረሰቻው ገልጸዋል። አዛዡ እንዳሉት በክልሉ የሚንቀሳቀሱ ሽብረተኞችን በተመለከተ ከፌደራል መንገስቱ የጸረ ሽብር ግብረሀይል ጋር በጋራ የሚሰሩ በመሆኑ፣ በዚሁ ወንጀል ተጠርጥረው የሚያዙ ካሉ በጋራ የሚታይ ጉዳይ ይሆናል ሲሉ አክለዋል
በጅጅጋ የተከበረውን የብሄር ብሄረሰቦች በአል ምክንያት በማድረግ “መታወቂያ የላቸውም፣ የከተማዋን ገጽታ ያበላሻሉ፣ ከተማዋን ያቆሽሻሉ፣ የጸጥታ ስጋት ደቅነዋል በሚል ከ770 በላይ ሰዎች ቀብሪበያህ በሚባለው ወረዳ ውስጥ በአንድ ክፍል ውስጥ እንዲታሰሩ ከተደረጉት መካከል ከ40 በላይ የሚሆኑት መሞታቸውን ማንነታቸው እንዳይታገለጽ ከጠየቁ የክልሉ ባለስልጣናት ያገኘውን መረጃ በመንተራስ ዘገባ መስራታችን ይታወሳል።
እስረኞቹ የሞቱት በምግብ እጥረትና በእስር ቤቱ ውስጥ በተነሳ የታይፎይድ ( ተስቦ) በሽታ መሆኑን የዜናው ምንጮች ገልጸዋል። ዘመዶች የሞቱባቸውንና ለቅሶ የተቀመጡ ሰዎችን ኢሳት ለማነጋገር ቢሞክርም፣ ሰዎቹ  ለደህንነታቸው በመስጋት ለመናገር ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል።
ሰዎችን ከከተሞች በመውሰድ ያሰሩዋቸው በክልሉ ውስጥ የሚንቀሳቀሱት ልዩ ሚሊሺያ እየተባሉ የሚጠሩት ታጣቂዎች መሆናቸውን ምንጮች አክለው ገልጸዋል። ማንኛውም የሰብአዊ መብት ድርጅት በአካባቢው በመሄድ በቀላሉ ማረጋገጥ የሚችለው ሀቅ ነው በማለት የክልሉ ፖሊስ አዛዥ የሰጡትን ማስተባበያ ውድቅ አድርገዋል። ለሁለት ወራት ያክል ታስረው የነበሩት በተለያዩ ምክንያቶች የታሰሩ የከተማዋ ነዋሪዎች ባለፈው ሳምንት መለቀቃቸውን መዘገባችን ይታወሳል።

ገዢው ፓርቲ የአንድ ለአምስት አደረጃጀትን ወደ ቤተሰብ አወረደ

 ገዢው ፓርቲ በመንግስት መስሪያ ቤቶች ፣ በትምህርት ቤቶች ፣ በአርሶ አደሩና በከተማው ነዋሪዎች ላይ  ሲዘረጋ የቆየውን የአንድ ለአምስት አደረጃጀት በቤተሰብ ደረጃ ለማዋቀር የተለያዩ ደብደባዎችን እየበተነ ነው።
የቦሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ ለወረዳ 02 የቤተሰብ አባላት ባዘጋጀው የቤተሰብ ማቋቋሚያ ቅጽ ላይ የቤተሰብ ፖሊስ መመስረት ያስፈለገበት ዋና ምክንያት ” በቤተሰብዎ መካከል ለሚፈጠሩ የጸጥታ ችግሮች ማለትም ያለመግባባቶች፣ የተለያዩ ማህበራዊ ግችቶች ወዘተ የመሳሰሉት ችግሮች ሲፈጠሩ እርስዎ ወይም የቤተሰብዎ  ወኪል እንደ ፖሊስ ሆኖ በቅርበት ከፖሊስ ጋር እየተወያየ የማስታረቅ፣ የማስማማት ስራ እንዲሰራ እና ችግሩን እየተከታተለ እዛው መፍትሄ እንዲሰጥና መፍታት ያልተቻለ በአካባቢው ከተመደቡት የፖሊስ አባላት ጋር ለመፍታት ታስቦ የተዘጋጀ ነው” ይላል።
በቤተሰብ ፖሊስ ማቋቋሚያ ቅጹ ላይ ” የመራች የቤተሰብ ፖሊስ ወይም ተወካይ ስም፣ የቤተሰብ ብዛት፣ ስልክ ቁጥር፣ የተወካይ ፊርማ፣ መንደር ወይም ልዩ ቦታ፣ የብሎክ ቁጥር፣ ብሄርና መግለቻ የሚሉ  ጥያቄዎች ተካተዋል።
በተመሳሳይ ዜናም የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ በከተማው ውስጥ በሚገኙ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የመማር ማስተማሩን ሒደት በጥራት ለማከናወን ይረዳል በማለት ‹‹ኮማንድ ፖስት›› የተሰኘና ሌሎች ተጨማሪ አደረጃጀቶች በማስተዋወቅ ላይ መሆኑን ሪፖርተር ዘግቧል።
የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ በዳግማዊ ምኒሊክ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በከተማው ከሚገኙ ሁሉም ትምህርት ቤቶች ለተጠሩ ርዕሳነ መምህራን፣ ሱፐርቫይዘሮችና ከሁሉም ክፍላት ከተሞችና ወረዳ ጽሕፈት ቤቶች ለተወከሉ ኃላፊዎች በአዲሶቹ አደረጃጀቶች ዙሪያ ገለጻ አድርጓል።
በቅርቡ ወደ ሁሉም ትምህርት ቤቶች ይወርዳል ከተባለው የኮማንድ ፖስት አደረጃጀት በተጨማሪ፣ ‹‹ትራንስፎርሜሽን ፎረም›› እና ‹‹የልማት ቡድን›› የሚሰኙ አደረጃጀቶችም እንደሚተዋወቁ ጋዜጣው ዘግቧል።
‹‹ኮማንድ ፖስት›› አደረጃጀት ዋና ተግባሩ ትምህርት ቤቶችን ከሕዝባዊና ከመንግሥት ክንፎች ጋር ማስተባበር እንደሆነ የዘገበው ጋዜጣው ፣ የ‹‹ትራንስፎርሜሸን ፎረም›› እና ‹‹የልማት ቡድን›› የተባሉት አደረጃጀቶችም በየትምህርት ቤቱ በሚገኙ የትምህርት ክፍሎች ውስጥ ተግባራዊ የሚደረጉ ሲሆን፣ ‹‹አንድ ለአምስት›› በሚል ስያሜ የተጀመረውን አደረጃጀት ለማጠናከርና ለማስቀጠል ጠቃሚ መሆናቸው ተመልክቷል።
ላለፉት ጥቂት ዓመታት በ‹‹ግንባር ቀደም›› አደረጃጀት በኋላም በ‹‹ተጓዳኝ›› አማካይነት የተከናወነው ሥራ የታሰበውን ውጤት ማምጣት አለመቻሉ ግልጽ መሆኑ በመታወቁ ‹‹ኮማንድ ፖስት›› የተባለውን አደረጃጃት ለማስተዋወቅ አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱ ተገልጿል።
መንግስት የትምህርት ጥራት ለማሻሻል ‹‹ተጓዳኝ›› የሚባለውን አደረጃጀት ማምጣቱን ቢገልጽም፣ አንዳንድ መምህራን ግን መንግሥት መምህራኑን ‹‹ለመጠርነፍ›› ሲል ያመጣቸውና ‹‹ከጥቅሙ ጉዳቱ የሚያመዝን አላስፈላጊ መሣሪያ›› ነው ሲሉ ውድቅ ያደርጉታል።
ጋዜጣው አያይዞም ፣ ‹‹አደረጃጀት በዛ፣ እኛም ለማስፈጸም እየተቸገርን ነው፤›› በማለት ርዕሰ መምህራን ለትምህርት ቢሮ ኃላፊው መግለጻቸውን ዘግቧል፡፡ ባለስልጣኑ ግን መምህራን የማሳመን ስራ መስራት ይኖርባቸዋል በማለት የርእሰ መምህራኑን ቅሬታ ሳይቀበሉት ቀርተዋል።
ጋዜጣው ያነጋገራቸው መምህር ስለአደረጃጀት መብዛት ተጠይቀው  ‹‹አደረጃጀት በማለት መንግሥት በየትምህርት ቤቶቻችን የሚያመጣብን አሠራሮች ብዙ ጊዜ መምህራንን ከማባሳጨት አልፎ የትምህርት ጥራትን የባሰ እየገደለ ነው፤›› በማለት መልሰዋል።
መንግስት የአገሪቱን ህዝብ በመላ በአንድ ለ አምስት አደረጃጀት ለመቆጣጠር ያስባል በሚል ወቀሳ እቀረበበት ቢሆንም፣ ኢህአዴግ በ9ኛው መደበኛ ጉባኤ በአደረጃጀቱ እንደሚገፋበት ውሳኔ አሳልፎአል።

በተንቤን ህዝባዊ ስብሰባ ተደረገ! (አብርሃ ደስታ – ከትግራይ)

መቀሌ መነሃርያ ስትገቡ ብዙ ተሽከርካሪዎች ተሳፋሪ ሲጠባበቁ ታያላቹ። ረዳቶች ‘የት ናችሁ? እዚህ ግቡ!’ ምናምን እያሉ ይሽቀዳደሙላችኋል፣ ይለሙኗችኋል። በመነሃርያው ብዙ አቅጣጫዎች መኪኖች መልተው ተጓዥ ሰው ይጠባበቃሉ። በአንድ ኮርነር ጥግ ግን ብዙ ተጓዝ ሰዎች የአንድ አውቶቡስ መምጣት ለብዙ ሰዓታት ይጠባበቃሉ። እነዚህ ለሰዓታት የሚንገላቱ ሰዎች ወደ ተምቤን ዓብይ ዓዲ የሚጓዙ ሰዎች ናቸው።
ቅዳሜ ጠዋት (ሁለት ሰዓት) ወደ ተምቤን ዓብይ ዓዲ ለመሳፈር መነሃርያ ገባሁ። ወደ ዓብይ ዓዲ ከተማ የሚሄድ መኪና የለም። ወደ ሌሎች ከተሞች የሚሄዱ መኪኖች ግን ሞልተዋል። በመነሃርያው የሚቆዩ በቂ ተሳፋሪ እስኪያገኙ ድረስ ነው። ወደ ተምቤን የምንጓዝ ግን የመነሃርያው አቧራ ሳይበግረን በትዕግስትና በተስፋ እንጠባበቃለን። ከሁለት እስከ አምስት ሰዓት ጠበቅን። ሲጨንቀን የትራንስፖርት ሓላፊዎቹ አማከርን። ‘ሁሌ እንደዛ ነው! ጠብቁ! ይመጣሉ’ አሉን።
ሁሌ እንደዛ መሆኑ አዋቅ ነበር። ወደ ተምቤን ዓብይ ዓዲ ስጓዝ ለሦስተኛ ግዜየ ነው። በሦስቱም ተመሳሳይ ሁኔታ አጋጥሞኛል። ‘ግን ለምንድነው ወደ ተምቤን የሚሄዱ መኪኖች የሌሉ?’ ብለን ጠየቅን። ‘መንገዱ ችግር ስላለበት ሹፌሮች ወደ ተምቤን መሄድ ስለማይፈልጉ ነው’ የሚል መልስ አገኝን። ሚኒባሶች ጭራሽ አይሄዱም። የተወሰኑ አውቶብሶች ብቻ ናቸው ወደ ዓብይ ዓዲ የሚመላለሱ።
ምን ማድረግ እንዳለብን ጠየቅናቸው። ‘ፐርሰንት ከፍላቹ ከባለባሶች ጋር መደራደር ትችላላቹ’ አሉን። ለመደራደር ወስነን ተስማማን። ሰልፍ ይዞ የነበረ ህዝብ ግን ብዙ ነው። በአንድ አውቶቡስ ሊጫን አይችልም። በሃይል ሩጠን፣ ተረጋግጠን፣ ሴቶችና ህፃናት አልፈን ገባን (ሰብአዊነት ቀረ)። የተወሰንን ተሳፈርን አብዛኛው ቀረ። ሁለት ሰዓት መነሃርያ የገባን ሰባት ሰዓት ጉዞ ጀመርን።
ተምቤን ዓብይ ዓዲ ከመቀሌ በስተ ምእራብ (?) በ90 ኪሎ ሜትር ርቀት የሚገኝ ነው። መንገዱ በጣም አስቸጋሪ ከመሆኑ የተነሳ ሰባት ሰዓት ተነስተን አስራ አንድ ሰዓት ደረስን። ለዘጠና ኪሎሜትር ርቀት አራት ሰዓት ፈጀብን።
ዓብይ ዓዲ የጥንት ከተማ ነው። ከዉቅሮ ቀጥሎ ለመቀሌ ቅርብ የሆነ ከተማ ዓብይ ዓዲ ነው። ሁሉም ዋና ዋና የትግራይ ከተሞች ከመቀሌ የሚያገናኝ አስፋልት መንገድ ተገንብቶላቸዋል (ከዓብይ ዓዲ ከተማ ዉጭ)። የኢህአዴግ መንግስት ዓብይ ዓዲ ከመቀሌ ከተማ ጋር በአስፋልት መንገድ ለማገናኘት ሃያ ሦስት ዓመት ፈጅቶበታል።
የተምቤን ህዝብ በ1996 ዓም ጥያቄ አስነስቶ ተቃውሞውን በሰለማዊ ሰልፍ ገልፀዋል። በወቅቱ ከተነሱት ጥያቄዎች የፍትሕ እጦት፣ የመብራትና የውኃ አገልግሎቶች፣ የአስፋልት መንገድ ጉዳይ ዋናዎቹ ነበሩ። የተቃውሞ ሰልፉ መሰረታዊ ምክንያትም ህወሓት በተምቤን ህዝብ ላይ አድልዎ እየፈፀመ ነው፤ ልማት እንዳናገኝ ተደርገናል፣ የተለየ ዓፈና ይደርስብናል ወዘተ የሚል ነበር።
ህወሓት ጥያቄያቸውን ከመመለስ ይልቅ ‘የተምቤን ህዝብ ከተነሳ ለስልጣን አደጋ ይሆናል’ በሚል ምክንያት የተቃውሞው አስተባባሪዎች በማስፈራራት ከተምቤን መሬት ለቀው እንዲጠፉ ተደረገ። አስተባባሪዎቹን በማባረር የተቀረውን በሃይል መጨፍለቅ ጀመሩ። የተቃውሞው መንፈስ አዳከሙት። አሁን የተምቤን ህዝብ አንድነት ፈጥሮ እንዳይታገላቸው በመስጋት ህዝቡ ይከፋፍሉታል፣ እርስበርሱ እንዳይተማመን ያደርጉታል። ጥያቄ ያነሳ ካለ ከሀገሩ ያባሩታል።
የተቃውሞ ሰልፉ ይመሩት ከነበሩ ወላይ ጫዓ አንዱና ዋነኛው ነበር። ወላይ ጫዓ ከተምቤን ተባሮ በሌላ ቦታ ለብዙ ግዜ ከተቀመጠ በኋላ አሁን ወደ ዓብይ ዓዲ ተመልሷል (በዓብይ ዓዲ ከተማ በ አካል አግኝቼው ነበር)። በ1996 ዓም የትግራይ ክልል ርእሰ መስተዳድር የነበሩ አለቃ ፀጋይ በርሀ ወላይ ጫዓን በጣም ይፈሩት እንደነበር የዓብይ ዓዲ ኗሪዎች አጫውተውኛል። አለቃ ፀጋይ ወላይ ጫዓን ከመፍራታቸው የተነሳ የተቃውሞ ሐሳብ የሚያነሳ ሁሉ ‘ወላይ ጫዓ’ ይሉ እንደነበር ነው የተነገረኝ።
በ1996 ዓም የተጠየቁ የመብራትና የዉኃ ችግሮች እስካሁን ድረስ ተገቢ መልስ አልተሰጣቸውም ብለው ኗሪዎች ያምናሉ። የአስፋልት መንገዱ ጉዳይ ግን ከአስር ዓመት በኋላ አሁን ተጀምሯል (ይቅርታ ከተመጀመረ ዓመታት ተቆጠረዋል፣ ግን እስካሁን ድረስ 30% እንኳን አልተጠናቀቀም)። በመንገዱ ጥራትም ብዙ ጥያቄዎች ይነሳሉ። የመንገዱ የተወሰነ አካል ይሰራሉ፤ ከወራት በኋላ ደግሞ ችግር አለበት ተብሎ አስፋልቱ ሳይጨርሱ መጠገን ይጀምራሉ።
በዓብይ ዓዲ ከተማ ከፍተኛ የመልካም አስተዳደር ችግር አለ። ህዝቡ የመንግስት አገልግሎት በአግባቡ አያገኝም። ‘የራሳችን ሰዎች ያስተዳድሩን’ የሚል ጥያቄ አለ። ህወሓት ይህንን ጥያቄ ለመመለስ የዓብይ ዓዲ ህዝብ በተምቤን ተወላጆች እንዲተዳደር ለማድረግ ሞክሮ አልተሳካለትም። የዓብይ ዓዲ ከተማ ከንቲባ ለመምረጥ ሦስት የተለያዩ የተምቤን ተወላጆች ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር። የተምቤን ተወላጆቹ ግን ቅድመ ሁኔታ አስቀመጡ። የተምቤን ተወላጆቹ ‘የከንቲባነት ስራ ለመስራት ከተፈለገ ህዝቡን በቅንነት ለማገልገል ነፃነቱ ሊሰጠን ይገባል! የህዝቡ ጥያቄዎች ለመመለስ ሊፈቀድልን ይገባል’ የሚሉ ቅድመ ሁኔታዎች አቀረቡ። ህወሓቶች አልተቀበሉትም። በተፈጠረው አለመግባባት ምክንያት የዓብይ ዓዲ ከተማ ለብዙ ግዜ ያለ ከንቲባ ቆየች። አሁን ሲጨንቃቸው ግን በሙያው ያልሰለጠነ የከተማው የፖሊስ አዛዥ የነበረ የከተማው ከንቲባ እንዲሆን መርጠውታል።
ዓረና መድረክ ዕለተ እሁድ ከተምቤን ህዝብ ጋር ለመወያየት ዕቅድ ይዞ ስለነበር ከአራት ቀናት በፊት ነበር ቅስቀሳ የጀመረው። ከዚህ በፊት በሌሎች አከባቢዎች ባደረግናቸው ቅስቀሳዎች (በቅስቀስ ወቅት) የተምቤን ያህል በአስተዳዳሪዎች ተፅዕኖ አልደረሰብንም። የዓረና መድረክ የተምቤን የቅስቀሳ ቡድን በየጭላ፣ ወርቅ አምባ፣ ሀገረሰላምና ዓብይ ዓዲ ታስረዋል። ይህ የተደረገው የቅስቀሳ ሂደቱ ለማሰናከል ነበር።
የተምቤን አስተዳዳሪዎች (በሌሎች አከባቢዎችም እንደሚደረግ ሁሉ) ህዝብ በስብሰባው እንዳይሳተፍ ለማፈን በየዘርፉና በየአከባቢው በዕለተ እሁድ የራሳቸው ስብሰባ ጠርተዋል። በተለየ ሁኔታ የዓብይ ዓዲ መምህራን ኮሌጅ መምህራንና ተማሪዎች በዓረና ስብሰባ እንዳይካፈሉ ለማድረግ ባልተለመደ መልኩ ለእሁድ ስብሰባ ተጠሩ። የኮለጁ አባላት ብዙ ጥያቄዎች አሉዋቸው።
እሁድ ጠዋት የማዘጋጃቤት ሰራተኞች፣ የፖሊስ አዛዦች፣ የዓብይ ዓዲ ከተማ የእያንዳንዱ ቀጠና ተጠሪ ካድሬዎች በስብሰባው አደራሽ በር አከባቢ ተቀመጡ። ለስብሰባ የመጣ ሰው እነሱን አይቶ ሰግቶ እንዲመለስ ለማድረግ ወይም በስብሰባው የተሳተፈ ሰው ለመመዝገብ ነበር የተቀምመጡት።
ህዝቡ ግን እነሱን ሳይፈራ በድፍረት ወደ አደራሹ መግባት ጀመረ። አደራሹ መልቶ ነበር ማለት ይቻላል። የተምቤን ስብሰባችን ለየት የሚያደርገው ህዝቡ ለመከልከል የተሰማሩ ካድሬዎች ራሳቸውም በአደራሹ ገብተው የስብሰባው ተካፋይ ሁነው፣ ጥያቄዎች መጠየቃቸውና መከራከራቸው ነበር። ካድሬዎቹም አመስግነናል (ከኛ ጋር መከራከር በመቻላቸው)። በስብሰባ ገብቶ የመከራከር ባህል ሊዳብር የሚገባ ነው።
ሞቅ ያለ ዉይይት ተደረገ። ደስ የሚል ነበር። ህዝቡ ስለሚደርሰው ችግር ተናገረ። ስለ የራስ አሉላ አባነጋ ትምህርትቤት ስያሜ መቀየር ያለው ቅሬታ ገለፀ። የተምቤን ህዝብ ለማዳከም ለሁለት መከፈሉ እንደሚቃወም አስረዳን። ደጉዓ ተምቤን ወረዳ ከዋናው ተምቤን ተነጥሎ ወደ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን እንዲሆን መወሰኑ ይታወቃል። ተምቤን ራሱ የቻለ ዞን መሆን እንዳለበትም ተነስቷል። ተምቤን ዞን እንዲሆን ሕግም ይፈቅድለታል። ምክንያቱም አንድ አከባቢ አራትና ከዛ በላይ ወረዳዎች ካሉት የዞንነት ደረጃ የማግኘት ዕድል አለው። ተምቤን አራት ወረዳዎች አሉት፤ (1) ደጉዓ ተምቤን፣ (2) ጣንቋ አበርገለ፣ (3) ቆላ ተምቤንና (4) ዓብይ ዓዲ።
የተምቤን ህዝብ ለውጥ ፈላጊ ነው። ለለውጥ የሚመራው የተደራጀ ሃይል ብቻ ነው የሚያስፈልገው። የህወሓት ሰዎችም የተምቤንን ህዝብ በተለየ ሁኔታ ይፈሩታል። በተምቤን ህዝብ አጠራር ህወሓት ‘ቂመኛ’ ነው። ቂም ይዞ ነው ተምቤኖችን የሚበድለው።
ባጠቃላይ የተምቤን ስብሰባችን ተስፋ ሰጪ ነበር። በድልም ተጠናቋል። ቀጣዩ ጉዟችን ወደ ዓዲ ግራት ወይ ሽሬ ይሆናል።

የኢህአዴግ አዲሱ አሰላለፍ ፪ – ከተመስገን ደሳለኝ (ጋዜጠኛ)

በድህረ-መለስ ኢትዮጵያ የፖለቲካው ሥልጣን በስርዓቱ ልሂቃን መካከል ከሚደረገው የኃይል መተናነቅ አንጻር፣ ዛሬም ከመፈራረቅ ጣጣው የተላቀቀ የማይመስልባቸው ምልክቶች መታየታቸው እንደቀጠለ ነው፡፡ ከአራት ወር በፊት በዚህ መፅሄት ላይ ‹‹አዲሱ የኢህአዴግ አሰላለፍ›› በሚል ባቀረብኩት ፅሁፍ በገዥው ፓርቲ ውስጥ ተፈጥሮ ከነበረው ክፍፍል የትኛው ቡድን የበለጠ ጉልበት አግኝቶ በአሸናፊነት መውጣት እንደቻለ ከገለፅኩ በኋላ ፅሁፉን የቋጨሁት እንዲህ በማለት ነበር፡- ‹‹የፓርቲው የታሪክ ድርሳን እንደሚነግረን ‹ይሆናሉ› የተባሉት ተቀልብሰው፣ ባልተጠበቁ ሁነቶች (የኃይል መገለባበጥ ተከስቶ) ፖለቲካው የሚመራበት አጋጣሚ ሊፈጠር የሚችልበት ዕድል ሊኖር እንደሚችልም መዘንጋት አያስፈልግም፡፡››
እነሆ በዚህ ፅሁፍ ደግሞ በቅርቡ በተጨባጭ የታዩትን አዳዲስ ኩነቶች እና ይህንኑ ተከትለው ሊመጡ ይችላሉ ብዬ የምገምታቸውን ‹የቢሆን ዕድሎች› (Scenarios) ለማየት እሞክራለሁ፡፡
ሰላም የራቀው-ኢህአዴግ 
በግንባሩ አባል ድርጅቶች መካከል ዛሬም ድረስ ሙሉ በሙሉ የተረጋጋ ፖለቲካ አልሰፈነም፤ የዚህ ዋነኛ ምክንያቱ ደግሞ፣ ቁልፍ የሥልጣን ቦታዎችን ጠቅልሎ ይዞ በነበረው በቀድሞ ሊቀ-መንበሩ ህልፈት ሳቢያ የተፈጠረው የአመራር ክፍተት እና እርሱን ሊተካ የሚችል መሪ ማግኘት ባለመቻሉ ይመስለኛል፡፡ እንዲህ አይነት አጋጣሚዎችም በተለይ እንደ ኢትዮጵያ ባለ ከሕግ ይልቅ የጠመንጃ ኃይልና የግለሰብ አምባገነናዊነት በገነነበት ሀገር ‹የማይገመቱ ክስተቶች› (Unpredictable Event) ማምጣታቸው የሚጠበቅ ነው፡፡
የሆነው ሆኖ በዚህ አጀንዳ ለመመልከት የምሞክረው ጉዳይ፣ በአሁኑ ጊዜ ሀገር እየመራ ያለው ኃይል ለሁለት የተከፈለ ቢሆንም፣ በአንፃራዊነት በጥምር የሚሰራ መሆኑን በማስረገጥ ነው፡፡ የእነዚህ ሁለት ቡድኖች የጉልበት ምንጭም የታጠቀውን ኃይል በመቆጣጠር እና የፖለቲካውን ሥልጣን በመያዝ ላይ የተመሰረተ ነው፤ ይኸውም ሠራዊቱ እና የደህንነት መስሪያ ቤቱ ሙሉ በሙሉ በህወሓት ሰዎች ሲንቀሳቀሱ፣ ፖለቲካውን ደግሞ የብአዴን መሪዎች፣ ከተወሰኑ የኦህዴድና ደህአዴን የአመራር አባላት ጋር ተባብረው መያዛቸውን የሚያሳዩ ምልክቶች መኖራቸው ነው፡፡
የህወሓት ኃይል
ህወሓት የቀድሞው ፍፁማዊ የበላይነቱን ለመመለስ ዋና ችግር የሆነበት በውስጡ ለተፈጠረው መከፋፈል እስካሁን መፍትሄው ተለይቶ አለመታወቁ ነው፤ ከዚህ ቀደም በዚሁ መፅሄት፣ አንዱ ኃይል የተሻለ ጉልበት በማግኘቱ ሌላኛውን (እነአዜብ መስፍንን ጨምሮ አባይ ወልዱና ቴዎድሮስ ሀጎስን የመሳሰሉ ከፍተኛ ካድሬዎች የተሰባሰቡበትን) በመብለጥ በተወሰነ ደረጃም ቢሆን እንቅስቃሴያቸውን መገደቡ ተሳክቶለት እንደነበረ ማስነበቤ ይታወሳል፡፡ ይህ ክፍፍል ምንም እንኳ እንደ 1993ቱ ከፓርቲ እስከ ማስወጣት የሚደርስ አለመሆኑ ቢታወቅም፣ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል እና ጌታቸው አሰፋ የተሰለፉበት ቡድን ተፅእኖ ፈጣሪ ሆኖ መውጣት ችሏል፤ ይህም ሆኖ ውስጥ ውስጡን የሚገመደው ተንኮልም ሆነ ሽኩቻ ገና መቋጫ አለማግኘቱ ግልፅ ነው፡፡
በዚህ ፅሁፍ ጠመንጃ የታጠቀውን ክፍል ‹የህወሓት ኃይል› እያልኩ የምገልፀበት ዓብይ ምክንያት፣ በጄነራል ሳሞራ የኑስ ኤታ ማዦር ሹምነት የሚመራው የመከላከያ ሠራዊት እና በማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ጌታቸው አሰፋ ስር ያለው የደህንነት ኃይል ለሚደግፉት ቡድን መጠናከር እያበረከቱት ያለውን አስተዋፅኦ ከግምት በመክተት ነው፡፡ ሁለቱም ሰዎች ለመለስ ፍፁም ታማኝ የነበሩ ቢሆንም፣ ከህልፈቱ በኋላ እንደእርሱ ተጭኖ ሊቆጣጠራቸው የሚችል ጉልበታም ህወሓትን ጨምሮ በሁሉም የግንባሩ አባል ፓርቲ ውስጥ አለመኖሩ፣ በፖለቲካው ‹ቼዝ› የ‹ዘመነ መሳፍንቱ›ን ሚካኤል ስሁል አይነት ሚና እንዲጫወቱ አስችሏቸዋል፤ ሁለቱም ከስራቸው የነበሩትንና ‹ስልጣን ሊጋፉ ይችላሉ› ብለው የጠረጠሯቸውን ባልደረቦቻቸውን አስቀድሞ ገለል ማድረጉ ከሞላ ጎደል የተሳካላቸው ይመስለኛል፡፡
በተለይም ጌታቸው አሰፋ ከራሱ ወንበር አልፎ ከእነአዜብ መስፍንና አባይ ወልዱ ጋር በመተባበር አንድ ቀን በጠቅላላው የመንግስት የሥልጣን እርከን ላይ ‹ናቡቴ ሊሆን ይችላል› የሚል ስጋት ያሳደረበትን እና ‹መለስ ዜናዊ ሞት ባይቀድመው በእርሱ ቦታ ሊተካው ነበር› እየተባለ የሚነገርለትን የመረጃ ኃላፊ ወልደስላሴ ወልደሚካኤል በሙስና የሚወነጀልበትን መንገድ አመቻችቶ ለእስር ባይዳርገው ኖሮ ‹‹ለቁርስ ያሰቡንን…›› አይነት ታሪክ ራሱን መድገሙ አይቀሬ ነበር ብዬ አስባለሁ፡፡
ጄነራል ሳሞራ የኑስ በበኩሉ ተቀናቃኙ አድርጎ ይመለከታቸው የነበረው ሶስቱ ከፍተኛ መኮንኖች እንደ ወልደስላሴ ‹ፍንቀላ መሳይ ነገር ሊሞክሩ ይችላሉ› ተብለው አይደለም፡፡ የእነርሱ የመጀመሪያው ችግር ከወታደራዊ ዲሲፕሊን በማፈንገጥ አለቃቸውን አለማክበራቸው ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ ሳሞራ ‹በየትኛውም ምክንያት ከኃላፊነቴ ብነሳ የቆየ ፋይል አገላብጠው አደጋ ላይ ሊጥሉኝ ይችላሉ› በሚል ስለሚጠረጥራቸው ነው፡፡ እነዚህ መኮንኖች የሰሜን ዕዝ አዛዥ ሌፍተናንት ጄነራል ሰዓረ መኮንን፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ መልካም ግንኙነታቸው እንደቀድሞው እንዳልሆነ የሚነገረው የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሌፍተናንት ጄነራል አበባው ታደሰ እና የአየር ኃይሉ አዛዥ ሜጀር ጄነራል ሞላ ኃይለማርያም ናቸው፡፡ እናም ሰዓረ እና አበባው በቀጥታ ሠራዊት ከሚያዙበት ቦታ ተነስተው በመከላከያ ሚኒስትር ውስጥ በቢሮ ስራ ላይ ሲመደቡ፣ ሞላም ከነበረበት ኃላፊነት አኳያ ብዙም ይመጥነዋል የማይባል የቢሮ ስራ ተሰጥቶታል፤ በእርሱም ቦታ ሜጀር ጄነራል አደም መሀመድ ተተክቷል፡፡ የሳሞራ እና የሞላ ልዩነት በመለስ ዘመንም በአደባባይ የሚታወቅ እንደነበረ ሰምቻለሁ፡፡
ለጉዳዩ ቅርብ ከሆነ የመረጃ ምንጬ እንዳረጋገጥኩት የአስተዳደር ዘይቤውን በማኪያቬሊያዊ አስተሳሰብ (ከፋፍለህ ግዛ) የሚያሳልጠው የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ፣ ለሞላ ትዕዛዝ የሚሰጠውም ሆነ ማንኛውንም ጉዳይ በተመለከተ የሚያነጋግረው የዕዝ ተዋረዱን ጠብቆ በኤታ ማዦሩ በኩል ሳይሆን፣ በቀጥታ በመገናኘት መሆኑ፣ አየር ኃይሉን ከመከላከያ ሚኒስቴር የተገነጠለ አስመስሎት ነበር፤ ይህ ሁኔታም በሁለቱ መኮንኖች መካከል ያለው ግንኙነት የሥልጣን ተዋረድን የጠበቀ እንዳይሆን በማሰናከሉ በጄነራሉ ላይ ደፍሮ የማይናገረው ቅሬታ ሊያሳድርበት ችሏል፤ ከመለስ ህልፈት በኋላም ሳሞራ ሂደቱን ለማስተካከል መሞከሩ፣ በየግምገማው ላይ እስከ መዘላለፍ አድርሷቸው ነበር (በነገራችን ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ወደ ሥልጣን ከመጣ በኋላ እንደ ጦር ኃይሎች አዛዥነቱ፣ ከጄነራሎቹ ጋር መደበኛ /Official/ በሆነ መንገድ ትውውቅ አላደረገም፤ እነዚህ ሶስት ጄነራሎችም ለዚህ አይነቱ የአሰራር መፋለስ ጥፋተኛ የሚያደርጉት አለቃቸውን ሳሞራ የኑስን ነው፤ ከምንጮቼ እንደሰማሁት ከሆነም ከወራት በፊት ኃይለማርያም ደሳለኝ በተገኘበት ‹ጎልፍ ክለብ› በሚባለው የጄነራሎቹ መዝናኛ በተዘጋጀ ፕሮግራም ማጠናቀቂያ ላይ ሳሞራ አንድ ጠረጴዛ ከበው ወደ
ተቀመጡት እነዚህ ጄነራሎች ጋ ሄዶ ‹ኑ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ላስተዋውቃችሁ› ማለቱን እና እነርሱም በጥያቄው ተበሳጭተው ቢሮ ያላቸው መሆኑን እና ክብራቸውን በሚመጥን መልኩ መተዋወቅ እንደነበረባቸው በኃይለ ቃል መመለሳቸውን ነው)
የሳሞራ የኑስ እና ሰዓረ መኮንን መነቋቆር ከትግሉ ዘመን ጀምሮ የመጣ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ሆኖም ሳሞራ ከማንም በላይ የሚፎካከረውም ሆነ መበለጥ የማይፈልገው በሟቹ ጄነራል ኃየሎም አርአያ እንደ ነበር የቀድሞ ጓዶቻቸው ያስታውሳሉ፤ ይህ ሁኔታ ዛሬም ድረስ በስራ ላይ ያሉ መኮንኖችን ‹የሳሞራ› ወይም ‹የኃየሎም ተከታይ› በማለት መከፋፈሉ በጓዶቻቸው እና በፓርቲው መሪዎች አካባቢ የሚታወቅ ነው፡፡ ሌላው ቀርቶ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ለማዕረግ እድገት የተለየ የድጋፍ አስተያየት የሚያገኙት በዛን ዘመን ‹የሳሞራ ተከታይ› የሚባሉት እየተመረጡ እንደነበረ በወሬ ደረጃ ይናፈሳል (በነገራችን ላይ ጄነራል ሳሞራ ከጤንነት ጋር በተያያዘ በአጭር ጊዜ ውስጥ በጡረታ ይሰናበታል በተባለበት ጉዳይ ላይ እያንገራገረ እንደሆነ ከመከላከያ አካባቢ የሚወጡ መረጃዎች ያመላክታሉ፤ እንደ ምክንያት የሚጠቀሰው ደግሞ ‹ለእኔ በጎ አመለካከት የላቸውም› በሚል የሚጠራጠራቸው ጄነራሎች በሥራ ላይ እያሉ የእሱ ጡረታ መውጣት ከመስሪያ ቤቱ ጋር ተያይዘው የሚነሱ ያደሩ የሙስና ካርዶች የሚመዘዙበትን ዕድል ያሰፋዋል የሚል ነው፤ በተለይም በግዙፍ የቢዝነስ ሥራዎች ላይ በታላቅ ተፎካካሪነት እየተሳተፈ የሚገኘው ‹መቴክ› ምንም እንኳ ማረጋገጫዎች ባይቀርቡበትም በመከላከያ ሥር ከነበረበት ዘመን እስከ 2002 ዓ.ም መጨረሻ ድረስ ከግዥዎች ጋር ተያይዘው የሚነሱ በርካታ የሙስና ሁኔታዎች በመኖራቸው ነው፡፡
መቴክ ካለፉት አራት ዓመታት ጀምሮ በአዋጅ የልማት ድርጅት እንዲሆን ቢደረግም፣ ዛሬም ዳይሬክተሩ የሠራዊቱ አባል ብርጋዴር ጄነራል ክንፈ ሲሆን፣ መከላከያ ደሞዝ የሚከፍላቸው ጥቂት የማይባሉ ሠራተኞችንም እንዳቀፈ ይታወቃል፡፡ እናም ሳሞራ ሃሳቡ ከተሳካለት ለጥቂት ተጨማሪ ዓመታት በሥልጣኑ ላይ ሲቀጥል፣ አሊያም ‹የወንድ በር› ለማግኘት በትግሉ ዘመን የእርሱ ሰልጣኝ እንደነበረ የሚነገርለትን እና በቅርቡ ብቸኛው ከሜጀር ወደ ሌፍተናት ጄነራል ማዕረግ ያደገው ዮሀንስ ገ/መስቀል እንዲተካው መንገድ ጠረጋውን ማመቻቸቱ ትኩረት ሰጥቶ የሚሰራበት ጉዳይ ይመስለኛል)
ይህም ሆኖ የተኮረኮርን ያህል የምንስቀው ጄነራል ሳሞራ የኑስ በቅርቡ ለታተመው ‹‹ህብረ ብሔር›› መፅሄት ሙስና ለሠራዊቱ አደገኛ መሆኑን እንዲህ በማለት መግለፁን ስናነብ ነው፡-
‹‹ሙስና ሠራዊቱን ሊያበላሸው ይችላል፡፡ ሙስና ፀረ-ልማት ነው፤ ሠራዊቱን ሊበትነው እና ሕዝባዊ ባህሪውን እንዲያጠፋ ሊያደርገው ይችላል፤ አንድ ሠራዊት ሠራዊት ነው የሚባለው እንደ ወታደር እንደ አንድ አካል ሲያስብ እንጂ ለግሉ ሲያስብ አይደለም፡፡ …በአጠቃላይ (ሠራዊቱ) በዚህ ነው የሚፈርሰው፡፡››
መቼም ጄነራሉ ይህንን የተናገረው እራሱን ጨምሮ በርካታ ከፍተኛ መኮንኖች እንደ እንግሊዝ ንጉሳውያን ቤተሰቦች በተንጣለለ ቪላ ቤት ውስጥ፣ የተቀማጠለ ኑሮ መኖራቸውን ረስቶት አይመስለኝም፤ ‹ይህ የተንዛዛ ወጪያቸውም የሚሸፈነው ከደሞዛቸው በሚያገኙት ገቢ ነው› ብሎ ቧልት መሳይ ክርክር ሊያመጣ አይችልም፡፡ ይሁንና እታች ያለው ጭቁን የኢትዮጵያ ሠራዊት ምንም እንኳ በአለቆቹ ‹ቴክሳስ›ነት ላይ ለመቆጣት ባይደፍርም፣ እንደማንኛውም ዜጋ ለኑሮ ውድነትና አስከፊ ድህነት የተጋለጠ መሆኑን መካድ አይቻልም፡፡
የሆነው ሆኖ ተሰሚነታቸው እየተቀዛቀዘ የመጣው አቦይ ስብሃት ነጋ ከወራት በፊት ለ‹‹ውራይና›› መፅሔት ‹‹ህወሓት ትንሳኤ ያስፈልገዋል›› በማለት የሰጡትን ምክር ተከትሎ፣ ጄነራል ሳሞራ እና አቶ ጌታቸው አሰፋ፣ ከድርጅቱ ምክትል ሊቀ-መንበር ዶ/ር ደብረፅዮን ጋር በመተባበር ህወሓትን ለማጠናከር እና በፖለቲካ ውስጥ የነበረውን የአንበሳውን ድርሻ ለማስከበር (ጉዳዩን ከለጠጥነው ደግሞ ‹ለማስመለስ›) እየሰሩ እንደሆነ ይነገራል (በነገራችን ላይ የሳሞራና ጌታቸው ተፅእኖ መጨመሩን ለመረዳት፣ መከላከያ ‹አገራዊ ጥቅምንና ደህንነትን ለመከላከል› በሚል ‹እጅግ ጥብቅ ሚስጢር ብሎ የሰየማቸውን የሰው ኃይል ፕሮፋይል፣ የሒሳብ መዝገቦችና ሰነዶች እና የክፍያ ማስረጃዎች ለማንም አካል እንዳይገለፅ› የሚያስችለውን ስልጣን፣ ደህንነቱ ደግሞ በስራ ላይ የሚፈፅማቸው ማንኛውም ጉዳዮች ወደፊት በህግ እንዳይጠይቅ እስከ መከላከል የሚደርሰውን አዲስ የተዘጋጁትን አዋጆች ማንበቡ በቂ ነው፡፡ በርግጥ እነዚህ ባለሥልጣናት እንዲህ ባለ ተመሳሳይ መንገድ እንዲጓዙ ያስተሳሰራቸው አንዱ ጉዳይ ‹ህወሓት ተዳከመ፣ ተሸነፈ፣ አበቃለት…› የሚለው የካድሬውና ደጋፊው ቁጭት እንጂ ወትሮም መልካም ግንኙነት ኖሯቸው አይመስለኝም)
ለማንኛውም በጥቅሉ ሲታይ የህወሓት ትልቁ ችግር ተብሎ በአመራር አባላቱ የሚጠቀሰው ‹በዚህ ወቅት ወደፊት መምጣት የሚችሉ ጠንካራ ቴክኖክራቶችን አለማፍራቱ፣ ሁለንተናዊ ድጋፍ የሚያደርግለትን የታጠቀውን ኃይል ተጠቅሞ የፖለቲካ ልዩነቱን ጨፍልቆ በአሸናፊነት ይዞት መውጣት የሚችል መሪ እንዳይኖረው አደረገ› የሚል ነው፡፡ በርካታ የላይኛ እና የታችኛው ካድሬዎችም ‹ለእንዲህ አይነቱ ክፉ ጊዜ ድርጅቱ የሚያስፈልገው፣ በትግሉ ዘመን ልምድ ያካበተ ታጋይ ብቻ ነው› የሚል አቋም እንዳላቸው ይነገራል፡፡ ስርዓቱ ከሚያራምደው ርዕዮተ-ዓለም ጋር ጠንካራ ትውውቅ ያሌለውን እና የትግሉን ዘመን በአሜሪካን ሀገር በማሳለፉ ‹የምዕራባውያን ድጋፍ አለው› ለሚባለው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም የሚሰጡት ዝቅተኛ አመለካከት መግፍኤም ይኸው ይመስለኛል፡፡
ለነገሩ እርሱም ቢሆን በጠንካራ ድርጅታዊ ዲሲፕሊን ካለመታነፁ እና መሰል ጉዳዮች ጋር በሚያያዙ ምክንያቶች ለትንፋሽ ጊዜ የማይሰጠውን የድርጅት ሊቀ-መንበርነትንም ሆነ የጠቅላይ ሚኒስትርነት ቦታ የሚወራውን ያህል ይፈልገዋል ብሎ መደምደሙ አስቸጋሪ ነው ብዬ አስባለሁ፤ ከዚህ ይልቅ በተፈጥሮ ከታደለው የተግባቢነት ባህሪው አኳያ እንደ ሕዝብ ግንኙነት የመሳሰለ ብዙም የማያጨናንቅ ሥራን ይመርጣል፡፡ ለዚህም ይመስለኛል ከሰለጠነበት ሙያ ጋር የቀጥታ ተያያዥነት ያለውን የጤና ጥበቃ ሚኒስትር በሚመራበት ዘመን፣ ከውጭ ሀገር በርካታ የተቋረጡ ፈንዶችን እንደገና ለማስለቀቅ መቻሉ እንደ ታላቅ ስኬት የሚወራለት፤ አልፎ ተርፎም ‹ወባን ከኢትዮጵያ ምድር ለማጥፋት ብርቱ ትግል አደረገ› ተብሎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሳይቀር እስከ መሸለም የደረሰው እዚህ መስሪያ ቤት እያለ እንደሆነም ይታወቃል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ በፓርቲውም ሆነ በመንግስት አስተዳደር ከህወሓት ሰዎች ትልቁን ስልጣን የያዘው ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ከምዕራባውያን ጋር የቆየ ቀረቤታ እንዳለው ሰምቻለሁ፤ እንደሚታወሰው ደብረፅዮን ከክፍፍሉ በፊት (የደህንነት መስሪያ ቤቱ እንዲህ እንደ ዛሬው እጅግ ዘመናዊ በሆነው የቻይና ቴክኖሎጂ ሳይጥለቀለቅ) ከነበረው ከፍተኛ የሥልጣን ቦታ ላይ ተነስቶ፣ ቁልቁል ወርዶ በሁመራ በአንድ ዞን እንዲሰራ የተመደበው (ሁላችንም ስንገምት እንደነበረው) የአንጃው አባል ወይም ደጋፊ ሆኖ አይደለም፤ ይልቁንም የእነስዬ-ተወልደ ቡድን በመባል የሚታወቀው (‹አፈንጋጩ› ኃይል) ደብረፅዮንን በሲ.አይ.ኤ እና ሞሳድ ወኪልነት የመክሰሱ ጉዳይ የድርጅቱን በርካታ አባላት ቀልብ በመሳቡ፣ መለስ ይህንን ተከትሎ ከሚመጣበት አደጋ ራሱን ለመከላከል የወሰደው እርምጃ በመሆኑ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት እስከ 1998 ዓ.ም መጨረሻ ድረስ በሁመራና ራያ አካባቢዎች በዞን ደረጃ ለማገልገል ተገዷል፡፡ እናም እርሱን የምዕራቡ ዓለም ፊት-አውራሪ አሜሪካና ሸሪኮቿ ወዳጅ ነው የሚያስብለው በቀድሞ መስሪያ ቤቱ በኩል በነበረው ግንኙነት ይመስለኛል።
የፖለቲካውን መዘውር የጨበጠው ኃይል
የዚህ ቡድን አምበል እንደ ድርጅት ብአዴን ቢሆንም፣ በቋሚ ተሰላፊነት ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ አባዱላ ገመዳ፣ ሙክታር ከድር እና ሬድዋን ሁሴን እንደሚገኙበት ይነገራል፤ ለብአዴን ‹በተሻለ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ላይ ለመገኘቱ መደላድል ፈጥሮለታል› የሚለውን ሙግት ምክንያታዊ የሚያደርገው ደግሞ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፖሊሲና ጥናት ምርምር አማካሪ በረከት ስምዖን፣ የኢህአዴግን የካድሬ ማሰልጠኛ ማዕከል በዳይሬክተርነት የሚመራው አዲሱ ለገሰ፣ ደርቦ ይዞት የነበረውን የትምህርት ሚኒስትርነት ለሽፈራው ደሳለኝ በመልቀቅ፣ በአሁኑ ወቅት ሙሉ የስራ ጊዜውን በግንባሩ ፅ/ቤት የሚያውለው ም/ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን እና የፌዴሬሽን ም/ቤት አፈ-ጉባኤው ካሳ ተክለብርሃን የያዙት ሥልጣን ያለውን የፖለቲካ አቅም መመዘኑ ይመስለኛል፡፡ በመከላከያ ሠራዊቱ ውስጥም ከሳሞራ አንድ እርከን ዝቅ ባለ ሥልጣን ከሌሎች ሁለት ጄነራሎች ጋር የሚገኘው አበባው ታደሰ እንደ ቀድሞው በዕዝ አዛዥነቱ (በቀጥታ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ወታደሮችን ማንቀሳቀስ የሚችልበት) ላይ ቢሆን ኖሮ ጥንካሬውን የተሟላ ማድረጉ አይቀሬ እንደነበረ መገመት ይቻላል፡፡
ከዚህ ሌላ ለእነበረከት ቡድን ተጨማሪ የፖለቲካ ጉልበት እየሆናቸው ያለው የኃይለማርያም ደሳለኝ ቢሮ እና በአባዱላ ገመዳ አፈ-ጉባኤነት የሚመራው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ነው፡፡ አባዱላ፣ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሪፖርት ለማቅረብም ሆነ ለመታዘዝ ፍቃደኛ ያልሆኑ አንዳንድ ባለስልጣናት፣ በውስጥ መስመር በሚተላለፍለት ‹ጥቅሻ› በምክር ቤቱ በኩል የሚመለከተው የቋሚ ኮሚቴ አባላት አስጠርቶ የተሰጠውን ኃላፊነት የሚገመግምበት ስልት እየተገበረ ነው፡፡ በአናቱም ምን ጊዜም የሳምንቱን የሥራ መጨረሻ ቀን አርብን ጠብቆ የሚሰበሰበው የሚኒስትሮች ም/ቤትን ከሞላ ጎደል ይህ ቡድን እየጠቀመበት ይመስለኛል፡፡ በርግጥ ሚኒስትሮቹ በሚገናኙበት አብዛኛውን ሰዓት ሳይግባቡ (በጭቅጭቅ) ማሳለፋቸው ይነገራል፤ የዚህ ምክንያቱ ደግሞ በአቶ መለስ ዘመን ም/ቤቱ የሚሰበሰበው የተለያዩ አጀንዳዎችን ለማቅረብ እና በቀረበው አጀንዳ ላይ ለመከራከር (ለመመካከር) ሳይሆን፣ መለስ ወስኖ የመጣበትን የሥራ ድርሻ ተቀብሎ ለመበተንና ሪፖርት ለመስማት የነበረው አሰራር፣ ዛሬ ተቀይሮ በርካታ የተነቃቁ ሚኒስትሮች የየራሳቸው ሃሳብ ተቀባይነት እንዲያገኝ (ለማንፀባረቅ) የሚታገሉበት መድረክ ወደ መሆን በመሸጋገሩ ነው፡፡ ይህም ሁናቴ ዋናውን የመንግስት ሥራ የመገምገም እና የማስፈፀም አቅምን ሳይቀር ከሚኒስትሮች ም/ቤት ወደ ኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ አሻግሮታል የሚያስብሉ ማሳያዎች አሉ፡፡ ይሁንና በዚህስብሰባ ላይም ቢሆን ደፈር ብሎ ከበረከት ስምዖን እና አባይ ፀሀዬ የተሻለ አዳዲስ ሃሳብ የሚያቀርብ ባለሥልጣን እንደሌለ ሰምቻለሁ (በነገራችን ላይ ምክንያቱን ባላውቅም የጠቅላይ ሚኒስትሩ ‹የፖሊሲና ጥናት ምርምር አማካሪ› ተደርገው የተሾሙት በረከት ስምዖን፣ አባይ ፀሀዬ፣ ኩማ ደመቅሳ እና ዶ/ር ካሱ ኢላላ የሥራ ቦታቸው በጠቅላይ ሚኒስትሩ ፅ/ቤት ሳይሆን መገናኛ አካባቢ በሚገኝ አንድ ህንፃ ላይ ነው፡፡ የተሰጣቸው ኃላፊነት ኃይለማርያምን በቅርብ እንዲያገኙ ከማስገደዱ እና በግልፅ ከሚታወቀው የአማካሪ አስፈላጊነት አኳያ ካየነው ግን ግራ የሚያጋባ ይመስለኛል)
ጠቅላይ ሚኒስትሩ…
ኃይለማርያም ደሳለኝ ይህንን ቦታ ከያዘ በኋላ፣ ብዙዎች በስልጣኑ የማዘዝ አቅሙ ላይ አመኔታ እንደሌላቸው (አንጋፋ ታጋዮች እንደ ‹አሻንጉሊት› ሊጠቀሙበት እንደሚችሉ) ደጋግመው መግለፃቸው ይታወሳል፡፡ በግልባጩ ‹አፈንግጦ ለመውጣት መሞከሩ አይቀሬ ነው› የሚሉ ግምቶች ነበሩ፡፡ በርግጥ እነዚህ መላ-ምቶች ዛሬም ድረስ እልባት ባያገኙም፣ እዚህ ጋ ያልጠቀስኳቸው አንዳንድ ጉዳዮች ላይ ያሳያቸው ወጣ ያሉ አቋሞቹን ሳስተውል ግን፣ አሁን ያለው አሰላለፍ (የአነበረከት እና አባዱላ ፖለቲካዊ መጠናከር) ለእርሱም የተረፈው ይመስለኛል፡፡ እንዲሁም ከቤንች ማጂ የተባረሩ አማርኛ ተናጋሪዎችን አስመልክቶ በድርጅቱ ውስጥ ባልተለመደ መልኩ ‹አጥፊዎቹ ላይ እርምጃ እወስዳለሁ› ከማለት አንስቶ (በነገራችን ላይ በአማካሪ ብዛት እንዲከበብ ካደረገው ምክንያት አንዱ ጓዶቹ በዚህ ንግግሩ መበሳጨታቸው ነው) በቅርቡ ህወሓትን ለመሸምገል በተዘጋጀ መድረክ ላይ ‹ሁኔታዎች እንዲህ እየተካረሩ ከሄዱ ወደ ማሰሩ መግባታችን አይቀርም› በማለት ማስፈራራቱ እና በቴዎድሮስ አድህኖም የሶሻል ሚዲያ አጠቃቀም ላይ የመቆጣቱ ጉዳይ ድረስ የሚካተቱ እውነታዎች ሰውየው የራሱን መንገድ ለመከተል እየሞከረ መሆኑን ያሳያሉ ብዬ አስባለሁ፡፡
የሆነው ሆኖ እነዚህ ሁናቴዎች የፖለቲካውን ጉልበት ሙሉ በሙሉ በብአዴንና በተባባሪነት በጠቀስኳቸው የኦህዴድና ደህአዴን የአመራር አባላት አካባቢ ቢያከማቻቸውም፣ በማንኛውም ሰዓት ያሻውን ማድረግ የሚችለው የታጠቀው ኃይል ደግሞ ከህወሓት ጎን እንደተሰለፈ ይገኛል፡፡ መጪውን ጊዜም አዲስ ክስተት እንድንጠብቅ ገፊ ምክንያት ይህ አይነቱ የኃይል አሰላለፍ ይመስለኛል፡፡
ምን እንጠብቅ?
ከረጅሙ የፓርቲ ፖለቲካና መንግስታዊ መንገራገጮች በኋላ፣ የሁለቱንም የኃይል መሰረቶች ጠቅልሎ በመዳፉ ሥር የከተተው መለስ ዜናዊ በሞተ ማግስት ‹የኃይል መገዳደሮች ሊከሰቱ ይችላሉ› የሚለው የብዙዎቹ ግምት ነበር፤ ከወራት በፊት አስነብቤ በነበረው ከላይ በተጠቀሰው ፅሁፍም ግምቶቹ እውን መሆን እንደ ጀመሩ ማሳያዎች ማቅረቤ ይታወሳል፡፡ ኢህአዴግ ውስጥ ራሳቸውን ያቧደኑት ኃይሎች ዋነኛ ግብ ከሥልጣን የሚነሱ ጥቅሞችና አነስተኛ የየራሳቸው ፓርቲ ፍላጎቶች የፈጠሩት በመሆኑ፣ እንደ ሟቹ ደመ-ቀዝቃዛ አምባገነን አይነት በጠንካራ መዳፍ ሥር የሚያሰባስባቸው ባለመገኘቱ በየጊዜው የኃይል መሸጋሸጎች ሊከሰቱ እንዲችሉ አድርጓቸዋል፤ አሁንም እየተስተዋለ ያለው ይኸው እውነታ ነው፡፡ በዚህ አውድ ላይ ቆመን ሊፈጠሩ የሚችሉ የቢሆን ሃሳቦችን ስናስቀምጥም በጠረጴዛው ላይ የምናገኘው ሁለት ዕድሎችን ይመስለኛል፡፡
የመጀመሪያ ሲናሪዮ የሚሆነው ከላይ የጠቀስኩት ቡድንተኝነት እንዳለ ሊቀጥል ይችላል የሚል ነው፤ ይህም የሚሆንበት ምክንያት ባለኝ መረጃዎች መሰረት የፖለቲካውን መስመር የያዘው ቡድን መሪ አባላት፣ አሁን ያላቸውን መንግስታዊ ሥልጣን ጠብቀው መቆየትን መሰረታዊ መሰባሰቢያ አጀንዳ ማድረጋቸው ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የሳሞራና ጌታቸው ጥምረት ህወሓትን ወደ ቀደመው ዘመኑ ለመመለስ ቢሻም፣ ሊሄድበት የሚችልበት መንገድ አደገኛ መሆኑ (ወታደራዊ ላዕላይ መዋቅሩንና የደህንነት ኃይሉን ከመያዙ አኳያ) ሁኔታዎችን ባሉበት ይዞ መቀጠልን በትርፍ-ኪሳራ ስሌት የተሻለ አማራጭ አድርጎ ይወስደዋል ብዬ አስባለሁ፡፡
ሁለተኛው የቢሆን ዕድል፣ ዳግመኛ የኃይል መሸጋሸግ ሊፈጠር መቻሉ ነው፤ ሰዎቹ ጥቅመኛ በመሆናቸው የቋንቋ ተናጋሪነት ልዩነቶቻቸውንና የኋላ የመቆራቆስ ታሪኮቻቸውን ተሻግረው፣ አንዳቸው ከአንዳቸው ጋር ሌላ መልክ ያለው ስብስብ ሊፈጥሩ ይችሉ ይሆናል፤ ይህ አይነቱ አዲስ የኃይል አሰላለፍም፣ ከቀጣዩ ሀገራዊ ምርጫ በፊት በማይታወቀው ተሰዊና ሰዊ ሊጠናቀቅም ይችላል፡፡
በመጨረሻም ምንም ይፈጠር ምን፤ እኛን ሊያግባባን የሚገባው ጭብጥ፣ የትኛውም ቡድን በግንባሩ ውስጥ ቢነሳ፣ የማዕከላዊ መንግስቱን ህልውና ወደሚበታትን ሂደት መግባቱ ሊሰካለት አለመቻሉ ነው፤ ምክንያቱም በዚህ መልኩ ሄዶ የሚጣሉበትን ጠረጴዛ መስበሩ ምን እንደሚያስከትል ያውቁታልና ወደዚህ ምዕራፍ እንደማይሻገሩ አምናለሁ፡፡ ይሁንና ከፓርቲው ዝግነት እና ከፖለቲከኞቹ አቋም የለሽነት አንፃር አሁንም ሆነ በቀጣይ ጊዜያት ከማንም ግምት ውጪ ያሉ ክስተቶች እንደ ደራሽ ውሃ ድንገት ሳይታሰብ ግንባሩን ሊያተራምሱት ይችላሉ ብሎ መገመቱ አግባብ ይመስለኛል፡ ,,,,,,       / ዘሀበሻ/

Nelson Mandela Foundation Denies Israel Training Claim

Insists No Evidence Freedom Icon Interacted With Mossad
GETTY IMAGES
By Forward Staff – December 21, 2013, The Nelson Mandela Foundation has denied an explosive report that the South African freedom icon received training from Israeli agents in the early 1960s.
“(The foundation) has not located any evidence in Nelson Mandela’s private archive…that he interacted with an Israeli operative during his tour of African countries in that year,” the group said in a statement to the South African Press Association.
Haaretz first reported last week that top secret Israeli files suggest that Mandela was trained by Mossad agents during a stop in Ethiopia in 1962, as he began efforts to launch the armed struggle against the white-led apartheid regime in South Africa.
It said Mandela, who died on Dec. 5, apparently underwent weapons training by Mossad agents in Ethiopia in 1962 without the Israeli secret service knowing his true identity. They attributed their report to “an intriguing secret letter lodged in the Israeli state archives”.
The letter supposedly said Mandela was instructed in the use of weapons and sabotage techniques and was encouraged to develop Zionist sympathies.
Any contact between Mandela and Israeli agents would have been controversial in South Africa, where Mandela’s African National Congress forged a close alliance with the Palestinians and regularly slammed Israel for propping up the white government.
The foundation emphatically denies any such contact between Mandela and Israeli agents occured.
“In 1962 Mandela received military training from Algerian freedom fighters in Morocco and from the Ethiopian Riot Battalion at Kolfe outside Addis Ababa, before returning to South Africa in July 1962.
“In 2009 the Nelson Mandela Foundation’s senior researcher travelled to Ethiopia and interviewed the surviving men who assisted in Mandela’s training and no evidence emerged of an Israeli connection,” read the statement.

Witness for Ethiopia’s Semayawi (Blue) Party By Prof. Al Mariam

Why I support Semayawi party as a political party
In the days leading up to my speech at the first Semayawi (Blue) Party town hall meeting in Arlington, VA, just outside of Washington, D.C., on December 15, I was peppered with all sorts of questions. The one recurrent question revolved around my unreserved support for Semayawi Party after so many years of staying neutral and unaligned with any Ethiopian political party or group.
As I explained in my interview on ethiotube.com, my support for Semayawi Party should be viewed as an expression of my total confidence in the power of Ethiopia’s young people to change the destiny of their country and their readiness to struggle for peaceful change. The percentage of Ethiopia’s population under the age of 35 today is 70 percent. The vast majority of the victims of human rights violations in Ethiopia today are young people. The targets of political persecution and harassment, arbitrary arrests and detentions, torture, abuse and maltreatment in the prisons are largely young people. Young Ethiopians are disproportionately impacted by pandemic unemployment and lack of educational and economic opportunities.
Here I record my “testimony” as a “witness” for Semayawi Party to affirm my unshakeable belief that Ethiopia’s youth shall overcome and rise above the dirty politics of ethnicity, pernicious religious animosity and audacious political mendacity to build a shining city upon the hill called the “Beloved Ethiopian Community.” This I believe to be the fixed historical destiny of Ethiopia’s young people today.
My “testimony” reveals only my personal views and opinions, and in no way reflects on any past, present or future official or unofficial position of Semayawi Party, its leadership or members. I have no role whatsoever in Semayawi Party. The only role I have is the one I have proudly conferred upon myself: “#1 Fan of Semayawi Party”.  My steadfast “testimony” here may raise eyebrows. I have heard some “criticism” that by showing strong support for Semayawi Party I am in fact playing a game of dividing society by age not unlike the divisive ethnic game of the regime in power. I will let the young people be the judge of that. As George Orwell said, “In times of universal deceit, telling the truth will be a revolutionary act.” I consider my “testimony” on behalf of Semayawi Party to be a “revolutionary act” against all of the political deceit, hypocrisy and chicanery in all around I see.
Why am I am the #1 cheerleader of Semayawi Party?
First, I support Semayawi Party because it is a political party of young people, for  young people and by young people. It is a party that aspires to represent the interests of the vast majority of Ethiopians. I underscore the fact that 70 percent of Ethiopia’s population today is under age 35. (Life expectancy in Ethiopia is between 49 and 59 years depending on the data source.) Ethiopia’s Cheetah (young) Generation needs a party of its own to represent the majority of Ethiopians. The Cheetahs need to speak up, stand up and wo/man up for themselves. Only they can determine their country’s destiny and their own.
The political parties of Hippos (my generation), by Hippos and for Hippos are simply out of sync with the dreams, aspirations, ambitions and passions of Ethiopia’s restless Cheetahs. We Ethiopian Hippos simply do not understand our Cheetahs. So many of us have been rolling in the mud of ethnic and killil (“bantustan” or “kililistan”) politics, muck of communalism and  sludge of historical grievances for so long that we have become completely paralyzed. Ethiopia’s Cheetahs do not want to be prisoners of antiquated identity politics nor do they want to walk around with the millstone of  the past tied around their necks. They want to break free and choose their own destiny and invent their own Ethiopia.
As a not-so-loyal member of the “Order of Ethiopian Hippos”, I had great difficulty accepting the fact that Ethiopia’s  Cheetahs are very different from Ethiopian Hippos. I had great difficulty accepting the fact that the time has come for me and my Hippo Generation to  pass on the baton, stand aside and serve as humble water carriers for the restless Cheetahs. That is why I transformed myself from a Hippo to a Chee-Hippo, a transformation I documented in my commentary “Rise of the Chee-Hippo Generation”.
Second, I am deeply concerned about the future of Ethiopia’s youth. As I noted a few years ago, “The wretched conditions of Ethiopia’s youth point to the fact that they are a ticking demographic time bomb. The evidence of youth frustration, discontent, disillusionment and discouragement by the protracted economic crisis, lack of economic opportunities and political repression is manifest, overwhelming and irrefutable. The yearning of youth for freedom and change is self-evident. The only question is whether the country’s youth will seek change through increased militancy or by other peaceful means….” I believe Semayawi Party will play a significant role in channeling youth frustration into peaceful transformation in Ethiopia.
Third, I wholeheartedly believe in youth power. Youth idealism and enthusiasm have the power to change hearts, minds and nations. Youth power is more powerful than all the guns, tanks and war planes in the world. The American civil rights movement was carried on the backs of young people. The vast majority of the leaders and activists were young people. Dr. Martin Luther King was 26 years old when he organized the nonviolent protests in Birmingham, Alabama. By the time John Lewis was 23 years old, he had been jailed 24 times and beaten to a pulp on so many occasions that he does not remember. On May 6, 1963, over 2000 African American high school, junior high and even elementary school students were jailed for protesting discrimination in Birmingham.
Young Americans stopped the war in Vietnam. The free speech movement that began at a California university transformed free speech and academic freedom in the United States for good. Barack Obama would not have been elected president without the youth vote. Youth have also played a decisive role in the peaceful struggle to bring down communist tyrannies and more recently entrenched dictatorships in North Africa and the Middle East. The tyrants in the seat of power in Ethiopia today were “revolutionaries” in their youth fighting against imperial autocracy and military dictatorship. In their old age, they have become the very evil they fought to remove.
I believe in the power of Ethiopia’s youth who have long played their part to bring about a democratic society and paid enormous sacrifices for decades. In 2005, the regime in power in Ethiopia today massacred hundreds of young people in cold blood in the streets and jailed tens of thousands. (I joined the human rights struggle in Ethiopia shocked and outraged by that crime against humanity.) Even today, Ethiopia’s young people continue to pay for democracy, freedom and human rights with their blood, sweat and tears. Ethiopia’s best and brightest have been persecuted, prosecuted, jailed, brutalized and  silenced. At the top of the list are Birtukan Midekssa, Eskinder Nega, Andualem Aragie, Reeyot Alemu, Bekele Gerba, Abubekar Ahmed, Woubshet Taye, Olbana Lelisa, Ahmedin Jebel, Ahmed Mustafa, Temesgen Desalegn, the late Yenesew Gebre and countless others.
Last but not least, I am in broad agreement with the Semayawi Party Program. It is a well-thought out and practical program that can effectively address the multifaceted problems of the country. In my special area of concern focusing on the administration of justice, human rights and enforcement of the rule of law, I find the Party’s program to be particularly robust. The Party supports a fully independent and competent judiciary completely insulated from political pressure and interference. Judges shall have lifetime tenure subject to impeachable offenses. The Party supports the establishment of a Constitutional Court with full judicial review powers. The Party pledges to abide by and respect all international treaties and conventions to which Ethiopia is a signatory.  The Party is committed to the full protection of individual rights, including the right to free speech and religion. There shall be strict separation of religion and state. The Party opposes any censorship of the press and curtailment of the activities of  civic organizations and associations. The Party’s program  emphatically states that the loyalty of the armed and security forces is to the country’s Constitution, and not to a political party, ethnic group, region or any other entity. The Party’s platform on economic, political, social and cultural issues is equally impressive.
Why I support Semayawi Party as a  movement and true voice of Ethiopia’s Cheetah (young) Generation
It is my opinion that Semayawi Party is much more than a political organization concerned with winning votes to hold political office. I would find nothing unique in Semayawi Party if it were merely an organization preparing itself for mundane elections and parliamentary seats. In a country where there are over 80 “registered parties” (the vast majority of which are nominal ethnic parties) and the ruling “party” wins “elections” by 99.6 percent, it would be absurd to create another party such as Semayawi to compete for a miniscule less than one-half percent of the votes. That is why I believe Semayawi Party is indeed a movement of young people, by young people and for young people in Ethiopia.
I regard “Semayawi Party Movement” to be an organizational mechanism to articulate the dreams and ideals of Ethiopia’s young people about the country they want to build for themselves and pass on to the next generation. As a Movement, Semayawi Party serves in various capacities. It is as an “educational” institution enlightening young Ethiopians about the history, traditions and cultures of their diverse country. It teaches young Ethiopians that they are the proud descendants of patriots who united as one indivisible people to beat and route a mighty invading European army. Unlike today, Ethiopia was once the pride of all Africans and black people throughout the world. The Movement aims to regain Ethiopia’s pride in the community of nations.
I share in “Semayawi Party Movement’s” core values. Semayawi Party believes in peaceful nonviolent struggle against tyranny and injustice. I champion peaceful nonviolent struggle against tyranny and injustice anywhere in the world. Semayawi Party believes in the transformative power of Ethiopia’s youth. A compilation of all of the weekly commentaries I have written on Ethiopian (and African) youth over the past 7 years could easily form  a book length apologia (defense) of the transformative power of Ethiopia’s youth. My slogan has always been and remains, “Ethiopia’s youth united can never be defeated. Power to Ethiopia’s youth!”
Semayawi Party Movement has only one goal: Creating the “Beloved Ethiopian Community” in the same vein that Dr. Martin Luther King dreamed of creating his “Beloved Community” in his long struggle for human and civil rights in America. Dr. King taught, “The end of nonviolent social change is reconciliation; the end is redemption; the end is the creation of the Beloved Community. It is this type of spirit and this type of love that can transform opponents into friends.” I believe the “Beloved Ethiopian Community” shall soon rise from the ashes of the kililistan (bantustan) Ethiopia has become.
The foundation for Semayawi Party Movement’s “Beloved Ethiopian Community” is unity, peace and hope. A “Beloved Ethiopian Community” is united by its humanity and is immune from destruction by the divisive forces of ethnicity and communalism. It is a Community that strives to establish equality, equity and accountability. The “Beloved Ethiopian Community” is a society at peace with itself and its neighbors. I believe Semayawi Party aspires to invent a new society free from ethnic bigotry and hatred; free from fear and loathing and free from tyranny and repression. Semayawi Party aims to build a Community where all Ethiopians –  rich and poor, young and old, men and women, Christian and Muslim — are free to dream, free to think, free to speak, to write and to listen; free to worship without interference; free to innovate; free to act and free to be free. I believe Semayawi Party Movement will use peace creatively to transform enmity, animosity and bellicosity in Ethiopian society into amity, cordiality and comity. I believe the Movement will choose  dialogue over diatribe, negotiation over negation, harmony over discord and use principles that elevate humanity to defeat brutality, criminality and intolerance.
The “Beloved Ethiopian community” is a “land of hope and dreams.” It is a community where young people could look forward to equal opportunity, equal justice and equal rights. It is a community where Ethiopia’s youth can freely share their common hopes and dreams. I have faith in Ethiopian youth’s  “audacity of hope”.
Let us ask what we can do for Semayawi Party  
I encourage and plead with all Ethiopians, particularly those in my Hippo Generation, to stand up and be counted on the side of Semayawi Party Movement. I know many have legitimate questions, doubts and skepticisms based on unpleasant past experiences as they consider lending their support. I have been asked, “How can we trust these young and inexperienced leaders to do the right thing?” I answer back, “How well did our experienced and trusted Hippo leaders do?”
Surviving under the most vicious dictatorship in Africa brings out the very best in many young people. Semayawi Party Movement leaders, members and supporters have shown us what they are made of: courage, integrity, discipline, maturity, bravery, honor, fortitude, creativity, humility, idealism and self-sacrifice. They have been arrested, jailed and beaten. They did not stop their peaceful struggle. What more sacrifice must they make before they can convince us that they deserve our full support? They are young and passionate; and they have all of the experience they need to continue their peaceful struggle for change.
Some have asked me for assurances that Semayawi Party is not a front for the regime or other hidden forces. All I can say is that if Semayawi Party Movement leaders, members and supporters are regime lackeys, then so are Prof. Mesfin Woldemariam, Prof. Yacob Hailemariam, and to mention in passing, Prof. Al Mariam. If the regime is so clever as to use Semayawi Party to broadcast its commitment to the rule of law and democratic governance, I am all for it. If today the regime released all political prisoners (including those held in secret prisons), repealed its oppressive laws, stopped massive human rights violations and stealing elections, I will be the first one to go out in the street and sing them praises. It is not about the people in power; it’s about the evil done by people in power.
I have been told that nearly all Ethiopian political organizations that have been launched in the past decade or so  have eventually failed. I have been asked, “How can you be sure Semayawi Party will not fail?” There are no guarantees Semayawi Party will not fail. If it fails, it will not be for lack of willpower, enthusiasm, dedication and sacrifice by Semayawi Party leaders and members. It will be mainly because of lack of support, lack of good will, lack of confidence, lack of generosity and  lack of material and moral support from their compatriots inside Ethiopia and in the Diaspora. If they should fail and we feel arrogant enough to wag an index finger at them and say, “I told you so!”, let us not forget that three fingers will be pointing at us silently. Nelson Mandela pleaded, “Do not judge me by my successes, judge me by how many times I fell down and got back up again.” Let us judge Semayawi Party not by the chances that it will slip and fall in the future but by how many times it is able to get back up after it falls, with our help and support.
Some have expressed concern to me that their financial contributions could be abused as has happened so many times in the past. They want assurances of strict accountability and transparency. They ask me, “How can we be sure Semayawi Party will not abuse our trust as others have in the past?”
The Semayawi Party Support Group in North America is a gathering of the most dynamic and disciplined group of young Ethiopians I have had the privilege to know and work with. These young Ethiopians have committed significant resources out of their own pockets to support the cause of Ethiopian youth. They are young professionals and private businessmen and women representing the ethnic, gender and cultural diversity of Ethiopia. They understand and appreciate the values of  accountability and transparency. They relate with each other on the basis of honesty and integrity. For my money, I have no problems taking chances with them because I am convinced they will not let me down! I have full faith in the integrity of Ethiopia’s young people; that is my guarantee they will do the right thing.
In my speech at the first town hall meeting for Semayawi Party on December 15, I told the audience that Yilikal Getnet, the chairman of Semayawi Party, did not come to the United States to beg for support or panhandle for nickels and dimes.  Semayawi Party does not want a handout or charity from us in North America. Yilikal came to America to share with us the trials and tribulations of his party, the challenges they face, their humble accomplishments under a brutal dictatorship and the dreams and hopes of Ethiopia’s young people for a free and democratic Ethiopia.
I believe that in all of the town hall meetings scheduled for Semayawi Party in the U.S., we should receive Yilikal, Semayawi Party members and supporters as heroes of a growing youth movement for peaceful change in Ethiopia. We must use the town hall meetings to celebrate not only the individual acts of heroism of youth leaders like Yilikal, Eskinder, Andualem, Reeyot and so many others but also to rejoice in the raw heroism of those young people demonstrating in the streets crying out “Anleyayim! Anleyayim!” (We will remain united!) or ‘Ethiopia, Agarachin! Ethiopia, Agerachin! (Ethiopia, our country!). (I always get a lump in my throat when I hear them chanting “Anleyayim! Agerachin, Ethiopia!)
For me, Yilikal’s presence in our midst as the leader of Semayawi Party is a reminder that the young people who were massacred in 2005 peacefully demonstrating a stolen election did not die in vain. He is a live witness that the peaceful struggle of those massacred for free and fair elections and the rule of law continues no matter what. So the question for us is: What can we do for Semayawy Party Movement? A better question is how do we show our appreciation, respect and admiration to our young heroes — the fallen ones, the ones in jail, the ones being tortured, those facing daily harassment, persecution and humiliation?
Semayawi Party Movement needs all the support they can get. They need our moral support. They need our encouragement; they need to know we have confidence in them. Most of all, they need material support to undertake their youth outreach, education and awareness programs. They need material support to expand and sustain their organizational presence throughout the country. They need material support to maintain a robust legal defense fund. They need our material support to stand up to the richest, most corrupt and ruthless dictatorship on the African continent.
Our financial gift to Semayawi Party Movement is merely a token of our appreciation and an indication that we are with them as long as they keep their peaceful struggle for justice, equality, democracy and human rights. Our gift to Semayawi Party Movement is an investment in an Ethiopia at peace with itself. We give so that the next generation of Ethiopians will live in a new Ethiopia unburdened by our mistakes and ignorance. It is our individual and social responsibility to support our young people. If we don’t support our children – all of the young people in Ethiopia – who will?
Let us ask what Semayawi Party can do for us
In August 2012, I asked, “Who can save Ethiopia?” in a commentary titled, “Cheetahs, Hippos and Saving Ethiopia”. I pleaded with Ethiopia’s youth to lead  a national dialogue in search of a path to peaceful change. I have repeated my appeal to them in various ways since then.
I call upon Semayawi Party Movement to continue and intensify the reconciliation dialogue among themselves and launch a reconciliation dialogue in the broader Ethiopian youth community. I believe the dialogue on national reconciliation in Ethiopia must begin within Ethiopia’s youth communities. Ethiopia’s Cheetah’s must empower themselves, create their own political and social space, set their own agendas and begin multifaceted dialogues on their country’s transition from dictatorship to democracy through dialogue.  They must develop their own awareness campaigns and facilitate vital conversations among youth communities cutting across language, religion, ethnicity, gender, region and so on. Their dialogues must be based on the principles of openness, truth and commitment to democracy, freedom and human rights. They must dialogue without fear or loathing, but with respect and civility.  Above all, the Cheetahs must “own” the dialogue process. At a gathering of Cheetahs, Hippos should be seen and not heard very much; welcomed and encouraged to observe Cheetahs in action. The Cheetahs must keep a sharp eye on wily Hippos who are very skillful in manipulating youth. They should learn not to fall in the trap young people fell during the “Arab Spring”. The cunning Hippos outplayed, outmaneuvered and marginalized them in the end.
I believe reconciliation dialogues should begin among activist youth in informal and spontaneous settings. For instance, such dialogues could initially take place among like-minded activist youth at the neighborhood and village level. Activist youth could undertake an assessment of their capabilities, potentials, opportunities and obstacles in setting up and managing a community-based informal reconciliation youth dialogues. Youth activist could focus on creating broader youth awareness and involvement in the dialogue process by utilizing existing organizations, institutions, associations and  forums.
Reconciliation dialogue involves not only talking but also actively listening to each other. Youth from Ethiopia’s multiethnic society have much to learn from each other and build upon the strengths of their diversity. Ethiopia’s Cheetahs should also learn from the mistakes of the Hippo Generation and the experiences of youths of other nations. I urge Ethiopia’s Cheetahs to be principled in their reconciliation dialogues. They should always disagree without being disagreeable. Disagreeing on issues should not mean becoming mortal enemies. Civility in dialogue, though lacking among Hippos, is essential for Cheetahs.
Silence of our…?
“In times of universal deceit,” silence speaks louder than words and pictures. Dr. Martin Luther King said, “In the end, we will remember not the words of our enemies, but the silence of our friends.” As I end this commentary, I must speak up against the “silence” of our “friends” because sometimes silence is more eloquent than speech. When the leader of Ethiopia’s youth party came to Washington, D.C. for the very first time and spoke to a capacity crowd of Ethiopians unseen in the past several years, the Voice of America (VOA) was conspicuously absent. VOA did not send a single reporter to cover the event. I do not know why the VOA decided to absent itself from the event. I do  know that the Semayawi Party event was no less important than the variety of Ethiopian sports, cultural, academic and community events and even book signings  VOA routinely covers on weekdays and weekends in around Washington, D.C. Perhaps for the VOA Semayawi Party and Ethiopia’s youth are a simple issue of mind over matter; VOA does not mind and Ethiopia’s youth don’t matter.
I want VOA to know that when they faced the slings and arrows of  Meles Zenawi, when Zenawi outrageously accused them of “promoting genocide in Ethiopia”, I stood up for them. I defended their integrity, professionalism and impartiality time and again. I expected the VOA to attend the Semayawi Party event and report on the proceedings with the integrity, professionalism and impartiality they have shown in the past. Perhaps Ethiopians will begin to ask whether the Voice of America is now the Silence of America (SOA). We will continue to listen to the SOA, but not in silence.
No more silence; let us shout out and show our support for Semayawi Party Movement
Let us be silent no more. Let us proudly proclaim our support for Semayawi Party Movement. Let’s stand tall and proud with them. Let’s show them we appreciate and support their peaceful and nonviolent struggle for change. Let’s assure them that no matter how long it takes to walk the long road to freedom, we will be with them. They will be victorious in the end. Let’s show Semayawi Party Movement we love them!
Ethiopia’s youth united can never be defeated. Power to Ethiopia’s Youth!