Tuesday 13 January 2015

በአንድነት አባላት እንዴት inspired እነደሆንኩ! – ሶሊያና ሽመለስ (የዞን 9 ቦልገር)

ትላንትና ያየሁት የአንድነት ፓርቲ አባላት ፎቶ ጭንቅላቴ ውስጥ ተቀርጾ ዋለ፡፡ ፎቶው ላይ ምርጫ ቦርድ የጠራው አስገዳጅ ጉባኤ ላይ ለመገኘት መጥተው ፓርቲው ቢሮ ውስጥ መሬት የተኙ አባላት ፎቶ ነበር፡፡
አንዱን እዛ መሬት ላይ የተኛ አባል አሰብኩት፡፡
“Most probably” ብዙም የኢንተርኔት ተጠቃሚ አይደለም፡፡ ( ኦፍ ላየን ያለው ነገር ደሞ ኦን ላየን ካለው ይበልጥ ተስፋ ያስቆርጣል) አገር ቤትም ሁሉም ሰው ጸጥ ባለበት ዘመን፣ የተቃዋሚ ፓርቲ አባል ለመሆን በመድፈሩ፣ በማህበራዊ ኑሮው በሰፈሩ ብዙ እየከፈለ ነው ፡፡ በጉዞ ደክሞት መሬት ላይ ነው የተኛው። እናም በዚያ ትግል ውስጥ ፓርቲውን ለማዳን ተስፋ አድርጓል፡፡ በማግስቱ ስብሰባውን ሲካፈል የምርጫ ቦርድ ተወካይ ተለጣፌው የ20 ሰው ስብስብ የጠራውን ስብሰባ ለመካፈል በመሄዱ እንደማይመጣ ይሰማል፡፡ ይሄ በራሱ ተስፋ አስቆርጦ ብርር የሚያደርግ ንዴት ይፈጥራል፡፡ ነገር ግን አማራጭ የለም ይሞክራል፡፡ እሁድ ጠዋት አንደማንኛውም ሰው ለልጆቹ ጋር ያለነጻነት፣ ግን በሰላም ማሳለፍ ይችል ነበር፡፡ የሚብሰው ሰሞ የሚከፍለው መስዋእትነት ምናልባት ውጤት የለሽ ሊመስልም ይችላል፡፡ ፓርቲውን ሊያግዱበት ካልሆነም የቀረውን 4 ወር የህጋዊነት ጨዋታ ሲያጫውቱ ከርመው ባለቀ ሰአት ካሻቸው በሉ ተሳተፉ ብለው ሂደቱንም ውጤቱንም ሊቀሙት( ድሮ ውጤት ብቻ ነበር የሚቀሙት) እና ለራሳቸው ጥቅም ሊያውሉት ወይም ደሞ ጭራሽ ሊያባርሩት ይችላሉ፡፡ ግን ማቆም ምርጫ አይደለም፡፡
በአንድነት አባላት እንዴት inspired እነደሆንኩ!
ዝም ብሎ የሚገርመኝ ነገር እንደው እንደኛ በሽብር የተከሰሰ የተሰደደ ሰው ሳይቀር አነዚህ ሰዎች ትንሽ ቦታ ሊከፍቱ ይችላሉ ብሎ ተስፋ አድርጎ ይጠብቃል፡፡ እነሱ ጭራሽ ብቻቸውን ለመሮጥ ( ለማሸነፍ አላልኩም- እሱ ታወቀ ነው) ነው ያቀዱት ፡፡ ህግና ስርአቱ ቀርቶ ይሉኝታና ነውር አንኳን አያውቁም ፡፡
ውጤቱ ቀርቶ ሂደቱ የሚሰጠውን ትርፍራፌ እድል ለመጠቀም አንኳን የማይቻልባት አገር ሆናለች ኢትዮጲያ አሁን፡፡ የዛሬው አይነት ቀን ደሞ ትካዜን ይጨምራል ፡፡ እናም ለዚህ ትካዜ ምክንያት ከሆነኝ ኢህአዴግ በላይ ( አምባገንን አይን አውጣ ምኑ ይተከዝለታል? ) ምርጫ ቦርድ ነን ብለው የተቀመጡ ግለሰቦች ላይ ነበር፡። ማታ እንዴት ይተኛሉ ? እንዴት የሰፈር ሰው እና ጎረቤት ፌት ቀና ብለው ይሄዳሉ ? አንዴት ዴሞክራሲን የሚያህል ስም እና ስራ እየናዱ ፈገግ ይላሉ እያልኩ ሳስብ ነበር፡፡ አንደግለሰብ እንዴት ቢያስቡ ነው ያን ያህል የማይቆቁራቸው ? ( ስሜት እነዳለው ሰው ሳስባቸው ዋልኩ)

10888719_760787797339490_5698232838446960729_n
አንድነት ቢሮ ውስጥ መሬት ላይ ተኝተው የሚታዩት ጉባኤውን ለመስተፍ ከየክፍለሃገሩ የመጡ የአንድነት አባላት
10600483_760787794006157_8891944273890351365_n
አንድነት ቢሮ ውስጥ መሬት ላይ ተኝተው የሚታዩት ጉባኤውን ለመስተፍ ከየክፍለሃገሩ የመጡ የአንድነት አባላት

አቶ ብርሃኑ አዴሎ ከሥልጣናቸው ተነሱ

 

  • 1584
     
    Share





Berehanu Adelo
(ዘ-ሐበሻ) ከጠቅላይ ሚኒስተር ሃይለማርያም ደሳለኝ ጋር በአንድ ላይ የደህዴን ፖሊት ቢሮ አባል የነበሩት አቶ ብርሃኑ አዴሎ ምክንያቱ ባልታወቀ ምክኒያት ድንገት ከስልጣናቸው መነሳታቸውን የዘ-ሐበሻ ምንጮች ገለጹ::
የኢትዮጵያ አዕምሮአዊ ንብረት ጽሕፈት ቤት ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ብርሃኑ አዴሎ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ የካቢኔ ጉዳዮች ኃላፊ ሆነው ይሰሩ የነበረ ሲሆን ከዚያም ቀደም ብሎ የደቡብ ክልል ምክትል የፍትህ ቢሮ ሃላፊ ሆነው ሰርተዋል:: በሌላም በኩል በርከት ያሉ የስርዓቱ ተላላኪዎች ሃገርን በመልካም ሁኔታ የሚመራ ትምህርት ሳይሆን ተንኮል ይማሩበታል በሚባልበት የሲቭል ሰርቭስ ኮሌጅ አስተማሪ ሆነው ያገለግሉ ነበር::
የዘ-ሐበሻ ምንጮች እንደሚሉት ብርሃኑ አዴሎ በሃይለማርያም ደሳለኝ የተፈረመ ደብዳቤ በደረሳቸውና ከስልጣናቸው በተነሱበት ዕለት በርሳቸው ምትክ አቶ ግርማ በጅጋ ተሹመዋል::

ኢህአዴግ ከምርጫ ቦርድ ጋር “የምርጫ ግብረ ኃይል” ጥርነፋ እያካሄደ ነው

"ሰማያዊ፣ አንድነትና መኢአድ ከፓርቲነት ተሰርዘዋል" የብአዴን ካድሬዎች
ብአዴን/ኢህአዴግ በምስራቅ ጎጃም ዞን “የምርጫ ግብረ ኃይል” በሚል አደረጃጀት የምርጫ ቦርድን ስራ እየሰራ መሆኑን የምስራቅ ጎጃም ዞን የሰማያዊ ፓርቲ ፀኃፊ አቶ ሳሙኤል አወቀ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ የብአዴን ካድሬዎች በምስራቅ ጎጃም በተለይም ደብረማርቆስ ከተማ ላይ ቤት ለቤት እየዞሩ ህዝቡ ካርድ እንዲያወጣ በሚቀሰቅሱበት ወቅት የምርጫ ካርድ አልወስድም የሚሉ ዜጎችን “አልወስድም ስትል ፈርም” እያሉ እያወከቡ እንደሚገኙ ኃላፊው ገልጸዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ “የምርጫ ግብረ ኃይል” በተሰኘው መዋቅር የምርጫ ካርድ እንደማይወስዱና እንደማይፈርሙ ስለሚገልጹት ዜጎች ከሌሎች መረጃ በመጠየቅ ለማስፈራራት እየሞከሩ መሆንን ገልጸውልናል፡፡
ከዚህም ባሻገር ካድሬዎቹ በየምርጫ ጣቢያዎቹ ለምርጫ ጽ/ቤት አቅጣጫ እንደሚሰጡ፣ የምዝገባ ሰነዶችም በእነሱ እጅ እንደሆኑና የምዝገባ ሂደቱን እያከናወኑ እንደሚገኙ ተግልጾአል፡፡ ካርድ የማቅረብና የመመዝገብ ኃላፊነት የምርጫ ቦርድ ስራ ሆኖ እያለ ሞጣ አካባቢ የምርጫ ካርድ አለቀ ሲባል በብአዴን ካድሬዎች ትዕዛዝ ከጎዛመን ወረዳ የምርጫ ካርድ ወደ ሞጣ መላኩን በመጥቀስ ብአዴን/ኢህአዴግ ምርጫ ቦርድን ተክቶ እየሰራ መሆኑን ኃላፊ ገልጸዋል፡፡
በሌላ በኩል የብአዴን ካድሬዎች ሰማያዊ፣ አንድነትና መኢአድ ከፓርቲነት ተሰርዘዋል እያሉ እያስወሩ እንደሚገኙ የተገለጸ ሲሆን በተለይ በየገጠሩ “ሰማያዊ ፓርቲ እውቅና የለውም፡፡ እውቅና ከሌላቸው ሌሎች ፓርቲዎች ጋርም ህገ-ወጥ ትብብር ፈጥሮ እየሰራ ነው፡፡ በመሆኑም ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር ከመስራታችሁ በፊት ህገ-ወጥ መሆኑን ልታውቁት ይገባል፡፡ ራሳችሁን ችግር ላይ እንዳትጥሉ” እያሉ እየቀሰቀሱ መሆኑን አቶ ሳሙኤል አወቀ ገልጸዋል፡፡ በተለይ በሰማያዊ ፓርቲ ላይ ዘመቻ ተከፍቷል ያሉት ፀኃፊው ብአዴኖች በከተማና በገጠር በሚኖረው ህዝብ ውዥንብር ለመንዛት እየጣሩ እንደሆነ ታዝበናል ብለዋል፡፡

የአንድነት ፓርቲ ሴቶች ጉዳይ ምክትል ኃላፊ ከፍተኛ ድብደባ ተፈፀመባት

ነፍሰጡር መሆኗ እየታወቀ ደብዳቢዎቹ ሆዷን በመርገጥ ደብድብዋታል
ወይዘሪት ወይንሸት፣ ንፋስ ስልክ አካባቢ ማንነታቸው ባልታወቁ ሁለት ሰዎች ከረፋዱ 5፡30 ላይ ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈፀመባት ለፍኖተ-ነፃነት የደረሰው መረጃ ያመላክታል፡፡
ወይዘሪት ወይንሸት፣ ነፍሰጡር መሆኗ የሚታወቅ ሲሆን ደብዳቢዎቹም ሆዷን በመርገጥ ድብደባውን ሲፈፅሙባት እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡ ደብዳቢዎቹ ድብደባውን ፈፅመው የተሰወሩ ሲሆን ወይዘሪት ወይንሸት፣ በአሁኑ ሰዓት ራሷን ስታ ሆስፒታል መግባቷን ለማወቅ ተችሏል፡፡
ወይንሸት፣ አንድነት ፓርቲ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ለማካሄድ በጠራው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በከፍተኛ ድምፅ የአስመራጭ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሆና በመመረጥ በምርጫው ላይ ጉልህ ሚና በመጫወት ድርሻዋን መወጣቷ ይታወሳል፡፡ በእለቱ በተካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በአንድነት ስም የሚነግዱትን ግለሰቦች በማውገዝ አስተያየቷን መሰንዘሯን ተከትሎ ድብደባው ሊፈፀምባት እንደተቻለ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ወይዘሪት ወይንሸት፣ በፓርቲው ውስጥ ንቁ ተሳትፎ ያላት ወጣት ከመሆኗም በተጨማሪ የአንድነት ፓርቲ ሴቶች ጉዳይ ምክትል ሀላፊ በመሆን በመስራት ላይ ትገኛለች፡፡ በዚህ ሳምንት ብቻ በአንድነት አባላት ላይ ድብደባ ሲደርስ ለሁለተኛ ጊዜ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ባለፈው እሁድ በአቶ መሳይ ትኩ፣ ላይ ድብደባ መፈፀሙ ይታወሳል፡፡mesay
በተመሳሳይ ዜና አንድነት ፓርቲ በጠራው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ተገኝቶ የነበረው አቶ መሳይ ትኩ፣ ከጉባኤው ወጥቶ ወደ መኖሪያ ቤቱ በሚያቀናበት ወቅት፤ ፒያሳ ራስ መኮንን ድልድይ አካባቢ በሚገኝ የኮሚኒቲ ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ በፖሊሶች ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈፀመበት ገልጿል፡፡
አቶ መሳይ ትኩ፣ ባለፈው ሳምንት “አንድነትን” ከገዢው ፓርቲ ጋር በመመሳጠር ለማፍረስ ሲሰሩ የነበሩት ግለሰቦችን ሴራ በማጋለጡ የተነሳ፤ በእነዚሁ ግለሰቦች ጠቋሚነት እና ግብረ-አበርነት በዛሬው እለት በከባድ ሁኔታ እንዲደበደብ ምክንያት ሆኗል፡፡ ከግብረ-አበሮቹ መሃል ዳንኤል ሙላት የተባለው (ቅድስተ ማርያም አካባቢ ነዋሪ የሆነው) ግለሰብ ክትትል ሲያደርግበት እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡

Monday 12 January 2015

የሕወሓት አስተዳደር ተለጣፊ አንድነት ፓርቲ መመስረቱ… የግንቦትና አርበኞች ግንባር ውህደት መነቃነቅ መፍጠሩ… ባለስልጣናቱ ለውጭ ሚዲያዎች የዋጋ ግሽበት መኖሩን ማመናቸውና ሌሎችም

የህብር ሬዲዮ ጥር 3 ቀን 2007 ፕሮግራም
የኢሳት ኤርትራ መግባትና የአርበኞች ግንባርና የግንቦት ሰባትን ውህደት በተመለከተ ከጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ጋር ቆይታ አድርገናል (ሙሉውን ያዳምጡ)
<…ምርጫ ቦርድ በአራት ቀን ውስጥ ጊባዔ አድርጉ አለ ባልጠበቀው ሁኔታ ከመላው አገሪቱ ጉባዔተኛው መጥቶ ጉባዔው ሲደረግ በስፍራው ሳይገኝ ተለጣፊ አንድነት አቋቁሜያለሁ አለ ። ኢ/ር ግዛቸውን የመረጠው የጠቅላላ ጉባዔ አባላት መካከል ከ209 በላይ ተገኝቶ አቶ በላይ ፈቃዱን መርጧል ሕግ የለም እንጂ ሕግ ቢኖር ያ በቂ ነው ከዚህ በሁዋላ አንድነት ከሚበረከክ ቢፈርስ ይሻላል ….>
አቶ አስራት አብርሃም የአንድነት ተጠባባቂ የሕዝብ ግንኙነት የነበሩ የዛሬውን የአንድነት ጉባዔና የምርጫ ቦርድን ሕገ ወጥ አካሄድ በተመለከተ ከሰጡን ማብራሪያ(ሙሉውን ያዳምጡት)
በፓሪስ የተደረገው የሽብር ጥቃት፣ የመናገር ነጻነትና ተከትሎት የመጡት ጥአቄዎች(ልዩ ዘገባ)
<<የሞት ጉዞ>> መጽሐፍ ደራሲ ከሆነው ጋዜጠኛና ደራሲ ግሩም ተክለሀይማኖትን ካለበት የመን እንዲሁም የ <<ምስጦቹ>> መጽሐፍ ደራሲ ተዘራ ታምራትን ከግብጽ ካይሮ ስለ መጽሐፋቸው አወያይተናል (ሙሉውን ያዳምጡት)
ሌሎችም
ዜናዎቻችን
በኢትዮጵያ ያለው የዋጋ ግሽበት እየጨመረ መሔዱን የአገዛዙ ባለስልጣናት ለውጭ ሚዲያ አመኑ
በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነው ጥንታዊው ጣይቱ ሆቴል ዛሬ በተነሳው የእሳት ቃጠሎ ከፍተኛ ውድመት ደረሰበት
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ጋና ላይ ተከስክሶ ወደቀ
አንድነት ፓርቲ በአስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤው ፕሬዝዳንቱን ደግሞ መረጠ
ምርጫ ቦርድና ሕውሓት በጋራ አንድነት የሚል ተለጣፊ ድርጅት ፈጥረው ፕሬዝዳንት ያሉት ተመረጠ
በተለጣፊው አንድነት ምርጫ ላይ አባላት ያልሆኑና የደህንነቱ መ/ቤት ሰዎች በአካባቢው እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል
ትንሳኤ ኢህአፓ በድርጅቱ ስም የሚንቀሳቀሱት ቡድኖች ከእርስ በእርስ ጥሎ ማለፍ ለፀረ ወያኔ ትግሉ ቅድሚያ በመስጠት ዛሬም አንድ ላይ እንዲመጡ ጠየቀ
የግንቦት ሰባትና የአርበኞች ግንባር ውህደት በአገር ውስጥና በውጭ መነቃቃት እየፈጠረ ነው

Andargachew Tsigie Before the T-TPLF Inquisition?

Monday, January 12, 2015 @ 02:01 AM Alma
Andy Tsgie
“Cirque d’Andargachew” presented by the Ringling T-TPLF Brothers
Voltaire (François-Marie Arouet) is often credited with the observation that one should “judge a man by his questions rather than his answers.”
Voltaire also wisely observed, “All murderers are punished unless they kill in large numbers and to the sound of trumpets.” How true! The late Meles Zenawi and the Thugtatorship of the Tigrean People’s Liberation Front (T-TPLF) have murdered thousands of people in Ethiopia and gotten away to the merry trumpets of their Western bankrollers.
Last week, the T-TPLF released a 10-minute and 31-second amateurishly stitched video of “answers” given by Andargachew Tsigie to unstated questions put to him by a faceless  interrogator(s), and expressly invited viewers to render a “judgment of conscience”.
In July 2014, the T-TPLF successfully plotted with the Yemeni regime to arrange the extraordinary rendition (kidnapping) of Andargachew Tsigie, who is the General Secretary of the Ethiopian opposition group known as Ginbot 7 Movement for Justice, Freedom and Democracy. In 2009 and 2012, the T-TPLF tried Andargachew in absentia on trumped up terrorism charges in kangaroo (monkey) court proceedings and sentenced him to death.
I condemned Andargachew’s outrageous and illegal abduction in Yemen in my commentary entitled, “Ethiopia: The Crime of Extraordinary Rendition”.   
Andy TsgieAndargachew is a British national of Ethiopian origin. It is a shame he is a British national in name only. The British Government has done absolutely nothing to secure his release or to ensure that he is not subjected to abuse and mistreatment at the infamous  Meles Zenawi Prison.  For over six months, the British Government has been twiddling thumbs as Andargachew is trotted out for exhibition in the Ringling T-TPLF Brothers media circus freak show.
The British Government has completely failed in its obligations to protect Andargachew under the 1963 Vienna Convention on Consular Relations. The British Government speaks with forked tongue on the issue of protection of its nationals who need assistance abroad. British officials say “provision of assistance by consular officials or diplomatic authorities to nationals in difficulty overseas” is their bedrock policy. They also say consular assistance is not a legal right to which UK nationals are entitled:  “The UK Government is under no general obligation under domestic or international law to provide consular assistance (or exercise diplomatic protection).”  They further claim consular intervention to protect their nationals abroad facing or likely to face torture is an integral to the British Government’s anti-torture strategy. The English aristocrat, writer, poet and soldier Sir Walter Raleigh aptly remarked, “O, what a tangled web we weave when first we practise to deceive!”
The British Foreign Office knows Andargachew has been sentenced to death twice in the T-TPLF’s kangaroo (monkey) courts and highly like to face torture. All it has done so far is express regrets and issue fuzzy and equivocal statements about making “consistent requests for information from the Yemeni authorities”, complain about the “the lack of any notification of his detention in contravention of the Vienna convention” and express “our concerns about the death penalty that Mr. Tsige could face in Ethiopia.” According to one report, “Mr. Simmonds (Africa Minister) expressed deep concern that the Ethiopian authorities had not allowed consular access.”
“Whoopty freaking doo!”, as Yankees like to say. Big deal! Nice display of Crocodile tears by the British Foreign Office. I (don’t) wonder if there is a double standard in the protection of British citizens facing torture based on whether they are first class or second-class citizens. Let me cut to the chase.What has the British Government done to secure the rights or release of one of its second class citizens abused by thugs in Ethiopia?  Bloody ‘ell, nothing!
Anyway, back to the T-TPLF and its media Cirque d’Andargachew

ኦኬሎ አኳይ እጅና እግራቸውን ታስረው ጨለማ ክፍል መታሰራቸው ተገለጸ

እስክንድር ነጋ ከቤተሰብ ውጭ ጠያቂ ተከልክሏል
okello a