Saturday 25 October 2014

ምጽዓት የዝርፊያው ፉክክር የት ለመድረስ ነው?


goat-and-sheep
“በግዞትም ቤት አደባባይ ታስሮ ሳለ የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ ኤርምያስ መጣ፡– ሂድ ለኢትዮጵያዊውም ለአቤሜሌክ እንዲህ በለው፤ — የእሥራኤል አምላክ የሠራዊት ጌታ ፣ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤- እነሆ ለበጎነት ሳይሆን ለክፋት ቃሌን በዚህች ከተማ ላይ አመጣለሁ፤ በዚያም ቀን በፊትህ ይፈጸማል፤ በዚያ ቀን አድንሃለሁ፤ ይላል እግዚአብሔር፤ በምትፈራቸው ሰዎች እጅ አልሰጥህም፤ ፈጽሜ አድንሃለሁ፤ ነፍስህም እንደምርኮ ትሆንልሃለች እንጂ በሰይፍ አትወድቅም፤ በበእኔ ታምነሃልና ይላል እግዚአብሔር፡፡” ትንቢተ ኤርምያስ 39/15-18
ኑዛዜ ኤርምያስን አነበብሁ፤ጉድ ነው! አንድ የማውቀውን ነገር አረጋግጥሁ፤ ብዙ የማላውቃቸው ነገሮችን አወቅሁ፤ የማውቀው ነገር ሂሳብ የተማረ ሰው ምን ጊዜም ጭፍን ሎሌ መሆን የማይችል መሆኑን ነው፤ ሂሳብ የተማረውን ሰው ለጭፍን ሎሌነት የሚቀጥረው ሰው ግን አንጎሉ የፈረጠ ነው፡፡
የማላውቃቸው ነገሮች ዝርፊያ በየፈርጁ! በቃሊቲ ወህኒ ቤት የትምህርት ቤት የነበረ ሕንጻ ወደ እስር ቤት መለወጡን አይቼ ነበር፤ አሁን ደግሞ የሕዝብ ትምህርት ቤት ለግለሰብ መሸጡን አወቅሁ፤ ጡንቻ ነው እንጂ ትምህርት ምን ዋጋ አለው! ይህ ሁሉ ዝርፊያ፣ ይህ ሁሉ ወንጀል ሲፈጸም ሌላው ሁሉ ጮሆ አቤት ለማለት እንኳን የማይደፍር ሆኖ ነው ወይስ የሕግ አስከባሪ በአገሩ ጠፍቶ ነው? ድፍረቱን አጥፍተውት ከሆነ በከበደ ሚካኤል ብእር ፋሺስቱ የተናገረው ልክ ነበር ማለት ነው፤–
መሬት የሁሉ ነች ባለቤት የላትም!
ኃይለኛ እየሄደ ያስገብራል የትም፤
መሬት ባለቤት ከሌላት ሰዎች አገር የላቸውም ማለት ነው፤ አገር የሌላቸው ሰዎች ዶላር ይዞ ለመጣ ቤታቸውንና መሬታቸውን እንዲያስረክቡ ይገደዳሉ፤ ሕገ መንግሥቱ መሬት የሕዝብና የመንግሥት ነው ስለሚል ባለዶላር ወይም ባለሀብት ሕዝብ የሚለውን ይተካል።
ኑዛዜ ኤርምያስን ያነበበ የወያኔ ባለሥልጣኖችን ራቁታቸውን ያያቸዋል፤ ካልዋሸ ራሱንም ራቁቱን ቆሞ ያየዋል፤ ከዚህ በፊት ብዙ ጊዜ ደጋግሜ እንዳልሁት ጨቋኝና ተጨቋኝ ተደጋጋፊዎች ናቸው፤ አንዱ ያላንዱ አይኖርም፤ በኑዛዜ ኤርምያስ ላይ ጎልቶ ለሚታየው የጨቋኞቹ ቆራጥነትና ጭካኔ ጉልበቱን ከየት አገኙት ቢባል መልሱ ቀላል ነው፤ ከተጨቋኞቹ ተንጋልሎ ጭቆናን ከመቀበል ችሎታ ነው፤ ድፍረታቸውን አደንቃለሁ፤ ድፍረታቸው ወደወንበሩ ስቧቸው ወጡበትና (ተቀመጡበት እንዳልል አልተመቻቸውም፤) ዘመኑ የፍርሃት፣  እንቅልፍ አጥቶ የመባነን፣ የመደናበር ሆኖባቸዋል፤ የፍርሃት በሽታ ዓይንን ይሰውራል፤ ጆሮን ይደፍናል፤ አቅምን እንዳያውቁ ያደርጋል፤ በዚህ ሁሉ ምክንያት ከማይችሉት ጋር ያላትማል።
ምጽዓት የሚል ግጥም አለኝ፤ ትዝ አለኝ!
ባሳብ ባሕር ዘፍቆ የሰው ልጅ ሲጨነቅ፣
ሃይማኖት ሲራባ ፍልስፍና ሲረቅ፣
ነፍስ እምነትን አጥታ፣ መንምና በችጋር፣
እውነቱ ሲያሳፍር፣ ሲያስጠላ፣ ሲያስመርር፣
ኃይል ክፋት ሲሆን የደካሞች ጭነት፣
ፍቅር ጥምቡን ጥሎ ሲገዛ እንደኩበት፣
ፍርሃት ትእግስት ሆኖ ድንቁርና ኩራት፣
ውርደትም ትሕትና ጮሌነትም እውቀት፣
ትምህርትም ጌጥ ሆነ ያውም የተውሶ፣
ስንፍናም ጨዋነት ሰውነት ረክሶ፣
ማተብ ክርስትና ነጭ ጥምጥም ክህነት፣
ሀብት ብልጽግና ምቾት ትልቅነት፣
ምኞት ተስፋ ሆኖ መቃብርም ኑሮ፣
እንጉርጉሮው ዘፈን፣ ዘፈኑ እንጉርጉሮ፣
ባዳ ሆነ ዘመድ ባለቤቱ እንግዳ፣
ሆድም አምላክ ሆነ አውሬውም ለማዳ፣
ገንዘብ ዳኛ ሲሆን ወንጀል ከሳሽ ሆኖ፣
ግብዝነት ደላው ጽድቅ ተኮንኖ!
ወጣትነት ጫጨ እርጅና እየለማ፣
የኋሊት መገስገስ የጊዜው ዓላማ!
ከራስ በላይ ነፋስ ትልቁ ሃይማኖት፣
ዘረፋን ሲያውጀው ቂም ሲያስረግዝ ጥቃት፣
ዓይን አያይም አሉ፤ ጆሮም አያዳምጥ!
ተለጉሞ አንደበት ሁሉም ይዞታል ምጥ!
በቁንጣን በስካር ጥቂቶች ሲንሩ፣
ብዙዎቹ ደግሞ በረሃብ መንምነው በቁንጫ ሲያርሩ.
የደሀ እንባ ሲጎርፍ መሬቱ ሲሸበር፣
ፍትሕ በሌለው ፍርድ ሚዛኑ ሲሰበር፣
ዝብርቅርቁ ወጣ!
ህይወት ትርጉም አጣ!
ኧረ የት ነው ጉዞው? ዓላማው ምንድን ነው?
ቀድመው የሄዱትን ምነው አናያቸው!
የት ገቡ? የት ጠፉ? ፋና እንኳን አይታይ፤
ብልጭ የሚል የለ፤ ከመሬት ከሰማይ!
መንገዱ ጠበበ ትርምስምሱ በዛ፤
እሪታው ኡኡታው ቀለጠ እንደዋዛ፤
መሬቱም ዓየሩም በክፋት ጠነዛ፤
ጥላቻና ቂሙ በሰፊው ተነዛ፤
እምቢልታው ሲጣራ፣ ነጋሪት ሲያገሳ፣
የአለው ሁሉ ሞቶ የሞተው ሲነሣ፣
ምጽዓት መድረሱ ነው፤ ሊስተካከል ነው ፍርድ፤
በግና ፍየሉ ሊለዩ በገሀድ!
የሚጠየቅ ሰው ቢኖር አንድ ቀላል ጥያቄ መጠየቅ እፈልግ ነበር፡- የዝርፊያው ፉክክር የት ለመድረስ ነው? በአንድ ቤተ ክርስቲያን ወይም መስጊድ ጓሮ ሁለት ሜትር በአንድ ሜትር ክፍል የሬሳ ቤት ለማሠራት? አይ ሰው!
ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
መስከረም 2007

ለቅድስት ቤተ-ክርስቲያን መልካም ሥራ የሚሠሩ ማኅበራትን ለማፍረስ መሞከር ቅድስት ቤተ-ክርስቲያንን ለማፍረስ እንደመሞከር ይቆጠራል


  • 284
     
    Share
መግለጫ ፎቶ
ጥቅምት 10 ቀን 2007 ዓ.ም.
ቁጥር : 10102014/0038
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን
ለቅድስት ቤተ-ክርስቲያን መልካም ሥራ የሚሠሩ ማኅበራትን ለማፍረስ መሞከር ቅድስት ቤተ-ክርስቲያንን ለማፍረስ እንደመሞከር  ይቆጠራል::
ለቅድስት ቤተ-ክርስቲያናችን ሕልውና ዘወትር በትጋት በማገልገል ላይ የሚገኘውን ማኅበረ-ቅዱሳንን ለማፍረስ እየተካሔደ ያለውን እንቅስቃሴ በመቃወም ከዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን እምነት ተከታዮች አንድነት የወጣ መግለጫ
“ነገር ግን ሐሰተኞች ነቢያት ደግሞ በሕዝቡ መካከል ነበሩ እንዲሁም በመካከላችሁ ደግሞ ሐሰተኞች አስተማሪዎች ይሆናሉ:: እነርሱም የዋጃቸውን ጌታ እንኳ ክደው የሚፈጥንን ጥፋት በራሳቸው ላይ እየሳቡ የሚያጠፋ ኑፋቄን አሹልከው ያገባሉ ብዙዎችም በመዳራታቸው ይከተሏቸዋል:: በእነርሱም ጠንቅ የእውነት መንገድ ይሰደባል:: ገንዘብንም በመመኘት በተፈጠረ ነገር ይረቡባችኋል ፍርዳቸውም ከጥንት ጀምሮ አይዘገይም ጥፋታቸውም አይዘገይም::” ፪ኛ ጴጥሮስ  ፪ ፥ ፩ – ፫

ጥንታዊት ታሪካዊትና ሐዋርያዊት የሆነችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከተመሰረተችበት ጊዜ አንስቶ ፈተና ርቋት አያውቅም:: ለዘመናት በተለያዩ ኃይሎች የተለያዩ ፈተናዎችን ስታስተናግድ የቆየች ሲሆን ሁሉንም በጠባቂዋ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ተቋቁማ ካለንበት ጊዜ ደርሳለች:: አሁንም በውስጥና በውጪ ጠላቶቿ ፈተና እየተፈራረቀባት ትገኛለች:: በተለይም ኢሕአዴግ በትረ ሥልጣኑን ከተቆጣጠረበት ጊዜ ጀምሮ በመንግሥት የሚደርስባት ጫናና ተጽእኖ እጅግ እየበረታ የመጣ ሲሆን በአማኞቿ ላይ የሚፈጸመው ስቃይና እንግልት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ነው:: ጉዳዩን በጥልቀት ለሚመረምር ሰው የቤተ ክርስቲያኒቱ የውጪና የውስጥ ጠላቶች ከረጅም ጊዜ ጀምሮ የሚደክሙበትን ቤተ ክርስቲያኒቱን የማሽመድመድና ከተቻለም የማፍረስ ሕልም ተግባራዊ ለማድረግ የሚሰራ ይመስላል:: ሆኖም እዚህ ላይ መረዳት የሚያስፈልገው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የተመሰረተችው በክርስቶስ ደም በመሆኑ ማንም ሊያፈርሳት አይችልም:: ይህንንም ለማወቅ የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ ፲፮ ፥ ፲፰ ማንበብ ያስፈልጋል:: ከታሪክም እንደምንረዳው በግራኝ መሐመድና ዮዲት ጉዲትም ብዙ ደክመው ቤተ_ክርስቲያኒቱን ማጥፋት እንዳልቻሉ ወደኋላ ሄዶ ታሪክን መመርመር ይገባል:: ይህንንም በማየት በቤተክርስቲያኒቱ ላይ የጥፋት በትሮቻቸውን ያነሱት ኃይሎች በሙሉ እጆቻቸውን ከቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ ማንሳት ጠቃሚ ነው እንመክራለን፥ ምክንያቱም ትግሉ ሲጥል እንጂ ሲታገል ከማይታየው ኃያል የምድርንና የሰማይ ፈጣሪ አምላክ ጋር ነውና::
በተደጋጋሚ እንደሚታየውና እንደሚሰማው የመንግስት ባለሥልጣናት ከእነርሱ በላይ የሁሉ ፈጣሪ ልዑል እግዚአብሔር መኖሩን ባለማመን ይሁን ባለማወቅ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖታችንና በተከታዮቿ ላይ ብዙ በደልና ግፍ ሲፈጽሙ ቅንጣት ያህል ሃፍረትና ፍርሃት አይሰማቸውም:: በሥልጣን ወንበሩ ላይ ያስቀመጣቸው ሁሉን ማድረግ የሚችል ኤልሻዳይ እግዚአብሔር መሆኑን ባለመገንዘብም ዘወትር በእብሪትና በትዕቢት የተሞሉ በርካታ ነገሮችን ሲናገሩ ይሰማሉ::
ለምሳሌ ያህል “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአማራ ዋሻ ናት”፤ “የአማራንና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንን አከርካሪ ሰብረናል” ፤ “አደረጃጀታችንን ስንጨርስ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ አማኞችም ማዕተብ እናስወልቃለን”፤ የሚሉትና የመሳሰሉት ይገኙባቸዋል:: ከሚፈጽሙት በደሎች መካከልም በልማት ሰበብ አብያተ ክርስቲያናትን ማፍረስ፤ ገዳማትን መዳፈር፤ ይዞታዎችን መንጠቅ ፤ በዘርና በጎሣ በማጋጨት ክርስቲያኖችን ማፈናቀል፣ ማስገደል፣ ማሰቃየት፣ ማንገላታት ወዘተ በጉልሕ የሚጠቀሱ ናቸው::
በ፪ኛ ጴጥሮስ  ፫ ፥ ፱ ላይ ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለተስፋ ቃሉ አይዘገይም፤ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሳል:: ተብሎ እንደተጻፈው የሰውን ጥፋት ሳይሆን መመለስ የሚፈልገው አምላክ ለእነዚህ በሕዝብና በሃይማኖታችን ላይ በደል ለሚፈጽሙ ባለሥልጣናት የንስሐ ጊዜ ቢሰጣቸውና ምልክትም ቢያሳያቸው ከክፉ ሥራቸው ከመመለስ ይልቅ ልባቸውን በማደንደንና ማን አለብን በማለት በጥፋት ላይ ጥፋት እየጨመሩ እንደ ፈርዖን ፈጣሪን በመገዳደር ላይ ይገኛሉ::
ሰሞኑንም በጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ በፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ሰብሳቢነት በተካሔደው ጉባዔ ላይ በተቀናጀ ሁኔታ በማኅበረ ቅዱሳን ላይ ሲሰነዘር የነበረው ውንጀላ በገሃድ የመንግሥትን ተልዕኮ ለማስፈጸም ታቅዶ የተጠራ ፖለቲካዊ ስብሰባ መሆኑን በስብሰባው ላይ የተንጸባረቁት ሃሳቦችና አስተያየቶች የሚያሳብቁ ነበሩ:: ለማስረጃም ያህል በስብሰባው ላይ ወቀሳ ሲያቀርቡ የሚሰሙት ካህናት ተብዬ ካድሬዎች በአብዛኛው ከመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ ይልቅ የፖለቲከኞቹን የአቶ መለስ ዜናዊንና የኢንጅነር ኃይሉ ሻውልን ንግግር እየጠቀሱና በዓለማችን ላይ በአሸባሪነታቸው የሚታወቁ ጽንፈኛ ድርጅቶችን ስም እያነሱ መናገራቸው አንዱ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ጉባዔው የተጠራው መዋቅር ሳይጠበቅና ጽሕፈት ቤታቸው ሳያውቀው መሆኑን የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ብጹዕ አቡነ ማቴዎስ መግለጻቸው ተጨማሪ ማስረጃ ነው::
ማኅበረ ቅዱሳን በእኛ ተቋምም ሆነ በሕዝበ ክርስቲያኑ ዘንድ የሚታወቀው፦
፩/ ገጠሪቱ ኢትዮጵያ ድረስ ዘልቆ በመግባት በችግር ምክንያት የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናትን ችግራቸውን አስወግዶ በማስከፈት፤
፪/ የቤተ ክርስቲያኒቱ የዕውቀት ምንጭ የሆኑትን የአብነት ት/ቤቶችን በመርዳት፤
፫/ የቤተ-ክርስቲያኒቱ ዕንቊ የሆኑ የአብነት መምህራንንና የአብነት ተማሪዎችን የሚያስፈልጋቸውን በማሟላት፤
፬/ በቤተ-ክርስቲያኒቱ ላይ የቅሰጣ ሥራ የሚሰሩ የመናፍቃን ተላላኪዎችንና የቤተ-ክርስቲያኒቱን ሀብት የሚመዘብሩ አማሳኞችን በማጋለጥ፤
፭/ ለሀገርና ለወገን በተለይም ለቤተ-ክርስቲያን ተቆርቋሪ የሆነ መንፈሳዊነትን የተላበሰ ትውልድ በማፍራት፤
፮/ በሀገራችን የሚገኙ ጥንታዊና ታሪካዊ ገዳማትን በመንከባከብና ምዕመናን የማያውቋቸውን እንዲያውቋቸው በማድረግ፤
፯/ በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃንና በሕትመት ሥርጭቶች ስብከተ ወንጌልን በማስፋፋት ሲሆን እነዚህን ዋና ዋናዎቹን ለአብነት ጠቀስን እንጂ ማኅበሩ ቀን ከሌሊት የሚተጋባቸው ብዙ በጎ ሥራዎች እንዳሉት ለማንም የተሰወረ አይደለም::
ታዲያ ይህ ሁሉ በጎ ሥራው እየታወቀ ፍጹም ፖለቲካዊ በሆነና ማመዛዘን በጎደለው መልኩ በእውነት ላይ ያልተመረኮዘ ትችት በማቅረብ ማህበሩን ለማፍረስ መሞከሩ ብዙ ምዕመናንን ያሳዘነና ያስቆጣ ከመሆኑም በላይ ከፓትርያርኩ ጀምሮ እስከ ካህናቱ ድረስ ለያዙት ሰማያዊ ሥልጣንና ኃላፊነት የማይታመኑ አድርጓቸዋል:: ከዚህ በተጨማሪ ፓትርያሪኩም ሆኑ ካህናቱ ሊረዱት የሚገባው ዋነኛው ነገር፣ ማኅበረ ቅዱሳንን እናፈርሳለን ሲሉ ወደ አንድ ሚሊዮን የሚጠጋውን አባላቱን እና የማኅበሩ ደጋፊ የሆኑትን ምዕመናን ከቅድስት ቤተ-ቤተክርስቲያናችን እንደመግፋት እና እንደማባረር እንደሚቆጠር ሊገነዘቡት ይገባል። መንግሥትም በተደጋጋሚ እንደሚያደርገው እራሱ ያዘጋጀውን ሕገ-መንግሥት በመጣስ በሃይማኖታችን ውስጥ ገብቶ ለማተራመስ እየዳከረ በመሆኑ ሕዝበ ክርስቲያኑን ወደ አልተፈለገ አመፅ እና እንቅስቃሴ ውስጥ እንዲገባ እየገፋው እንደሆነ ሊረዱት ይገባል::
ስለዚህ የኢሕአዴግ መንግሥት ይህንን ተገንዝቦ ለቤተ-ክርስቲያኒቱ በጎ ሥራ የሚሰራውንና ከፖለቲካ ነጻ የሆነውን ማኅበር በቤተ-ክርስቲያኒቱ ውስጥ በሰገሰጋቸው ካድሬዎቹ ተጠቅሞ በእጅ አዙር ለማፍረስ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ በአስቸኳይ እንዲያቆም እያሳሰብን፤ በማንኛውም መንገድ ማኅበሩን ለማፍረስ የሚካሔደው ስውር ደባ ቤተ-ክርስቲያኒቱን ለማፍረስ የሚካሔድ ተግባር አድርገን ስለምንቆጥረው በጽኑ የምናወግዘውና የምንቃወመው መሆኑን እንገልጻለን::
በመጨረሻም የቤተ-ክርስቲያኒቱ የበላይ ጠባቂ ቅዱስ ሲኖዶስም ሆነ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ክፍሎች ሁሉ ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት በማኅበሩ ላይ የሚካሔደውን ሤራ እንዲያስቆሙ ስንጠይቅ ሕዝበ ክርስቲያንም በሙሉ በኃይማኖታችን ላይ የሚሸረበውን ስውር ደባ በአጽንዖት እንዲቃወሙና ሁላችንም አንድ ሆነን ቅድስት ቤተ-ክርስቲያናችንን እንድንጠብቅ ጥሪያችንን እናቀርባለን::
ዓለም አቀፍ የኢ/ኦ/ተ/ቤተ- ክርስቲያን እምነት ተከታዮች አንድነት
ግልባጭ
  • ለቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት
  • ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ
  • ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ
  • ለብፁዕ አቡነ ማቴዎስ
  • ለብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ
  • ለብፁዓን አባቶች በሙሉ

Get well Dr. Craig Spencer (by Yilma Bekele)

October 25, 2014
by Yilma Bekele
What kind of place would the world be without people like Dr. Craig Spencer? Dr. Spencer is the medical doctor that is currently in New York Hospital with symptoms of the Ebola virus. Before his privacy was breached and his name associated with the dreaded virus Dr. Spencer was an International Emergency Medical (IEM) fellow at Columbia University in New York.Dr. Craig Spencer
According to his Profile in Emergency Physicians International, Dr. Spencer is a tireless advocate of introducing modern medical practices in Africa and is dedicated to helping local health providers get knowledge so they can help their people better. In May he was in the Democratic Republic of the Congo and Burundi helping Doctors and sharing his knowledge. Dr. Spencer is quoted to have said ‘sometimes even aspirin just weren’t available’
A University of Columbia educated medical doctor is someone we would refer to as a high achiever. It is a result of dedication, drive and plenty of sweat. It opens the door for whatever the individual feels is important in his/her life. Dr. Spencer choose to help those that are less fortunate and make his mark in life in a quiet way.
That is the reason he travelled to Guinea as part of Doctors without Borders team to treat Ebola patients and was back in Ney York October 17. Today our friend is in isolation getting the best treatment possible to overcome this virus that is killing Africans in the thousands. There is no question he would come out of this a better and stronger person for the prayer of all Africans is with this angel of a human being that showed up when we needed him most.
As an Ethiopian I feel kinship with the good doctor. I am more energized when I see such a human being that cares for those that are unable to help themselves due to different circumstances we all face in life. I envy his dedication and I promise myself to double my efforts to help the less fortunate.
My people face the same enemy like the Ebola virus. I am not trying to belittle the human catastrophe that is being faced by our African brothers and sisters. There is a saying in my country and it goes for a child whose mother has died or went to the market would cry the same, since the immediate absence is what matters. Our brethren in West Africa are dying in droves and the family is being decimated.
In our case for the last twenty years we have been dying a slow death in so many ways. Some are faced with lack of basic nutrition to sustain life and it is called famine. A lot are faced with the absence of hope and the constant dread of not knowing what tomorrow would bring. That results in untold mental anguish. Families fret because their children are left to roam the streets for lack of anything worthwhile to do. The little girls are forced to sell their body using the cover of darkness. The boys are left to poison their mind and body with drugs to numb the spirit caused by boredom and lack of drive.
Families are forced to sell their valuable cattle, personal belongings to send their children to the Middle East hoping they will be able to make something for themselves. A very minuscule achieve that goal while the vast majority suffer in silence unable to return due to shame and but forced to stay by unscrupulous Arab slave owners.
Yes it is true Ebola is fast and merciless. Watching the human toll in West Africa is a lesson in how fragile the human existence is. The whole world is in shock but a few dedicated individuals like Dr. Spencer rush to where danger awaits and offer their services. There was no financial gain, no fame and no recognition awaiting but he did what he thought has to be done because it was in his power to do.
The starvation for freedom and human dignity is an important cause in our country that should be put on an emergency footing. Physical death is not the only form of dying. Denying a human being to experience life to its fullest, muzzling his freedom not to dream and achieve and condemning his family to live a wretched life is a form administering a slow death. We need human beings like Dr. Spencer that feel the pain of others and dedicate themselves to offer relief.
We Africans wish Dr. Craig Spencer a fast recovery and a happy reunion with the ones he love.

ቴዲ አፍሮ በአውሮፓ 6 ከተሞች የሙዚቃ ኮንሰርቶቹን እንደሚያቀርብ ተገለጸ


  • 172
     
    Share
teddy afro
(ዘ-ሐበሻ) በአዲስ አበባ ግዮን ሆቴል ከዛም በአሜሪካ የተለያዩ ግዛቶች የተሳካ የሙዚቃ ኮንሰርቶችን ያቀረበው ቴዲ አፍሮ “70 ደረጃ” የተሰኘውን ነጠላ ዜማ ከለቀቀ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በአውሮፓ 7 የተለያዩ ከተሞች የሙዚቃ ኮንሰርቶቹን እንደሚያቀርብ ከድምጻዊው ሥራ አስኪያጅ ያገኘነው መረጃ አመለከተ::
ቴዲ ዲሴምበር 6 በፊላንድ ሄልሲንኪ
ዲሴምበር 13 በፈረንሳይ ፓሪስ
ዲሴምበር 20 በኖርዌይ ኦስሎ
ዲሴምበር 27 በስዊድን ስቶክሆልም
ለፈረንጆች አዲስ ዓመት ዋዜማ ዲሴምበር 31 በጀርመን ፍራንክፈርት
ለፈረንጆች አዲስ ዓመት ጃንዋሪ 3 በስዊዘርላንድ ጄኔቫ ሥራዎቹን ያቀርባል::
በአውሮፓ ቴዲ ኮንሰርቶቹን እንደሚያቀርብ ከተሠማ በኋላ ብዙዎች ቀኖቹን በጉጉት እየጠበቁት እንደሆነ ከተለያዩ የመረጃ ምንጮች ያገኘናቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ::
70 ደረጃ ለተሰኘው ነጠላ ዜማ አዲስ የሙዚቃ ክሊፕ እየተሠራለት እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን ብዙዎች ይህን በጉጉት እንደሚጠብቁት ይታወቃል::
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/35690#sthash.wBZxvuQs.dpuf

የአ.አ ከንቲባ ጽ/ቤት ጠባቂ ፖሊሶች ተታኮሱ


addis ababa M
የአዲስ አበባ መስተዳደር ማዘጋጃ ቤት (ከንቲባ ጽ/ቤት) ውስጥ የሚሰሩ ፖሊሶች ዛሬ በግምት ከቀኑ 6 ሰዓት አካባቢ እርስ በእርሳቸው መታኮሳቸውን አስተዳደሩ ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡
ፖሊሶቹ የተታኮሱት በከንቲባው ጽ/ቤት ውስጥ የሚሰሩ ፖሊሶች በነበራቸው ግምገማ በተፈጠረ አለመግባባት እንደሆነ ታውቋል፡፡ ፖሊሶቹ የተታኮሱት ከስብሰባው እንደወጡ እንደሆነም ምንጮቹ ገልጸዋል፡፡
በከንቲባ ጽ/ቤት ፖሊሶች በተታኮሱበት ወቅት የአትክልት ተራን ጨምሮ በአካባቢው የሚገኘው ማህበረሰብ በድንጋጤ ውስጥ እንደነበርና አብዛኛው ከተኩሱ በኋላ ወደ አስተዳደሩ ቢሮ በማቅናቱ በከንቲባው ጽ/ቤት አካባቢ በርከት ያለ ህዝብ እንደሚገኝ ምንጮቻችን ጠቅሰዋል፡፡
ፖሊሶቹ በተታኮሱበት ወቅት ገላጋዮች መሃላቸው በመግባታቸው በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለና ይህም በግምገማው ወቅት ለገላጋይ ያበቃ አጨቃጫቂ ጉዳይ እንደነበራቸው ያሳያል ተብሏል፡፡ (የዜናው ምንጭ እና ፎቶ: ነገረ ኢትዮጵያ)

Friday 24 October 2014

ለ‹‹ዜሮ ድምር››ም ያልበቃው የኢትዮጵያ ፖለቲካ

ጌታቸው ሺፈራው
በአገራችን ከ‹‹ልማታዊ መንግስት›› እስከ ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ››፣ ከ‹‹ኪራይ ሰብሳቢነት›› እስከ ‹‹ሽብርተኝነት››፣ ከ‹‹መሃል መንገድ›› እስከ የ‹‹ጽንፍ ፖለቲካ››፣ ከ‹‹ዘረኝነት›› እስከ ‹‹ወያኔነት››፣ ከ‹‹ብሄር›› እስከ ‹‹ጎሳ›› ያልተተረጎሙ ነገር ግን ማንም እያነሳ የሚጥላቸው፣ ሊተነትናቸው የሚሞክራቸው የፖለቲካ ቃላት አሉ፡፡ እነዚህ አብዛኛዎቹ ማንም አንስቶ የሚለውሳቸው የፖለቲካ ቃላት በአብዛኛው በገዥው በኩል የተለመዱ ሲሆኑ በተቃዋሚው ጎራም ሳይቀር የሚዘወተሩ ነገር ግን ያልተተረጎሙ፣ ረጋ ብለን የማናያቸውም ናቸው፡፡
ከእነዚህ መካከል በተደጋጋሚ የሚሰማው የ‹‹ዜሮ ድምር ፖለቲካ›› የሚባለው ነው፡፡ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ተሳታፊ አሊያም ተመልካች ነን የሚሉ አካላት በተለይም ‹‹ተቀናቃኞች›› የሚሄዱበት መንገድ ትክክል አለመሆኑን ለመግለጽ ‹‹በዜሮ ድምር ፖለቲካ›› ባህላቸው ይወቅሷቸዋል፡፡ በግልጽነት ተናገርን የሚሉ ራሳቸውን አሊያም አጠቃላይ የአገራቸውን ሁኔታ ‹‹የዜሮ ድምር ፖለቲካ ባህል›› እንደተጠናወተው ይተቻሉ፣ ይተነትናሉ፣ ያማርራሉ….፡፡
እኔ እስከ ማውቀው የኢትዮጵያ ፖለቲካ የዜሮ ድምር ፖለቲካ በሚባሉበት አጋጣሚ ‹‹አይደለም›› ያለ አካል አላጋጠመኝም፡፡ ይልቁን ልዩነቱ የሚመጣው ለዚህ ‹‹ባህል›› ተጠያቂው ላይ ነው፡፡ ተቃዋሚዎቹ ገዥውን ፓርቲ አሊያም ሌሎች ተቀናቃኞቹን፣ ገዥው ደግሞ ተቃዋሚዎችን ይወቅሳሉ የፖለቲካ ባህላችን የ‹‹ዜሮ ድምር›› እንደሆነ በማይተማመኑትም መካከል ስምምነት የተደረሰበት ይመስላል፡፡ እኔ ደግሞ ለዚህ ብልሹ የፖለቲካ ባህልም አልደረስንም ባይ ነኝ፡፡
የዜሮ ድምር ፖለቲካ ተብሎ የሚጠራው ‹‹የፖለቲካ ሁኔታ›› ከእንግሊዝኛ የመጣ እንደመሆኑ ከአማርኛው ይልቅ ‹‹zero sume game›› የሚለው የእንግሊዝኛው ሀረግ ይበልጡን ይገልጸዋል፡፡ ይህ የፖለቲካ ሁኔታ የፖለቲካ ጨዋታ ነው፡፡ ጨዋታ ደግሞ ህግ፣ የመጫወቻ ሜዳ፣ ሁለትና ከዚያ በላይ ተጫዋቾች፣ ተመልካች፣ ዳኛ፣ ቢቻል ታዛቢ ያስፈልገዋል፡፡ በተጫዋቾች መካከል የተግባቡበት ግንኙነት ሊኖር የግድ ነው፡፡ ፈረንጆቹ ‹‹political game›› ወይንም እንደ አጠቃላይ ‹‹game theory›› በሚሉት የፖለቲካ ሁኔታም ተጫዋች፣ ህግ፣ ተመልካች፣ ዳኛ ከተቻለም ታዛቢ እንዳለው እናያለን፡፡ በአብዛኛው የዜሮ ድምር ፖለቲካ የሚባለው በየትኛውም የፖለቲካ ‹‹ጨዋታ›› አሸናፊና ተሸናፊ አለ ከሚል አስተሳሰብ በመነሳት ነው፡፡ አሸናፊና ተሸናፊነት በፖለቲካ መድረክ አንዳንዴ አጨቃጫቂ ቢሆንም በግልጽ የሚታዩባቸው እንደ ምርጫ አይነት መድረኮችን መግለጽ ይቻላል፡፡
ፈረንጆቹ ‹‹ጌም ቲዮሪ›› የሚባለውን ‹‹the study of mathematical models of conflict and cooperation between intelligent rational decision-makers›› ብለው ይተረጉሙታል፡፡ ‹‹የዜሮ ድምር ፖለቲካ›› የሚባለው የአማርኛው ፍችም ከመሰል የእንግሊዝኛው ትርጉም የመጣ ነው፡፡ በዚህ ትርጉም ደግሞ ‹‹የዜሮ ድምር ፖለቲካም›› በሂሳብ ስሌት፣ በታሰበበት ውሳኔ እንጂ በማንቦጫረቅና በዘፈቀደ ላይ የተመሰረተ እንዳልሆነ ነው፡፡
police ethiopia
በ‹‹ፈረንጆቹ ትርጉም›› መሰረት የዜሮ ድምር ፖለቲካ አብላጫውን ያገኘው አካልና ያጣው አካል ተደምሮ ዜሮ የሚመጣ ከሆነ ብቻ ነው፡፡ አንዱ ያገኘውና ሌላኛው ያጣው ተደምሮ ዜሮ ይመጣል እንደማለት ነው፡፡ ይህ በሂሳብ ስሌት አንዱ 2 ሲያገኝ ሌላኛው ሁለትን ያጣል አሊያም ነጋቲቭ ሁለት ያገኛል እንደማለት ነው፡፡ በአገኘውና ያጣው ሲደመር ውጤቱ ዜሮ ይመጣል ማለት ነው፡፡
በአገራችን ‹‹የዜሮ ድምር ፖለቲካ›› ስንል አንዱ ሁሉንም ጠቅልሎ የሚወስድበት አሊያም ሌላኛው ሁሉንም የሚያጣበት የሚለው ትርጉም ይሰጠዋል፡፡ አንዳንዴ ደግሞ ተወያይቶ ችግርን አለመፍታት፣ ተደራድሮ አለመታረቅ፣ ተነጋግሮ አለመደማመጥ ሁሉ ‹‹ዜሮ ድምር ፖለቲካ›› እየተባለ ይጠራል፡፡ ሁሉም የሚያጣበት ፖለቲካ ተብሎ ተተረጎመ ማለት ነው፡፡ ዜሮ ሲደመር ዜሮ ያው ዜሮ እንደማለት ነው፡፡
በአብዛኛው የእኛ አገር ፖለቲካ ማንም የማያተርፍበት ፖለቲካ ነው፡፡ በተለይ ተወያይቶ ችግርን አለመፍታት፣ ተደራድሮ አለመታረቅ፣ ተነጋግሮ አለመደማመጥ፣ ተባብሮ አለመስራት፣ ተነጣጥሎም መውደቅ፣ ተባብሮም አለመተባበር ሁሉንም ሲያከስሩ ይታያል፡፡ ይህ ግን ከዋነኛው ትርጉም አንጻር የ‹‹ዜሮ ድምር ፖለቲካ›› ሊሆን አይችልም፡፡ አንዱ ያጣውና ሌላኛው ያገኘው ተደምሮ ሳይሆን ሁለቱም ምንም ያገኙ አይደሉም፡፡ ምን አልባት ‹‹አንችም ዜሮ ዜሮ፣ እኔም ዜሮ ዜሮ›› ለሆነው ለዚህ የፖለቲካ ሁኔታ ሌላ ትርጉም ያስፈልገው ይሆናል፡፡
የእንግሊዝኛው ትርጉም ‹‹አሸናፊው ያገኘው ተሸናፊው ካጣው ከበለጠ (ድምሮ ከዜሮ ይበልጣል) ወይንም አሸናፊው ያገኘው መጠን ተሸናፊው ካገኘው ካነሰ (ሁለቱ ሲደመር ከዜሮ በታች ነው የሚሆነው) ዜሮ ድምር ፖለቲካ አይደለም›› ይላል፡፡ የሁለቱ አካላት ያገኙትና ያጡት ተደምሮ ከዜሮ የሚያንስ ወይንም የሚበልጥ ከሆነ የዜሮ ድምር አይደለም ማለት ነው፡፡ አንዳንዶቹ ይበልጡን አትራፊ ሲሆኑ ሌሎቹ ደግሞ ይበልጡን ከሳሪዎች ይሆናሉ፡፡
በእርግጥ የእኛው አገር የ‹‹ፖለቲካ ጨዋታ›› ከቁጥር ስሌት፣ ከድምር ፖለቲካም የሚገባ አይደለም፡፡ የዜሮ ድምር ፖለቲካ ህግ፣ የመጫወቻ ሜዳ፣ ተጫዋቾች፣ ተመልካቾች፣ ዳኞች፣ ቢቻል ታዛቢዎች ይኖሩታል፡፡ የእኛ አገር የ‹‹ፖለቲካ ጨዋታ›› ህግ፣ ተጫዋች፣ ተመልካች፣ ዳኛ፣ ታዛቢን የሚያሟላ አይደለም፡፡ በእኛ አገር ፖለቲካ በአንድ ‹‹ጨዋታ›› የተለያየ ማሊያ ለብሶ ተጫዋች፣ ዳኛ፣ ተመልካችም፣ ታዛቢም፣ ዳኛም የሚሆነው ራሱ ገዥው ፓርቲ ነው፡፡
በአንድ አካል የበላይ ተዋናይነት የሚመራው የ‹‹ፖለቲካ ጨዋታው›› በቋሚ ህግ የሚመራ ሳይሆን ይህ ሁሉ በእጁ ሁሉ በደጁ የሆነ አካል ሲፈልግ ‹‹ጨዋታ ፈረሰ›› የሚልበት፣ ህግ ብሎ ካስቀመጠው ውጭ ጨዋታውን የሚዘውርበት፣ ተቀናቃኝ ተጫዋች ወይንም ቡድን የሚወስንበት፣ የሚያሰለጥንበት፣ የሚቀጣና የሚሸልምበት መድረክ ነው፡፡ በመሆኑም በእኛ አገር የ‹‹ዜሮ ድምር ፖለቲካ›› በሂሳብ ስሌት ማን አገኘ፣ ማን ምን ያህል አጣ፣ ተደምሮስ ስንት ይሆናል ከማለታችን በፊት ‹‹ጨዋታ››ነትን አላሟላም ማለት ነው፡፡
በመሆኑም ዜሮ ድምር ፖለቲካ ሊኖር የሚችለው (በአወንታዊም ሆነ በአሉታዊ መልኩ) ስርዓት ላበጁ፣ ስርዓቱ ምንም ይሁን ምን በዛ ስርዓት ወይንም ህግ ለሚገዙ አካላት ነው፡፡ በእርግጥ ይህ ነው የሚባል ስርዓት የሌላቸው ወይንም ብልሹ የፖለቲካ ስርዓት ላይ የመጫወቻ ሜዳቸውን የመሰረቱ አገራት ላይ በገዥነት ላይ የተቀመጡ ስርዓቶችም ከእኛዎቹ ገዥዎች የተሻሉ ወደ ‹‹ፖለቲካ ጨዋታው›› ይጠጋሉ፡፡
ለአብነት ያህል የምርጫ ቦርድ የሚባል ዳኛ፣ የምርጫ ስነ-ምግባር፣ የምርጫ ቦርድ አዋጅ፣ ህገ መንግስትና ሌሎችንም ህጎች አውጥቶ፣ ፖለቲካ ፓርቲዎች እንዲኖሩ ‹‹ፈቅዶ››፣ ምርጫ የሚባል መወዳደሪያ ሜዳ እንዳለ አሳውቆ፣ ህዝብ (ተመልካች) በነጻነት እንደሚመርጥ ቃል ገብቶና በህግ አጽድቆ ይህን ሁሉ ተግባር በራሱ ከሚወጣው ኢህአዴግ ይልቅ እነዚህን ቀልዳቀልዶች ሁሉ እንደሌሉ ህዝቡ እንዲያውቅ ቁርጡን ተናግሮ ብቸኛ ‹‹ሀቀኛ›› ተጫዋች ነኝ ያለው የኢሳያስ አፈወርቂ መንግስት ‹‹ለፖለቲካ ተጫዋችነት›› የቀረበ ነው ማለት ይቻላል፡፡
የኢሳያስ መንግስት ራሱ የሚያዘው ምርጫ ቦርድን ‹‹ነጻ ነው!››፣ ራሱ ያሰማራቸውን ካድሬዎች ታዛቢዎች ናቸው፣ መንቀሰቀቀስ የማይችሉትን ተቃዋሚዎች ተቀናቃኞች ናቸው፣ ስርዓቱ የመሰረተውንና በሱ ሳንባ የሚተነፍስ ሚዲያ ነጻ ሚዲያ ነው ብሎ የሌለ ‹‹ጨዋታን›› እንጫወት ብሎ ባለማሞኘቱ ከኢህአዴግን በአንጻራዊነት የተሻለ ያደርገዋል ባይ ነኝ፡፡
እንደ ሙጋቤ ያሉት አምባገነኖች ህግን በቀጥታ ከመጣስ ይልቅ ለእነሱ የሚመች የመጫወቻ ሜዳ ያበጃሉ፡፡ ለዚህም ሲባል የዚምባብዌ ህገ መንግስት በርከት ላለ ጊዜ ተሻሽሏል፡፡ ይህም በቀጥታ የጨዋታውን ህግ ከመጣስ ይልቅ የጨዋታውን ህግ የማስቀየር ጨዋታን ነው የሚጫወተው፡፡ ከዛ በኋላ ግን ላወጣው ህግ ሲገዛ ይታያል፡፡ ይህም ቢሆን ከኢህአዴግ የተሻለ ነው ባይ ነኝ፡፡
እነዚህ አምባገነኖች የገነኑባቸው አገራት ከኢትዮጵያው ሁኔታ ይሻላል በሚል እንጂ ትርጉሙን ያሟላሉ በማለት አይደለም፡፡ የዘሮ ድምር ፖለቲካ በአብዛኛው በተጫዋቾቹ ብቃትና ውሳኔ የሚወሰን ነው፡፡ በእርግጥ ዳኛ፣ ተመልካች፣ ታዛቢም በዜሮ ድምሩ ይቅርና በሌሎች የመዝናኛ ጨዋታዎችም አሸናፊና ተሸናፊን ይወስናሉ፡፡ ሆኖም ግን ተጫዋቾቹ ሚና በመጀመሪያ ደረጃ የሚቀመጥ ይሆናል፡፡ በፖለቲካው ዓለምም ተፎካካሪ በአንድም ሆነ በሌላው ተሳታፊ ተጽዕኖ አግባብ ያልሆነ ውጤት ሊያገኝ ይችላል፡፡
ነገር ግን መጀመሪያ አንደኛው ተጫዋች ሌላኛውን በህጋዊ ሰውነት የሚያይበት፣ እኩልና ተወዳዳሪው መሆኑን የሚያምንበት፣ ህግ ለመጠቀሚያ ሳይሆን ሁለቱን ለመዳኘት የሚውልበት፣ ተመልካቹ በተጫዋቾቹ ብቃት የሚደግፍና የሚመርጥበት፣ ዳኛውና ታዛቢው በገለልተኝነት የሚሰሩበት መድረክ መዘጋጀት አለበት፡፡ በዚህ ሁኔታ በሰዋዊ ስህተትም ሆነ በሌላ መንገድ ማጭበርበር ቢኖርም አንደኛው ተጫዋች ተነስቶ ዳኛ የሚሆንበት፣ ተቃናቃኙን የሚታዘብበት፣ ተመልካቹን አስገድዶ የራሱ የሚያደርግበት መሆን የለበትም፡፡ አሊያም ይህ ስህተት የሚዳኝበት ህጋዊ መሰረት ይኖራል፡፡
ይህ ካልሆነ ግን ልክ እነ ኢሳያስ እንኳን ‹‹እንደ ኢትዮጵያ ከሆነ በአመትም 10 ምርጫ ማድረግ እንችላለን›› እንደሚሉት የኢትዮጵያ አይነት የማሞኛ ምርጫ መሆኑ ነው፡፡ እንዲህ አይነት ‹‹ተጨፈኑ ላሞኛችሁ›› ደግሞ ‹‹ዜሮም ሆነ የሚሊዮን ድምር›› የሚያበቃ የ‹‹ጨዋታ›› ለዛ የለውም፡፡ በዚህ ረገድ ፖለቲካችን ከ‹‹ጨዋታ›› ይልቅ ‹‹መጫወቻ፣ መቀለጃ›› የሆነ ብልሹ ፖለቲካ ነው፡፡
የፖለቲካ ጨዋታ ዜሮም ይሁን ምን ተጫዋች፣ ተመልካች፣ ህግ፣ ተመልካች፣ ታዛቢና ሜዳ የሚኖረው በመሆኑ በእኛ አገር ራሳቸው ህግ አውጥተው፣ ራሳቸው ከሚጥሱት፣ እየተጫወቱ ተመልካችም፣ ዳኛም ታዛቢም ከመሆኑት ብቸኛ ተጫዋችነትን በገሃድ ባወጁት ‹‹ቅን አምባገነኖች›› አለ ቢባል ይቀላል፡፡ በትርጉሙ መሰረት ደግሞ ወጠምሻዎች ከሚመሩት ‹‹ስርዓት›› ይልቅ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት በገነቡት አገራት ሊኖር የሚችል የ‹‹ፖለቲካ ጨዋታ›› ነው፡፡
ይህን ሁሉ ስናይ የኢትዮጵያ ፖለቲካ በብልሹነቱ ከምናነሳው የ‹‹ዜሮ ድምር›› ፖለቲካም ደረጃም አልደረሰም ማለት ነው፡፡ የሂዳን ስሌቱ እንዳለ ሆኖ ቢያንስ በዛ ‹‹ብልሹ ፖለቲካ››ም ውስጥ ተጫዋቾች፣ የሚከበር ህግ፣ ተመልካቾች፣ ዳኞች፣ ታዛቢዎች መኖር ይጠበቅባቸዋልና ነው፡፡

Freedom Demonstration Europe Nov 7th 2014



EPRDF MUST STOP KILLING THE INDIGENOUS PEOPLE OF GAMBELLA

October 24, 2014
Gambella Nilotes United Movement/Army
Press Release
October 24th 2014, Gambella
“EPRDF MUST STOP KILLING THE INDIGENOUS PEOPLE OF GAMBELLA”
Gambella Nilotes United Movement (GNUM) strongly condemns the Ethiopian government’s ethnic cleansing plans and act by creating conflict between highlanders and the indigenous people of Gambella. The massacre of Mezenger tribe since September 11/2014 is increasingly spreading to all villages of Godere zone by criminal and illegal highlanders supported by EPRDF national defence forces. Along the border between Gurafarda District (SNNPR of Ethiopia) and Godere District of Gambella all Mezenger villages were destroyed by Ethiopian National Defence following the campaign of the government to eliminate all Mezenger people from their ancestral land. Until today there is no access for independent body to visit the area to investigate the scale of damage and massacre of the Mezenger people due to presence of highly equipped military throughout the two districts.Gambella Nilotes United Movement
Since 2003 Anuaks genocide in the Gambella region, the Ethiopian government has increasingly carried out several massacres and serious crimes against humanity as means to appropriate land for the northern settlers and commercial investors in Gambella. The chronological records of these massacres are still mounting.
On October 13th 2014 in Abwobo town highlanders killed innocent Anuaks and caused many injuries and stability. The killing in Abobo town spread to Gambella town as well. On Tuesday night of October 14th 2014 one Anuaks young boy was killed and another one injured. As pretext the EPRDF government is currently mobilizing illegal and criminal highlanders to own machetes and pangas to carry out a well planned massacre against the indigenous populations. This is a racist plan of the EPRDF/TPLF government to create ethnic cleansing conflicts in the region to displace and extinct the indigenous Nilotes from their ancestral lands and promote systematic settlements and occupations of Northerners in the land they don’t own in the South-western regions. We are calling up on all the indigenous people to remain alert and conscious to defend themselves against the planned atrocities of the Ethiopian government.
GNUM has been aware that the Ethiopian federal police and the Ethiopian National Defence Forces (ENDF) have been very instrumental in instigating racist conflicts against the indigenous Nilotes in the region, and their role always is to make sure they flush out the indigenous populations from their ancestral lands in favour of highlanders. The indigenous Nilotes don’t enjoy freedom and equality as they continue to suffer discrimination against their colour and race in the country. They are seen inferior, less citizens, less humans of not deserving any right to acquire properties as other citizens, even in their own lands.
For this very reason, GNUM is determined to fight for the freedom and equality of the indigenous Nilotes to ensure their full recognition and identity in their ancestral land. The TPLF government beyond any doubt is a racist government that puts ethnic conflicts as means to prosper its own people from the north. It does not care for all its citizens, and it should be resisted strongly by all means.
GNUM would like to inform the Nilotic people of south-western Ethiopia to remain courageous that the TPLF government have lost support from the Ethiopians and it will soon vanish. We urge all Nilotes and Omotic people to maintain their unity and moral to fight back this dictator and oppressive regime. For all those who lost their lives in the hands of EPRDF government, we share your grief and death for your ancestral land and your bloodshed in will not be in vain; one day will change to freedom, prosperity, happiness, and equality. Your bloods cry loud for freedom and justice before God. GNUM will stand with you always.
Therefore, GNUM would like to call upon all the indigenous Nilotes to unite themselves as one people and should resist and fight the racist government plan to protect their land. Resistance should be encouraged and strengthened against this racist government to protect the livelihood of the indigenous populations. Our land, as indigenous peoples, should be known as source of our livelihood. We should be determined to protect this right at all cost.
In this particular moment, GNUM would like to call upon the international community to investigate the killings of indigenous people in Majenger Zone, Abobo and Gambella towns through neutral body, and cause the perpetrators to be brought to justice. We call upon all the international donors to stop their funding to the TPLF government to make sure their funds are not used to perpetuate the killings against the innocent indigenous populations.
We are also strongly calling upon the international community to investigate more critically the root cause of the increasing killings against the indigenous populations in southwest Ethiopia and come up with strong recommendations and actions for maximum self determination as the only lasting solution to protect the life of the indigenous populations.
In conclusion the Gambella Nilotes United Movement (GNUM) will continue it struggle for all people of Gambella and South-western Nilotes to ensure security, freedom, liberty, justice, and prosperity are brought to the indigenous peoples in their God given lands.
“Southwest Ethiopian Indigenous Nilotes Should Unite As One People to Resist and Fight the Racist Government of EPRDF/TPLF”
Gambella Nilotes United Movement/Army
Central Committee
Our contact:
gambellagnuma@yahoo.com OR gambellagnuma@gmail.com

David Cameron writes to Ethiopian PM on behalf of British political dissident on death row – By JONATHAN OWEN

Andargachew “Andy” Tsege, a critic of the Ethiopian regime, was kidnapped in Yemen
 Thursday 23 October 2014, The Prime Minister has personally intervened in the case of a British father-of-three facing the death sentence in Ethiopia, after the man’s children appealed for his help. David Cameron wrote to the Ethiopian Prime Minister in a bid to save the life of Andargachew “Andy” Tsege, 59, whose plight was revealed by The Independent last Friday.
His actions were in response to what he described as “very touching messages” from Mr Tsege’s children, who are calling for the Prime Minister to help get their father home.
Mr Tsege, who came to Britain as a political refugee in 1979, was arrested at an airport in Yemen in June and promptly vanished. Two weeks later it emerged he had been sent to Ethiopia, where he has been imprisoned ever since. The Briton, a prominent opponent of the Ethiopian regime, is facing a death sentence imposed five years ago at a trial held in his absence.
Menabe, his seven-year-old daughter, recently wrote to Mr Cameron asking him to help get her “kind, loving and caring dad” out of prison. Her twin brother, seven-year-old Yilak, simply asked: “What are you doing to get my dad out of jail?” Mr Tsege’s 15-year-old daughter, Helawit, summed up the mood of the family in her letter: “Please, please, please (!) bring him back soon. We miss him so much.”
The 59-year-old sought asylum in Britain in 1979 after being threatened by Ethiopian authorities over his political beliefsThe 59-year-old sought asylum in Britain in 1979 after being threatened by Ethiopian authorities over his political beliefs (Reprieve)
Responding to the children’s appeals, the Prime Minister claimed the government is taking the case “very seriously”. In the letter to Yemi Hailemariam, Mr Tsege’s partner and mother of their children, Mr Cameron admitted “Ethiopian authorities have resisted pressure” from British officials to have regular “access” to Mr Tsege.
“As a result of the lack of progress to date I have now written personally to Prime Minister Hailemariam Desalegn to request regular consular access and his assurance that the death penalty (which the British Government opposes in all circumstances) will not be imposed,” he added. “I very much hope that there will be further progress to report in response to my letter,” he concluded.
Responding to the news, Maya Foa, head of the death penalty team at legal charity Reprieve, commented: “The Prime Minister says he is ‘concerned’ – but where is the outrage at this flagrant breach of international law, and the ongoing abuse of a British citizen?”
She added: “Andy’s small children are terrified of losing their father, his partner is desperate with worry, and we are no closer to seeing Andy released and returned to safety. Enough delays – we need firm action now to bring him home to London.”
Tsege was arrested during a two-hour stop over in the Yemeni capital, Sana’aTsege was arrested during a two-hour stop over in the Yemeni capital, Sana’a (EPA)
Reprieve has begun legal moves which could result in a judicial review to force Foreign Office officials to press for Mr Tsege’s immediate release and return to Britain – something which the Government has resisted to date. A letter to Treasury Solicitors, sent last week by lawyers acting for the charity, argues: “Far from not being ‘entitled’ to request his return, the UK Government has every reason to do so and we urge you to exercise that power as a matter of urgency.”
Meanwhile, Mr Tsege’s family remain in limbo. The past four months have been “agonising” said Ms Hailemariam. “Waking up every day not knowing where Andy is or how he’s being treated is taking a terrible toll on my children and myself.” She added: “The Prime Minister has told our family that he is taking action, but it seems like next to nothing is being done to get Andy back. The children and I need him here with us in London. The Government must demand his return, before it’s too late.”

Thursday 23 October 2014

አንድነት ውስጣዊ የዴሞክራሲ ባህል ያለው ፓርቲ ነው!

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ መግለጫ

UDJአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ (አንድነት) ፓርቲ በአሁኑ ሰዓት ከመቼም ጊዜ በላይ በጠንካራ አቋም ላይ ይገኛል። በፓርቲው ውስጥ ጎልቶ እየታየ የመጣው የለውጥና የማንሰራራት ፍላጎት ተገንዝበው የፓርቲው ፕሬዚደንት የነበሩት ኢንጂነር ግዛቸው ሺፈራው በራሳቸው ፍቃድ መልቀቃቸው የፓርቲው የዴሞክራሲ ባህል የላቀ ደረጃ ላይ መድረሱን በትክክል የታየበት፤ ፓርቲው በተሻለ ቁመና ላይ እንዲጓዝ በር የከፈተ ትልቅ እርምጃ በመሆኑ ሊደነቅ የሚገባ ጉዳይ ነው። በመሆኑም ብሄራዊ ምክር ቤቱ ጥቅምት 2/2007 ዓ.ም. ባደረገው ስብሰባ የኢንጂነር ግዛቸውን የመልቀቂያ ጥያቄ አዳምጦ ካፀደቀ በኋላ የፓርቲው መተዳዳሪያ ደንብ በሚፈቅደው መሰረት አስመራጭ ኮሚቴ አቋቁሞ ፓርቲውን በቀጣይነት የሚመራ ሰው በዕለቱ ከቀረቡት ሶስት እጩዎች መካከል አቶ በላይ ፍቃዱን በከፍተኛ ድምፅ የፓርቲው ፕሬዝዳንት አድርጎ መርጠዋል።
አንዳንድ ወገኖች በዚህ ፍፁም ደንባዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ ሂደት ያለፈና የፀደቀ ጉዳይ የደንብ ጥሰት የተፈፀመ በማስመሰል ጫጫታ ለመፍጠር የተንቀሳቀሱበት ሁኔታ ቢኖርም፤ በዚህ ዴሞክራሲያዊ የሆነ የስልጣን ሽግግር ላይ ምንም ዓይነት የደንብ ጥሰት ያልተፈፀመ መሆኑ አፅንኦት ሰጥተን ለመግለፅ እንፈልጋለን። አንድነት ውስጣዊ የዴሞክራሲ ባህል ያለው፤ ልዩነቶችን በውይይት መፍታት የሚችልና በዚህ ለሌሎችም ትምህርት የሚሆን ልምድ ያለው ፓርቲ ነው።
በአሁኑ ሰዓት አዲሱ ፕሬዚዳንት በአዲስ መንፈስ ካቢኔያቸውን አቋቁመው በፍጥነት ወደ ስራ የገቡበት ሁኔታ ነው ያለው። ፓርቲው የተሻለ እንቅስቃሴ እንዲያደርግ ውስጡን የማጥራትና የማስተካከል ስራ እየተሰራ ከመሆኑም ባሻገር የሁሉም ኢትዮጵያውያን ቤት እንዲሆንና ብቃት ያላቸው አመራሮች ወደፊት እንዲመጡ በማድረግ አንድነት በሰላማዊ ትግሉ ታግሎ በማታገል የስርዓት ለውጥ ማምጣት የሚችል ህዝባዊ መሰረት ያለው ፓርቲ እንዲሆንና ጠንካራ ቁመና እንዲኖረው ርብርብ እየተደረገ ይገኛል። ህዝቡ ይህን ተገንዝቦ እንደ ከዚህ ቀደሙ ከጎናችን እንዲቆም፤ ለነፃነትና ለዴሞክራሲ በምናደርገው ትግልም ላይ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆን በዚህ አጋጣሚ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
ኢትዮጵያ በነፃነቷና በአንድነቷ ለዘላለም ትኑር!
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ (አንድነት) ፓርቲ
ጥቅምት 12/2007 ዓ.ም.
አዲስ አበባ

መልዕክት ስለተመስገን ደሳለኝ ከጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ

 

  • 111
     
    Share

Temesgen‹ተመስገን፣ ጥሩ ታጋይ እና ሰው ሆኖ ለእስር ይወጣል››
‹‹ተመስገን፣ የህዝብ ልጅ ነው፤ ነገም ከነገወዲያም የህዝብ ልጆች ይፈጠራሉ››
ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ‹‹ስለተመስገን ደሳለኝ ሃሳቤን አስተላልፍልኝ›› ካለኝ የተወሰደ
ከትናንት በስትያ፣ ሰኞ ዕለት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና የአንድነት ፓርቲ ጸሐፊ የሆነውን አቶ አንዷለም አራጌን በ2007 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ ላገኛቸው ችዬ ነበር – ለአቤል አለማየሁ ጋር፡፡ ባለፈው ሳምንት የ‹‹ባንዲራ ቀን›› በተከበረበት ዕለት ቃሊቲ ከወዳጄ እዩኤል ፍስሐ ጋር ሄጅ እነስክንድርን መጠየቅ ሳንችል ተመልሰን ነበር፡፡
የሆኖ ሆኖ፣ ከእስክንድር ጋር ለ15 ደቂቃ ያህል ለማውጋት ችለን ነበር፡፡ እስኬው፣ ሁሌም መንፈሱ ጠንካራ ነው፡፡ ሰኞም ያ አስደማሚ ጥንካሬው፣ ትህትናው፣ እውነተኛ ቅንነቱ፣ ብርታቱ፣ ቀናኢነቱ…አብረውት ነበሩ፡፡
ሰዓት ደርሶ ከእስክንድር ጋር ቻው ከተባባልን በኋላ ‹‹ኤልያስ፣ አንዴ ላናግርህ›› ብሎ ከጠራኝ በኋላ ‹‹እባክህ አንድ መልዕክት ስለተመስገን ደሳለኝ አስተላፍልኝ›› አለኝ፡፡ እስንክድር፣ ሁሌ ሀሳቤን አስተላልፍልኝ ሲለኝ ግልጽነቱ እጅግ ይማርካል፡፡
‹‹እሺ›› አልኩት››
‹‹ተመስገን፣ ጥሩ ታጋይ እና ጥሩ ሰው ሆኖ ከእስር ይወጣል፡፡ ተመስገን የህዝብ ልጅ ነው፡፡ ነገም ከነገወዲያም የህዝብ ልጆች ይፈጠራሉ፡፡ እስሩ ስለሀገሩ ያበረታዋል፤ ያጠነክረዋል፡፡ ብዙ ነገር እንዲረዳ ያደርገዋል፡፡ ሰዎች ይታሰሩ እያልኩ አይደለም፡፡ ይሄ አንዱ የሰላማዊ ትግል መስራት ውጤት ነው፡፡ በለውጥ እና በትግል መስመር ላይ ያሉ ኢትዮጵኖች መታሰራቸው ነገ ለውጥ ያመጣል፡፡››
ካለኝ በኋላ ለሁሉም ‹‹እወዳችኋለሁ፣ አከብራኋለሁ፣ በተሰማራችሁበት የህይወት መስመር፣ በሰላማዊ መንገድ በርትታችሁ ለለውጥ ታገሉ!›› በልልኝ ብሎኛል፡፡
እኔም ዛሬ ‹‹የሀገሪቱን ህዝቦች አንድነት እንዲፈርስ እና በሀገሪቱ ሕዝቦች መካከል ጸብና ቁርሾ እንዲፈጠር በማሰብ …›› የሚል ከባድ ክስ ብቀበልም የእስክንድርን መልዕክት ለማስተላለፍ አልተቆጠብኩም፡፡

ፍቅር ያሸንፋል!
Elias Gebru Godana

አንድነት ውስጣዊ የዴሞክራሲ ባህል ያለው ፓርቲ ነው!

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ መግለጫ

UDJአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ (አንድነት) ፓርቲ በአሁኑ ሰዓት ከመቼም ጊዜ በላይ በጠንካራ አቋም ላይ ይገኛል። በፓርቲው ውስጥ ጎልቶ እየታየ የመጣው የለውጥና የማንሰራራት ፍላጎት ተገንዝበው የፓርቲው ፕሬዚደንት የነበሩት ኢንጂነር ግዛቸው ሺፈራው በራሳቸው ፍቃድ መልቀቃቸው የፓርቲው የዴሞክራሲ ባህል የላቀ ደረጃ ላይ መድረሱን በትክክል የታየበት፤ ፓርቲው በተሻለ ቁመና ላይ እንዲጓዝ በር የከፈተ ትልቅ እርምጃ በመሆኑ ሊደነቅ የሚገባ ጉዳይ ነው። በመሆኑም ብሄራዊ ምክር ቤቱ ጥቅምት 2/2007 ዓ.ም. ባደረገው ስብሰባ የኢንጂነር ግዛቸውን የመልቀቂያ ጥያቄ አዳምጦ ካፀደቀ በኋላ የፓርቲው መተዳዳሪያ ደንብ በሚፈቅደው መሰረት አስመራጭ ኮሚቴ አቋቁሞ ፓርቲውን በቀጣይነት የሚመራ ሰው በዕለቱ ከቀረቡት ሶስት እጩዎች መካከል አቶ በላይ ፍቃዱን በከፍተኛ ድምፅ የፓርቲው ፕሬዝዳንት አድርጎ መርጠዋል።
አንዳንድ ወገኖች በዚህ ፍፁም ደንባዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ ሂደት ያለፈና የፀደቀ ጉዳይ የደንብ ጥሰት የተፈፀመ በማስመሰል ጫጫታ ለመፍጠር የተንቀሳቀሱበት ሁኔታ ቢኖርም፤ በዚህ ዴሞክራሲያዊ የሆነ የስልጣን ሽግግር ላይ ምንም ዓይነት የደንብ ጥሰት ያልተፈፀመ መሆኑ አፅንኦት ሰጥተን ለመግለፅ እንፈልጋለን። አንድነት ውስጣዊ የዴሞክራሲ ባህል ያለው፤ ልዩነቶችን በውይይት መፍታት የሚችልና በዚህ ለሌሎችም ትምህርት የሚሆን ልምድ ያለው ፓርቲ ነው።
በአሁኑ ሰዓት አዲሱ ፕሬዚዳንት በአዲስ መንፈስ ካቢኔያቸውን አቋቁመው በፍጥነት ወደ ስራ የገቡበት ሁኔታ ነው ያለው። ፓርቲው የተሻለ እንቅስቃሴ እንዲያደርግ ውስጡን የማጥራትና የማስተካከል ስራ እየተሰራ ከመሆኑም ባሻገር የሁሉም ኢትዮጵያውያን ቤት እንዲሆንና ብቃት ያላቸው አመራሮች ወደፊት እንዲመጡ በማድረግ አንድነት በሰላማዊ ትግሉ ታግሎ በማታገል የስርዓት ለውጥ ማምጣት የሚችል ህዝባዊ መሰረት ያለው ፓርቲ እንዲሆንና ጠንካራ ቁመና እንዲኖረው ርብርብ እየተደረገ ይገኛል። ህዝቡ ይህን ተገንዝቦ እንደ ከዚህ ቀደሙ ከጎናችን እንዲቆም፤ ለነፃነትና ለዴሞክራሲ በምናደርገው ትግልም ላይ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆን በዚህ አጋጣሚ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
ኢትዮጵያ በነፃነቷና በአንድነቷ ለዘላለም ትኑር!
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ (አንድነት) ፓርቲ
ጥቅምት 12/2007 ዓ.ም.
አዲስ አበባ

BREAKING THE CYCLE OF DYSFUNCTION IN ETHIOPIAN INSTITUTIONS. – SMNE FORUM

Ethiopia’s strategic importance is growing in an increasingly global world. As it does, a tug of war over access to Ethiopia and its resources between and among internal and foreign players has ignored the voice of the people, furthering their oppression. Opposing images of Ethiopia have emerged.

The faulty image presented by those in power, along with their supporters, is one of remarkable economic progress and with it, widespread development and the alleviation of hunger. Such an image sharply contrasts with the testimonies of people on the ground, refugees fleeing the country, and record amounts of remittances going into the country to support relatives, otherwise unable to survive in many cases. At the same time, record levels of illicit capital leakage from Ethiopia, some $11.7 Billion (USD), left the country from 2000 to 2009, with a loss of $3.6 billion (USD) in 2009 alone. It has only increased since then.
Human rights organizations document widespread violations, often accompanied by the forceful eviction of people from their homes and land. Voices of freedom and truth are locked up in prisons and detention centers through the misuse of an anti-terrorism law. Various studies and indexes place Ethiopia close to the bottom in terms of freedom, justice and wellbeing in Africa, as well as globally.
Laws restricting civil society have virtually eliminated any independent voice. Instead, the regime controls all public and private institutions and uses them either to advance their own interest or as political weapons against dissenters. Within their grasp are the Parliament, the justice system, the military, federal and local security forces, the media, financial institutions, telecommunications, religious groups, and access to educational, economic and other opportunities. High levels of corruption, including the misuse of donor aid, accompany this.
The fomenting of ethnic and religious conflict, a trademark of ethnic-based regime of the TPLF/EPRDF, has fueled the dehumanization of others. As intended, this has divided Ethiopians into hostile and competing factions in order to maintain their minority power through a strategy of divide and conquer. Experts warn that the ethnic-based or religious-based conflict in Ethiopia is a ticking bomb that may erupt into violence, killing and chaos like that of Rwanda, Yugoslavia, or South Sudan if action is not taken to avert it.
The people of Ethiopia are aware of these dangerous divisions; yet, they remain isolated in their ethnic or religious groups, talking about others rather than to each other. How can ordinary Ethiopians play a major role in creating a healthier, more just and harmonious Ethiopia? Beginning this conversation among diverse Ethiopians will be the goal of this people-to-people conference.
The first session of the forum will focus on: “Dysfunctional Institutions in Ethiopia.” We will hear from Ethiopian and non-Ethiopian experts on the state of institutions; in particular, how regime control, the misuse of foreign aid, control of information, deceptive statistics regarding double-digit economic growth, and rampant corruption have led to a crisis of liberty, human rights, and development. The names of the speakers and panelists will be released soon The second session will focus on: “Identifying, Affirming and Building a New Ethiopia based on our Shared Core Values.” We will hear from Ethiopians of diverse ethnicity, religion, gender, and background, as well as experts, on the subjects of reconciliation, meaningful reforms, and the restoration of justice. In the absence of functional institutions, the people must assume their role. The problem of weak institutions did not start with the current regime, but has been rooted in our history. Unless the people create a groundswell of momentum for stronger institutions, the changes we all seek, even once the present regime ends, will fail to be realized.
Saturday, November 15, 2014, 10:00 AM to 7:00 PM
Sheraton Pentagon City Hotel,
900 S Orme St., Arlington, VA

Let the conversation begin!
This event is open to the public. For more information or opportunities to be a sponsor, please contact: Obang Metho at obang@solidaritymovement.org.