Friday 24 January 2014

ከቃሊቲና ቂሊንጦ እስር ቤቶች በላይ የሚያንጸባርቁ ከዋክብት -ዳዊት ከበደ ወየሳ፣ አትላንታ

(ይህ ጽሁፍ የርዕዮት አለሙ የልደት በአል በአዲስ አበባ በተከበረበት ወቅት; ከውጭ አገር ንግግር እንዳደርግ በተጋበዝኩበት ወቅት… የስራ ባልደረቦቼን እስክንድር, ውብሸት እና ርዕዮትን በማሰብ የተዘጋጀ ነው)
ይህ ሳምንት የታላቁ ማርቲን ሉተር ኪንግ የልደት በአል በመላ አሜሪካ የሚከበርበት ነው:: በአሜሪካ ከክርስቶስ ልደት ቀጥሎ ስራ እና ትምህርት ቤት ተዘግቶ ልደቱ የሚከበርለት አንድ ሰው ቢኖር ማርቲን ሉተር ኪንግ ብቻ መሆኑን ልብ ይበሉ:: የማርቲን ሉተር ኪንግ የልደት በአል በሚከበርበት ወቅት በህይወት ዘመኑ ለጥቁር ህዝብ ነጻነት ያደረገው አስተዋፅኦ ይታወሳል:: በህይወት በነበረበት ወቅት ለሰው ልጅ እኩልነት ተሟግቷል; የነጻነት ቀንዲልን ለኩሷል:: ሆኖም እኩልነት እና ነጻነትን ሳያጣጥም በበርሚንግሃም እስር ቤት ተጥሎ ፍዳውን እንዲቆጥር ተፈርዶበት ነበር:: በመጨረሻም የሰውን ልጅ ክብር እና ነጻነት በማይደግፉ ሰዎች ህይወቱ ማለፉ ይታወቃል – መልካም ስራዎቹ ግን አላለፉም::
ዛሬም በአገራችን ስለፍትህ, ስለነጻነት የሰበኩና የደሰኮሩ; የጻፉና የመሰከሩ… ለሃቅ ቆመው፣ ግፍ የተሰራባቸው፣ ከአገር የተሰደዱና የወጡ፤ በግፍ ሰንሰለት ለጨለማ እስር የተዳረጉ ወገኖቻችን ብዙ ናቸው:: እስክንድር፣ ውብሸት፣ ርእዮት፣ አንዷለም እና ሌሎች ኢትዮጵያውያን ራሳቸውን በሰብአዊነት መሰረት ላይ ስላነጹ እና ሃሳባቸውን በነጻነት ስለገለጹ መጨረሻቸው እስር እና እንግልት ሆኗል::
እንደ እውነቱ ከሆነ ሃሳብን በነጻነት መግለጽ… ብሎም የህዝብ ልሳን ሆኖ ለህዝብ የቤዛነት ዋጋ መክፈል የሚያስከብር እንጂ የሚያሳስር አልነበረም:: በመሆኑም ለነጻ ፕሬስ መክፈል የሚገባቸውን ዋጋ ከመጠን አሳልፈው የከፈሉት፤ ርዕዮት አለሙ፣ እስክንድር ነጋ እና ውብሸት ታዬ… ሶስቱም ከአገራቸው አልፈው በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅና አግኝተዋል:: በአለም አቀፍ ደረጃም በልዩ ልዩ አለም አቀፍ የጋዜጠኞች ማህበራትና ተቅውውማት ለሽልማት ታጭተው አሸናፊ ሆነዋል::
የ’ነዚህ የስራ ባልደረቦቼ ብዕር… ህዝብን ሳይሆን የተወሰኑ ወገኖችን አሸብሮ ሊሆን ይችላል:: እነርዕዮት አለሙ በዚህ አይነት ሰበብ አስባብ በቃሊቲ እና በቂሊንጦ እስር ቤት ታግተው፤ ነጻነታቸውን አጥተውና ህክምና ተነፍገው ይታሰሩ እንጂ፤  ለእውነት የቆሙ ወገኖች ግን ለመልካም ስራቸው ሽልማትን አልነፈጓቸውም::
ማርቲን ሉተር ኪንግ በበርሚንግሃም እስር ቤት ታስሮ ቢማቅቅም የአሜሪካም ሆነ የአለም አቀፉ ማህበረሰብ አልዘነጋውም:: ቆይቶም ቢሆን የአለም አቀፉ ኖቤል ተሸላሚ እስከመሆን ደርሷል:: ዛሬ በእስር ላይ የሚገኙት የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች የኖቤል ተሸላሚ ባይሆኑም አለም ግን አልረሳቸውም:: ከታሰሩበት የጨለማ ወህኒ ቤት ጀርባ፤ ከብረት ፍርግርግ እና ከግድግዳዎቹ ባሻገር በመቶዎች፣ በሺዎች እና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች እነዚህን ጋዜጠኞች በመልካም ስራቸው ያስታውሷቸዋል; ይዘክሯቸዋል:: ስለሆነም የጻድቃን ሞት፤ የሰማዕትነት ጽድቅ ተደርጎ እንደሚቆጠረው ሁሉ… የነ እስክንድር፣ ውብሸትና ርዕዮት እስር፤ ከቶውኑ ዋጋ ቢስ እና ፍሬ አልባ ሊሆን አይችልም::
ኢትዮጵያ ውስጥ በነበርኩበት ወቅት በፕሬስ ጉዳይ ተደጋጋሚ የሆነ እስር ደርሶብኛል:: በ’ነዚህ የእስር እና እንግልት ጊዜያት ግን… ከጨለማው እስር ቤት ማዶ ለምን እንደታሰርኩ የሚረዱ ሺዎች በመኖራቸው ሁልጊዜ እጽናና ነበር:: በተደጋጋሚ እስር ቤት እየመጣ የሚጠይቀኝ እና የዋስ መብቴን አስጠብቆ ከእስር እንድወጣ ያደርገኝ የነበረው ወላጅ አባቴ፤ “የታሰርከው ሰርቀህ ወይም ሌላ ወንጀል ሰርተህ ሳይሆን፤ እውነትን ስለተናገርክ ነው:: ስለዚህ አንገትህን ቀና ልታደርግ እንጂ ልትሸማቀቅ አይገባህም::” የሚል አጽናኝ ቃል ሁሌ ይነግረኝ ነበር:: ዛሬ አባቴ በህይወት የለም:: ቃሉ እና ምክሩ ግን አብሮኝ አለ:: በእስር ላይ ለሚገኙ የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች፤ “አንገታችሁን ቀና አድርጉ!” የሚለውን መልዕክት አጋራቸዋለሁ::
ዛሬ በጋዜጠኞቻችን ላይ የተለያዩ ክሶች ተመስርቶባቸው መታሰራቸው ሳያንስ; ከታሰሩም በኋላ በሃሰት ሊወነጅሏቸው የሚሹ ብዙ ግራ ዘመም ሰዎች መኖራቸውን ታዝበናል:: በአሜሪካ ከፍተኛ የአየር ሽፋን አግኝቶ ዲሞክራቶችን በመሳደብ የሚታወቀው ራሽ ሊምቦ የተባለ ጋዜጠኛ በቅርቡ ኔልሰን ማንዴላ በሞት ሲለዩ… “ብታምኑም ባታምኑም ኔልሰን ማንዴላ አሸባሪ ነበሩ::” ብሎ ሰፊ ሙግት ፈጥሮ ነበር:: ይህ አባባሉ ለኛ እና ለሌሎች አፍሪቃውያን ሊገርመን ይችል ይሆናል:: ነገር ግን የራሳቸው አመዛዛኝ ህሊና ያልፈጠረባቸውና ይህን ሰው በጭፍን የሚከተሉት ሰዎች “አዎ ማንዴላ አሸባሪ ነበሩ” ብለው ቢሉ ሊገርመን አይገባም::
ዛሬም ባገራችን በተመሳሳይ መልኩ የነርዕዮት አለሙን መልካም ስም ጥላሸት ለመቀባት እላይ ታች የሚሉ ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ… እኛ ግን እንላለን:: “ወንጀል አልሰራችሁምና አንገታችሁን ቀና አድርጉ!” ስማችሁ ከቃሊቲና ከቂሊንጦ እስር ቤቶች በላይ፤ በጠራው ሰማይ ላይ ያንጸባርቃል፤ ቃለ ሃቃቹህ በአየር ናኝቶ… ኢትዮጵያዊያን ባሉበት ሁሉ በመላው አለም ላይ ተሰራጭቷል::
የማርቲን ሉተር ኪንግ ልደት ሲከበር መልካም ስራዎቹ እንደሚወደሱ ሁሉ፤ ዛሬም ሆነ ወደፊት የነርእዮት አለሙ ልደት ሲከበር መልካም ስራዎቻቸው በተደጋጋሚ ይነሳሉ ይዘከራሉ:: ዛሬ ማንዴላን አሸባሪ ብለው የሚከሱ ሰዎች እንደመኖራቸው መጠን; በተመሳሳይ መልኩ ለነርእዮት አለሙ ተመሳሳይ ስም የሰጡና ያሰጡ… ለመስጠት እና ለማሰጠት የሚጥሩ ሰዎች አሉ:: እኛ ግን የተለኮሱ ሻማዎች ይዘን ልደት ስናከብር; የብርሃናችን  ጮራ፤ ሌሎች የፈጠሩትን የጨለማ ድባብ ሰንጥቆ… አንዳች ብርሃን እንደሚፈነጥቅላቸው በማመን ነው:: ዛሬ የርዕዮት አለሙን የልደት ቀን ስናከብር፤ ያለፍትህ የታሰሩትን ፍትህ የሚፈልጉትን፤ ነጻነት የተጠሙትን ነፍሶች በማሰብ ጭምር ነው::
መልካም ልደት – ርዕዮት!

Ethiopia’s teff poised to be next big super grain – The guardian

Rich in calcium, iron and protein, gluten-free teff offers Ethiopia the promise of new and lucrative markets in the west – The guardian.
 and  in Addis Ababa
MDG : Mounds of teff grain dry in fields in Ethiopia
Mounds of teff dry in fields in Ethiopia. The gluten-free grain is used to make flour for injera, the national dish. Photograph: Julio Etchart/Alamy
At Addis Ababa airport, visitors are greeted by pictures of golden grains, minute ochre-red seeds and a group of men gathered around a giant pancake. Billboards boast: “Teff: the ultimate gluten-free crop!”
Ethiopia is one of the world’s poorest countries, well-known for its precarious food security situation. But it is also the native home of teff, a highly nutritious ancient grain increasingly finding its way into health-food shops and supermarkets in Europe and America.
Teffs tiny seeds – the size of poppy seeds – are high in calcium, iron and protein, and boast an impressive set of amino acids. Naturally gluten-free, the grain can substitute for wheat flour in anything from bread and pasta to waffles and pizza bases. Like quinoa, the Andean grain, teff’s superb nutritional profile offers the promise of new and lucrative markets in the west.
In Ethiopia, teff is a national obsession. Grown by an estimated 6.3 million farmers, fields of the crop cover more than 20% of all land under cultivation. Ground into flour and used to make injera, the spongy fermented flatbread that is basic to Ethiopian cuisine, the grain is central to many religious and cultural ceremonies. Across the country, and in neighbouring Eritrea, diners gather around large pieces of injera, which doubles as cutlery, scooping up stews and feeding one another as a sign of loyalty or friendship – a tradition known as gursha.
Outside diaspora communities in the west, teff has flown under the radar for decades. But growing appetite for traditional crops and booming health-food and gluten-free markets are breathing new life into the grain, increasingly touted as Ethiopia’s “second gift to the world”, after coffee.
Sophie Kebede, a London-based entrepreneur who, with her husband, owns Tobia Teff, a UK company specialising in the grain, says she was “flabbergasted” when she discovered its nutritional value. “I didn’t know it was so sought after … I am of Ethiopian origin; I’ve been eating injera all my life.”
The gluten-free market is the backbone of Kebede’s business. Today, Planet Organic shops in London stock 1kg bags of Tobia Teff flour (£7 each), while 300g packets of its teff breakfast cereal sit alongside milled flaxseed and organic, sugar-free Swiss muesli, and cost £5.44 The company also sells readymade, gluten-free teff bread with raisin, onion, sunflower and other varieties. (Teff is available at other UK stockists).
As western consumers acquire a taste for teff, how to ensure that Ethiopia and its farmers benefit from new global markets is a critical question. Growing demand for so-called ancient grains has not always been a straightforward win for poor communities. In Bolivia and Peru, reports of rising incomes owing to the now-global quinoa trade have come alongside those of malnutrition and conflicts over land as farmers sell their entire crop to meet western demand.
MDG : Mama Fresh Injera teff factory in Addis, EthiopiaThe tiny seeds are rich in nutrients. Photograph: Elissa JobsonEthiopia’s growing middle class is also pushing up demand for teff, andrising domestic prices over the past decade have put the grain out of reach of the poorest. Today, most small farmers sell the bulk of what they grow to consumers in the city.
This may have helped boost incomes in some rural areas but it has hadnutritional consequences, says the government, as teff is the most nutritionally valuable grain in the country. Estimates suggest that while those in urban areas eat up to 61kg of teff a year, in rural areas, the figure is 20kg. The type consumed differs too: the wealthy almost exclusively eat the more expensive magna and white teff varieties; less well-off consumers tend to eat less-valuable red and mixed teff, and more than half combine it with cheaper cereals such as sorghum and maize.
The Ethiopian government wants to double teff production by 2015. Its strategy, published in 2013, argues that the grain could play an important role in school meals and emergency aid programmes, and help reduce malnutrition – particularly among children and adolescents.
It notes that teff is also gluten-free, so it is well suited to address growing global gluten-free demand, and calls on companies to start testing, promoting and mass manufacturing teff-based products such as cakes and biscuits.
Though Ethiopia has a fast-growing economy, it remains on the UN’s list of least-developed countries. An estimated 20% of under-fives are malnourished or suffer stunted growth, and the UN’s World Food Programme estimates the costs of chronic malnutrition could be worth 16.5% of GDP.
The government’s agricultural transformation agency aims to boost yields by developing improved varieties of the grain, along with new planting techniques and tools to reduce post-harvest losses.
The Syngenta Foundation, the non-profit arm of the Swiss seeds and pesticides company, has also joined the quest for increased teff production.
Government restrictions, instituted in 2006, forbid the export of raw teff grain, only allowing shipments of injera and other processed products. But this could change: the goal is to produce enough teff for domestic consumption and a strong export market, according to the government’s strategy.
In Addis Ababa, the Ethiopian capital, dozens of women painstakingly sift and mill teff at the factories of Mama Fresh Injera, one of the few domestic companies that exports teff products.
MDG : Mama Fresh Injera teff factory in Addis, EthiopiaThe Mama Fresh factory in Addis Ababa. The family firm has set its sights on the gluten-free market in the west. Photograph: Elissa JobsonMama Fresh is a family firm that has been selling injera to top restaurants and hotels in the Ethiopian capital for years. It also ships the flatbread to Finland, Germany, Sweden and the US, primarily for consumption by diaspora communities. But the company has its eye on the gluten-free market. It aims to double exports to America in 2014, and will soon start producing teff-based pizzas, bread and cookies.
David Hallam, trade and markets director at the UN’s Food and Agriculture Organisation, says while there is money to be made from new global markets for traditional crops, governments have to support small-scale producers to ensure they share the benefits of increased trade.
“Typically, these products are going to go through many hands before they reach the shelves of Sainsbury’s or wherever. There are [profit] margins at every step, and small farmers are not necessarily well placed to bargain with the bigger traders,” says Hallam, who sees quinoa’s popularity as a cautionary tale of how export opportunities can be a mixed blessing for poor countries.
Regassa Feyissa, an Ethiopian agricultural scientist and former head of the national Institute for Biodiversity, warns that without careful planning, increased teff production for export may displace other important crops for farmers. And efforts to boost production could benefit business interests at the expense of small farmers.
With little Ethiopian teff on the international market, farmers in the US have started planting the crop. Farmers in Europe, Israel and Australia have also experimented with it.
Kebede says she gets her grain from farms in southern Europe, though she would prefer to source it from Ethiopia. “Teff is second nature to an Ethiopian; so who better to supply it? We have this sought after grain being grown in the country, so why can’t an Ethiopian farmer benefit from this?”

በይርጋጨፌ መምህራን ለሁለተኛ ጊዜ የስራ ማቆም አድማ አደረጉ

ኢሳት ዜና :-ለአባይ ግድብ ማሰሪያ በሚል ያለፍላጎታቸው ደሞዛቸው የተቆረጠባቸው የይርጋ ጨፌ ሁለተኛ ደረጃ መምራህራን ከወር በፊት የስራ ማቆም አድማ ማድረጋቸውን ተከትሎ ፣ የተቆረጠባቸው ደምዞ ተመልሶ እንደሚሰጣቸው ቃል ተገብቶላቸው የነበረ ቢሆንም፣ የወረዳው አስተዳዳሪ ገንዘቡ በዝግ አካውንት የገባ በመሆኑ፣ ገንዘብ ለመክፈል አንችልም በሚል ምላሽ መስጠታቸውን ተከትሎ መምህራኑ ከትናንት ጀምሮ የስራ ማቆም አድማ አድረገዋል። አድማው ዛሬም የቀጠለ ሲሆን አስተዳደሩ ከመምህራኑ ጋር ለመነጋገር ስብሰባ ጠርተዋል። ይህን ዘገባ እስካጠናከርንብ ጊዜ ድረስ የስብሰባው ውጤት ምን እንደሆን ለማወቅ አልተቻለም።
መምህራኑ የትምህርት ጊዜውን አጠናቀው ፈተና ለመስጠት ዝግጁ በሚሆኑበት ወቅት የጀመሩት የስራ ማቆም አድማ መስተዳድሩን ማስደንገጡ ታውቋል። አንዳንድ መምህራን ስራ እንዲጀምሩ ለማባበል ባለስልጣናቱ እየተራወጡ ቢሆንም፣ መምህራኑ ግን አሻፈረን ብለዋል። ደመዞቻው እስከ ሳምንቱ መጨረሻ የማይከፈላቸው ከሆነም ሰኞ አድማውን እንደሚቀጥሉበት ገልጸዋል።
ተመሳሳይ የስራ ማቅም አድማ እድርገው የነበሩ የዲላ መምህራን የተቆረጠባቸው ደሞዝ ተመልሶ እንዲሰጣቸው በመደረጉ ስራ ለመጀመር ችለዋል። በዚህ የተበረታቱት የይርጋ ጨፌ ሁለተኛ ደረጃ መምህራን እንደ ዲላ ጓደኞቻችን ያለፈቃዳችን የተቆረጠው ደሞዝ ይመለስልን በማለት ያለፈውን አንድ ወር በስራ ላይ ሆነው ሲጠይቁ ቆይተዋል። በጉዳዩ ዙሪያ የወረዳውን ባለስልጣናት ለማነጋገር ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።

ከቁጫ ችግር ጋር በተያያዘ በአርባምንጭ እስር ቤት የታሰሩ የ232 ሰዎች ስም ዝርዝር ታወቀ

 ኢሳት ዜና :-ከማንነት፣ ከልማትና መልካም አስተዳዳር ጋር በተያያዘ በአርባምንጭ እስር ቤት የታሰሩ የ232 የቁጫ ወረዳ ነዋሪዎች ስም ዝርዝር የወጣው ከራሳቸው ከእስረኞች ነው። ለኢሳት ከተላከው ስም ዝርዝር ለመረዳት እንደተቻለው አብዛኞቹ እስረኞች አርሶ አደሮች ቢሆኑም፣ 5 የሃይማኖት አባቶች፣ 7 መምህራን፣ 6 ነጋዴዎች፣ 25 ተማሪዎች፣ 22 በልዩ ልዩ የመንግስት ስራ ላይ የሚገኙ፣ 5 መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ውስጥ የሚሰሩና አንድ ፖሊስ ይገኙበታል።
ከእስረኞች መካከል 27ቱ እድሜያቸው ከ60 እስከ85 የሚጠጋ ሲሆን፣ አብዛኞቹ ከ50 በታች ናቸው።፡ በጸታ ደረጃ ደግሞ 7ቱ ሴቶች ናቸው። በትምህርት ደረጃም ፒ ኤች ዲ፣ ማስተርስ እና የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው ምሁራን ታስረዋል።
ካልተሰሩት ነገር ግን ከስራ የተሰናበቱ 6 ፖሊሶች በዝርዝር ውስጥ ሲካተቱ፣ ከ20 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ከስራ መባረር እስከ ወር ደሞዝ ቅጣት እንደደረሰባቸው ተመልክቷል። 17 ሰዎች ደግሞ የእስር ጊዜያቸውን አጠናቀው በተለያየ ቅጣት ተለቀዋል።
የስም ዝርዝሩ ከሰኔ 28/2005 ዓ.ም እስከ ጥር 13/2006 ዓ.ም ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ የታሰሩና የተከናወኑ ድርጊቶችን የሚዘረዝር ነው።
በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን የጠየቅናቸው የአንድነት ፓርቲ የደቡብ ክልል ተወካይ አቶ ዳንኤል ሽበሺ  በእስር ላይ የሚገኙት የቁጫ ነዋሪዎች ከ400 በላይ ይደርሳሉ

Tuesday 21 January 2014

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዜና አቀራረብ ጋዜጠኞችን ብቻ ሳይሆን አንባቢን ያሳፍራል – ታደሰ ብሩ

የኢዜአ ማደናገሪያ ዜና – አንድ ተጨባጭ ምሳሌ
January 20, 2014
ታደሰ ብሩ
በቅድሚያ የሚከተለውን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎትን (ኢዜአ) ዜና አጣጥሙልኝ።
ጎባ ጥር 10/2006
በባሌ ዞን ከእርሻ ስራ በተጓዳኝ በንብ ማነብ ፓኬጅ የተሳተፉ አርሶ አደሮች ከ53 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ ማግኘታቸውን የዞኑ የእንስሳት ሀብት ልማትና ጤና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
በጽህፈት ቤቱ የእቅድና ግምገማ በለሙያ አቶ ታዬ ኣጋ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ባለፉት ስድስት ወራት የማር ምርቱን ለአካባቢው ገበያ ያቀረቡት ከ89ሺ 200 የሚበልጡ አርሶ አደሮች ናቸው ።
የማር ምርቱን ለአካባቢያቸውና ለሀገር ውስጥ ገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ከሆኑት አርሶ አደሮች መካከል ከ21 ሺህ 699 የሚበልጡት ሴቶች መሆናቸውንም አብራርተዋል ።
በዞኑ ዘጠኝ ደጋማ ወረዳዎች ውስጥ የሚገኙ አርሶ አደሮች የማር ምርቱን የሰበሰቡት ከ100ሺ ከሚበልጡ ባህላዊ፣ የሽግግርና ዘመናዊ የንብ ቀፎዎች በመጠቀም እንደሆነ አብራርተዋል ።
በዞኑ ባለፉት ስድስት ወራት ለገበያ የቀረበው የማር ምርት ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ1ሺህ ኪሎ ግራም ብልጫ ያለው እንደሆነም አስታውቀዋል ።
ጽህፈት ቤቱም የዞኑን አርሶ አደሮች የማር ምርትና ምርታማነት በሁለት እጥፍ ለማሳደግ ዘመናዊ የንብ ቀፎዎችን ለአርሶ አደሮቹ በማሰራጨት ላይ እንደሆነም ጠቁመዋል ።
ይህንን ዜና እዚህ ያገኙታል።
ዜናውን በጥንቃቄ ያላነበበ ሰው የተለመደ ልማታዊ ዜና በመሆኑ ምንም የሚያስደንቅ ነገር አያገኝበትም። ሆኖም ትንሽ ስሌት ብጤ እንጨምርበት።
ሀ. ከሽያጭ የተገኘው ገንዘብ 53.7 ሚሊዮን: ብር 53, 700, 000
ለ. የአምራቾቹ ብዛት: 89, 200 ገበሬዎች
ሐ. የፈጀባቸው ጊዜ: 6 ወር
ከዚህ በመነሳት የሚከተለውን ማስላት ይቻላል።
የአንድ አምራች አማካይ የሽያጭ ገቢ: 53, 700, 000 ÷ 89, 200 = ብር 602.02
የአንድ አምራች አማካይ ወርሃዊ የሽያጭ ገቢ: 602.02/ 6 = ብር 100.34
በዚህ “ድንቅ ስኬታማ ፓኬጅ” አንድ ገበሬ በወር በአማካይ የሚያገኘው የሽያጭ ገቢ ብር 100.34 ነው። በአማካይ ማለት ደግሞ ከዚህም በታች የሚያገኙ ብዙ አሉ ማለት ነው። በተለይ አንድ ብርቱ “ልማታዊ” ገበሬ ካለ የሌሎቹ ሰብስቦ ነው የሚወስደው። ለማንኛውም ግን የገበሬዎች ምርታነት እኩል ነው ብለን እናስብና ስሌታችንን በአማካይ እንቀጥል።
አንባቢ እንደሚያውቀው የሽያጭ ገቢ የተጣራ ገቢ (ወይም ትርፍ) አይደለም። ገበሬዎች ከዚህ ፓኬጅ ምን ያህል እንደተጠቀሙ ለማስላት ወጪያቸው መሰላትአለበት። ከዜናው በመነሳት በአዕምሮዓችን የሚመጡ ወጪዎች የሚከተሉት ናቸው።
እያንዳንዱ ገበሬ በአማካይ በወር ምን ያህል ሰዓታት በዚህ ሥራ ላይ አዋለ?
“ከ100ሺ ከሚበልጡ ባህላዊ፣ የሽግግርና ዘመናዊ የንብ ቀፎዎች” በሥራ ላይ ውለዋል። የእነዚህ ቀፎዎች የእልቀት ዋጋ (depreciation) በወር ምን ያህል ነው?
(በነገራችን ላይ ይኼ ራሱ ሌላ ዜና የሚወጣው ነገር ነው። በአገሪቱ ትልቁ የዜና አገልግሎት በትላልቅ ፎንት ዜና የሠራለት “ፓኬጅ” ለአንድ ገበሬ በአማካይ ሁለት ቀፎ እንኳን ሳያቀርብ ነው። ለ 89,200 ሰው 100, 000 ማለትም በአማካይ ለአንድ ገበሬ 1.12 ቀፎ ነው!)
ማሩ በምን ታሸገ? (ስልቻም ከሆነ የስልቻው ዋጋ)
ማሩ በምን ተጓጉዞ ገበያ ደረሰ?
የገበሬን ድካም ለሚያውቅ ወጪዎቹ እነዚህ ብቻ እንደማይሆኑ ይረዳል፤ ግን ይብቃኝ።
ይህንን ሁሉ ስናስብ ነው ዜናው እጅግ አስገራሚ የሚሆነው። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዜና አቀራረብ ጋዜጠኞችን ብቻ ሳይሆን አንባቢን ያሳፍራል። ይህንን ዜና ሳነብ የተሰማን ስሜት እፍረት ነው። ይህ ነው የኢዜአ ልማታዊ ጋዜጠኝነት!!!
የኢዜአ ስኬትን የማጋነን ፍላጎት፤ ማለትም የተገኘው ገንዘብ እና በፓኬጁ የተሳተፉ ገበሬዎችን ብዙ አድርጎ የማቅረብ ፍላጎት፣ ብዙ ሲካፈል ብዙ ትንሽ የሚሆን መሆኑ ያስረሳው ይመስለኛል።

የወያኔ ነፍስ በበረከት ስምዖን በኩል ስትቃዥ

January 21, 2014
ነፃነት ዘለቀ (አዲስ አበባ)
አንደኛው መስከረም ጠብቶ ሌላኛው መስከረም እስኪጠባ ድረስ ባሉት የ365.25 ቀናት ውስጥ ስንት ጉድ መስማት እንዳለብን የሚጠቁም አሃዛዊ መረጃ ሊኖር እንደማይችል መቼም ግልጥ ነው፤ ነገር ግን የዘመናችን ኢትዮጵያ የታሪክ ጎርፍ ያመጣብን ከወያኔና መሰሎቹ በስተቀር ሌሎቻችን ያልጠበቅነው ዱብዕዳ ክስተት ምሥጋና ይንሳውና በዬቀኑ የማንሰማውና የማናየው ዕንቆቅልሽ እንዳይኖረን ሆነናል፡፡ በዚህ መልክ በተለይ ባለፉት 22.8 ዓመታት ውስጥ የታዘብነው የታሪክ ምፀትና ወኔያዊ የውሸት ስንክሳር በረጂሙ ታሪካችን ታይቶም ሆነ ተሰምቶ እንደማያውቅ ማንም ጤናማ ኅሊና ያለው ዜጋ የሚመሰክረው ይመስለኛል፡፡ ለዛሬ አንዱን የወያኔ ነጭ ውሸት እንመለከታለን፡፡Bereket Simon, Woyanne propaganda chief
በነገራችን ላይ ወያኔና እውነት ዐይንና ናጫ መሆናቸውን የማይረዳ ወገን እንደማይኖር እገምታለሁ፡፡ የወያኔን ተፈጥሮ ወያኔ ራሱን ጨምሮ ሁሉም ያውቃል፤ የወያኔ እውነት፣ የእውነት ግልባጭ የሆነችው ሀሰት ናት፡፡ ለወያኔ ውሸት ማለት እውነት ናት፡፡ ለወያኔ እንደእውነት የሚመርና የሚያቅር ነገር የለም፡፡ በተቃራኒው ደግሞ ለወያኔ እንደሀሰት የሚጣፍጥ ምንም ነገር የለም፡፡ ወያኔና እውነት በሂሳባዊ አገላለጽ ‘asymptote’ ናቸው – መቼም ሊገናኙ የማይችሉ ተጻራሪ ኑባሬያት በመሆናቸው፡፡ ወያኔ የሀሰት የህግ ባል ነው፤ የሚለያዩት ወይም የሚፋቱት ከሁለት አንድኛቸው ወይም ሁለቱም ሲሞቱ ብቻ ነው፡፡ ሀሰት ግን እስከዓለም ፍጻሜ ስለምትኖር ወያኔ ካልጠፋ ከውሸታምነቱና ከሀገር አጥፊነቱ ተፈጥሯዊ ባሕርይው ሊፋታ አይቻለውም፡፡ ታሪክ ግን ሥራውን የማይረሣ ቆፍጣና ገበሬ በመሆኑ ጊዜውን ጠብቆ እነዚህን ጉግማንጉጎች ወደማይቀረው መቃብራቸው እንደሚሰዳቸው የታመነ ነውና መፍረስ የጀመረው የበሰበሰ ሥርዓታቸው ከነሰንኮፉ ተገርስሶ ሀገራችን በቅርቡ ነጻ እንደምትወጣ በሙሉ ልብ አምናለሁ፡፡ በዚህች መንደርደሪያ ወደሰሞነኛው የበረከት ስምዖን ውሽከታ እንለፍ፡፡
“የኢትዮጵያ አርሶ አደር እስካሁን በተደረገለት ሥራ በሚገባ የረካ ስለሆነ ‹መንግሥት ሰልፍ ውጣ ቢለው ይወጣል፤ መንግሥት ተኛ ቢለው ይተኛል፤ ግፍ ብንፈጽም እንኳን አርሶ አደሩ ይህንን መንግሥት ይሸከመዋል እንጂ ምንም አይለውም፡፡”
ይህን የብፃይ በረከት ንግግር በዓይነቱ ልዩ የሚያደርገው የተባበሩት መንግሥታት ሰሞኑን ባወጣው አንድ ጥናታዊ ዘገባ ላይ በአፍሪካ ፈጣን ዕድገት ከሚያሳዩ አሥር ሀገሮች ውስጥ ኢትዮጵያ አለመካተቷና በተጓዳኝም ይህቺው ኢትዮጵያ – ይህቺው ወያኔን በጫንቃዋ እንደምትሸከም በረከት አፉን ሞልቶ የመሰከረላት ጉደኛዋ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ጠኔ ጓዙን ጠቅልሎ ከመሸገባቸው አምስት የመጨረሻ ድሃ ሀገራት ውስጥ መመደቧ ነው – (በረከት ይህን ሪፖርት ሳያነብ መሆን አለበት ያን በህልሙ የደረሰውን ጅሎችን የማሞኛ ተምኔታዊ(utopian) ቧልታይና ድንቃይ ድርሰቱን የደሰኮረው!)፡፡ በነገራችን ላይ በአምባገነንነትና በድህነት በወያኔ መንግሥት ሳይቀር የምትታማዋ ኤርትራ በነዚህ ዘገባዎች አልተካተተችም(እንዲያውም ዘገባው ኢትዮጵያን ይግረማት ብሎ ከአሥሩ በፍጥነት እያደጉ ካሉ የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ አንዷ ኤርትራ እንደሆነች የገለጠ መሰለኝ)፡፡ ኢትዮጵያ ቻድን ብቻ በልጣ በአፍሪካ በርሀብተኝነት ሁለተኛ ስትወጣ ኤርትራ ከአምስቱ የባሰባቸው ሀገራት ውስጥ አልገባችም፡፡ የርሷ መግባት አለመግባት የኔ ራስ ምታት አይደለም፡፡ ነገር ግን ይህች በማዕቀብና በልዩ ልዩ የማሰቃያ መንገዶች የተወጠረች የቀድሞ የኢትዮጵያ ግዛት ከኢትዮጵያ የተሻለች መሆንዋን በመረጃ በተደገፈ ዘገባ የሚረዳ ጤናማ ሰው የወያኔን ሚዲያ አስችሎት እንዴት ሊከታተል እንደሚችል ይታያችሁ፡፡ ክርስቶስ ‹አፌን በምሳሌ እከፍታለሁ› አለ፡፡ ወያኔም ይህችን የክርስቶስ አባባል ቀምቶ በማንሻፈፍ ‹አፌን በሀሰትና ዕብለት እከፍታለሁ› አለና ነጋ ጠባ የማያቅመን የሀሰት ወሬ የማይነጥፍበት አስገራሚ ፍጡር ሆነ፡፡
መዋሸት የማይሰለቸው ‹ልማታዊው መንግሥታችን› በሚዲያው የሚያሳየን ኢትዮጵያና እኛ በግልጥ የምናያት ኢትዮጵያ ተለያይተውብን ተቸግረናል፡፡ እነሱ ‹ኢትዮጵያ በልማት ጎዳና እየተመመች ናት፤ የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ራዕይ ለማሳካት በየፈርጁ የምናካሂደው የልማት ግስጋሴ ግቡን እየመታ ነው፤ የኢትዮጵያ ልማት ማንም በማይወዳደረው ሁኔታ ወደፊት እየተምዘገዘገ ነው፡፡ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓታችንን በማይነቃነቅ ዓለት ላይ ገምብተናል፤ የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መብት ሳይሸራረፍ የተከበረባትና በሕዝቦች መፈቃቀድ ላይ የተመሠረተ አንድነት እውን የሆነባት አዲሲቷ ኢትዮጵያ ተፈጥራለች፡፡ አሁን ዋናው ጠላታችን ድህነት ነው፡፡ እሱንም እየተዋጋነው ነው…›እያሉ በቲቪያቸው እያላገጡብን ነው – ድህነትን ለመዋጋትና ለማሸነፍ ደግሞ ስንት አሥር ዓመቶች እንደሚያስፈልጉን እነሱው ናቸው የሚያውቁት፤ ለመልካም አስተዳደር እኮ አንድ የመኸር ወቅትም ትልቅ ጊዜ ነው – እንኳንስ 23 ዓመታት፡፡ ወያኔዎች ግን በድህነት ላይ እንደዛቱና ወደታሪክነት እንለውጠዋለን እንዳሉ ሦስት ዐሠርት ዓመታትን ሊደፍኑ ነው፤ አያፍሩም፡፡ በማከያው ግን ዕድሜ ለወያኔው ጉጅሌ በምግብ “ሞልቶ መትረፍረፍ” ከአፍሪካ አንዲት ሀገር ብቻ በልጠን በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎቻችን የተንጣለሉ የአስፋልት መንገዶችንና በአብዛኛው የትግራይ ተወላጆች የሆኑ ኢንቬስተሮች የገነቧቸውን ሕንፃዎች “እየተመገቡና እየጠገቡ” መሆናቸው እየተነገረን ነው፤ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ያጡ የነጡ ዜጎቻችንም ከዬቆሻሻ ገንዳዎች የሀብታም ፍርፋሪና የሙዝ ልጣጭ ለመሻማት ቀን ከሌሊት ሲራኮቱ ይታያሉ፡፡ የወያኔ ዕድገት ይህ ነው፡፡ የወያኔ ‹ልማታዊ ጋዜጠኞች›ም በበኩላቸው የሕዝቡን ሰቆቃ እንዳይመለከቱና እንዳይዘግቡ እንደአቃቂ ፈረስ ዐይኖቻቸውን በወያኔ ተከልለው በብድርና በዕርዳታ በተገነቡ መንገዶችና ድልድዮች ላይ ካሜራዎቻቸውን በመደቀን ሌት ከቀን በተመሳሳይ ዜናዎችና ሀተታዎች ማደንቆራቸውን ተያይዘውታል፡፡ እኛን እሚያሳክከን ሆዳችን ላይ እነሱ እሚያኩልን እግራችንን፡፡ የሚገርሙ ጋዜጠኞችና የሚገርም የማፊያዎች መንግሥት፡፡
ወደበረከት ንግግር እንመለስ፡፡ እንደእውነቱ በረከት ከፍ ሲል የተናገረውን ነገር ለምን እንደተናገረው አልገባኝም፡፡ ምን ማለት እንደፈለገ ለመረዳት አስተርጓሚ ሳያስፈልግ አይቀርም፡፡  አማርኛ ቋንቋን አውቃለሁ ብዬ ደረቴን ነፍቼ እናገራለሁ፡፡ ነገር ግን ይህንን የበረከትን ንግግር እንደመሰለኝ ተርጉሜ እንዲገባኝ ጥረት አደረግሁ እንጂ በቅጡ ልረዳው አልተቻለኝም፤ እርሱም ቢሆን ጎንደር ውስጥ ብዙ ዓመታትን ስለኖረ አማርኛን ከአፍ መፍቻው ባልተናነሰ ያውቃል ብዬ እገምታለሁና ‹ምን ማለት እንደፈለገ ሳይገባው እንዲህ ያለ የተወነዣበረ ንግግር በአደባባይ ተናግሮ የሰው መሣቂያ ለመሆን አይደፍርም› ብዬ ለማመንም በጣም ተቸገርኩ፡፡
ይህን ንግግር በብዙ መልኩ መገንዘብ እንደሚቻል አምናለሁ፤ በአማርኛው “የጊዮርጊስን ግብር የበላ ሳይነኩት ይለፈልፋል” ወይም በሌላ ፈሊጣዊ አገላለጽ “የምላስ ወለምታ” የምንላቸው ምሥል ከሳች አባባሎች አሉ፡፡ በፈረንጅኛው “Fruedian slip” የሚባል በሥነ ልቦና የትምህርት ዘርፍ የሚጠቀስ ሐረግ አለ፡፡ ይህ ሰው የተናገረውን ከነዚህ ጽንሰ ሃሳባዊ ዕይታዎች አንጻር ብንመለከተው ወያኔ ከመጃጀቱና በወንጀል ድርጊቶች ከመጨመላለቁ የተነሣ ነፍሱ እየቃዠች መሆኗን መረዳት አያዳግተንም፡፡ አለበለዚያ ግፍ በመሥራት ላይ የቆመ የወሮበሎች መንግሥት  “ገበሬው ግፍ ብንፈጽምበትም ይሸከመናል” ብሎ መናገሩ ምን ትርጉም ይኖረዋል? አንድ ጤነኛ ሰው ከመሬት ተነስቶ “በጥፊ ባጮልህና ዐይንህን በጉጠት ባወጣውም እንደማትቀየመኝ አውቃለሁ! ከኔ በበለጠ ሊያሰቃይህ የሚችል ወገን እንደሌለ ስለማውቅ ለስቃይ ለስቃይ እኔው እሻልሃለሁና ምርጫህ እኔው ብቻ ልሆን ይገባኛል” ብሎ እንዴት ሊናገር ይችላል? እንዲህ ብሎ የሚናገር ሰው ካለ ደግሞ እንደበረከት የለዬለት በሽተኛ እንጂ ጤናማ ሰው ሊሆን አይችልም፡፡ ከወፈፌና በሽተኞች ንግግር ይሠውረን፡፡ “ዱባ ካላበደ ቅል አይጥልም” አሉ? የሚገርም በረከት ነው የሆነብኝ እባካችሁን፡፡
ይህን ንግግር በቁሙ መረዳት እንደሚቻለው በረከት ማለት ቅል ራስና እሚናገረውን እንኳን የማያውቅ ገልቱ ሰው ነው፡፡ ለመደዴ የቃላት አጠቃቀሜ ይቅርታ ይደረግልኝና እንደዚህ ያለ ድፍን ቅልና ባልጩት ራስ የኢትዮጵያ አንዱ ባለሥልጣን እንደነበረ በነገው የታሪክ መዝገባችን ሠፍሮ ሲታይ በቀጣይ ትውልዶቻችን ዘንድ በእጅጉ ከምናፍርባቸው የታሪክ ስብራቶቻችን መካከል አንዱና ትልቁ ነው፡፡ ሰው ምን ቢጃጃል እንደዚህ አይናገርም ወይም አይጽፍም፤ አለበለዚያም አብዷል ማለት ነው፡፡ “አፍ ሲከፈት ጭንቅላት ይታያል” የሚባለው እኮ እንደዚህ ያለ በደናቁርት አስተሳሰብ የተለወሰ የአነጋገር ጭቅቅት ሲያጋጥም ነው፡፡ ተመልከቱልኝ፡-
“መንግሥት ሠልፍ ውጣ ቢለው ይወጣል፤ ተኛ ቢለው ይተኛል፡፡”
ምን ማለት ነው? ገበሬውን በማስገደድም ይሁን በማታለል ሠልፍ ማስወጣት ይቻል ይሆናል፡፡ ነገር ግን እንዴት ነው እንደሕጻን ልጅ ገበሬውን በትዕዛዝ አባብሎ ማስተኛት የሚቻለው? ምን ዓይነት ዕብሪትና ትምክህት ነው? ምን ዓይነት የድንቁርና አነጋገር ነው? ለነገሩ ወያኔዎች ከአለቃቸው ከመለስ ጀምሮ ለአነጋገራቸው ደንታ የላቸውም፤ የሚያስቡት እንደጤናማ ሰው በጭንቅላት ሣይሆን እንደ አውሬ በጡንቻ ሣይሆን አይቀርም – አውሬ በጡንቻው ካሰበ፡፡ ሀገር፣ ታሪክና ወገን አለን ብለው ራሳቸው ስለራሳቸው የሚያምኑ አይደሉም፤ ባህል የላቸውም፤ ሞራል ወይም ‘ethical values’  ብሎ ነገር አያውቁም፤ ምናልባት ከሴቴኒዝም በስተቀር ሁነኛ ሃይማኖትም ያላቸው አይመስሉም (ለዚህም ይመስላል ወንጀለኝነት የሚያዝናናቸውና በሰዎች ስቃይ የሚደሰቱት)፤ በትውፊትና በወግ ልማድ አያምኑም፤ ባጭሩ ወፍዘራሽ የመርገምት ውጤቶች ናቸው፡፡ ከሁሉም ነገር የወጡና ከዜሮ መጀመር የሚወዱ በፈረንጅኛው አገላለጽ nihilists ናቸው – hedonist የሚል ምርቃትም ማከል ይቻላል፡፡ ታሪክን ማጥፋትና ነባር ባህልን ማውደም ያረካቸዋልና፡፡
ወያኔዎች ማለት ባጭሩ ማሊ በምትባለዋ አፍሪካዊት ሀገር ‹አዛዋድ› በሚል ራሳቸው በፈጠሩት አዲስ ግዛት ውስጥ ፈረንሣይ ድምጥማጣቸውን እስክታጠፋቸው ድረስ ለተወሰነ ጊዜ በሼሪዓ ህግ የሚተዳደር እስላማዊ መንግሥት መሥርተው እንደነበሩት የቱዋሬግ አማፅያን  የሚመሰሉ ናቸው – ወያኔዎች እንደሶማሊያው አልሻባብ ዓይነትም ናቸው – ነገር ግን መንግሥት ስለያዙ ደፍሮ በአሸባሪነት የፈረጃቸው ዓለም አቀፍ ኃይል ሊገኝ አልቻለም፡፡ ለነገሩ ወያኔዎች ሀገራዊ አጀንዳ ስለሌላቸውና የማንንም ፀረ-ኢትዮጵያ የሆነ አጀንዳ አንከርፍፈው በተባባሪነት ስለሚጓዙ ለዓለም አቀፍ ታዋቂ ኃይሎች እስትራቴጃዊ ጠቀሜታ እስከሰጡ ድረስ በአጋርነት የሚያስጠጋቸውና ሙሉ ድጋፍ የሚሰጣቸው አያጡም(ኢትዮጵያውያንን ለጊዜውም ቢሆን እያስቸገረን ያለው ይህን መሰሉ የወያኔ እስስታዊ ተፈጥሮ ነው)፡፡ እነዚያ የአልቃኢዳ የአፍሪካ ክንፍ የሆኑ አማጽያን በቲምቡክቱ ውስጥ የነበሩ ዕድሜያቸው በሺዎች ዓመታት የሚገመት የታሪክ ቅርሶችን በዶማና አካፋ እንዲሁም በግሬደር በአጭር ጊዜ የሥልጣን ቆይታቸው ውስጥ ድራሻቸውን ማጥፋታቸውን የቅርብ ጊዜ ትዝታ በመሆኑ ከዐይነ ልቦናችን ገና አልተሰወረም፡፡ ወያኔዎችም እያዋዙ በእስከዛሬው የኃይል አገዛዛቸው እጅግ በርካታ የኢትዮጵያ ቅርሶችንና ታሪኮችን አጥፍተዋል – ከሁሉም የሚብስ ጥፋታቸው ግን ከቁሣዊው ይልቅ ሥነ ልቦናዊውና  ኅሊናዊ ወመንፈሣዊው አጠቃላይ ውድመት የበለጠ ኪሣራ ያደረሰብንና ለማገገምም ብዙ ጊዜ የሚወስድብን ከባዱ ጥፋት ይመስለኛል፡፡ እነዚህ ናቸው እንግዲህ ጅብ እማያውቁት ሀገር ሄዶ ቁርበት አንጥፉልኝ እንደሚል በምናውቃቸው ምሥኪን ዜጎች መሀል ሆነው ገበሬው የነሱ እንደሆነ የሚሰብኩን፡፡ ለነገሩ ጅብ እንኳን በማያውቁት ሀገር ነበር ተናገረው የተባለውን የተናገረው፡፡ ወያኔዎች ግን ዐይናቸውን በጨው አጥበው እኛው ፊት ሸፍጣቸውንና የሀሰት ቱሪናፋቸውን ካለተቀናቃኝ ለብቻቸው በተቆጣጠሩት ሚዲያቸው ያናፉብናል፡፡
የኢትዮጵያ ገበሬ ኑሮው ምን ይመስላል?
በአሁኑ ወቅት በወያኔ ሥርዓት እንደገበሬው የሚማረር የለም፡፡ የወያኔን የውሸት ፕሮፓጋንዳ ለወያኔና ወያኔያውያን ትተን እውነቱን ብቻ እናውራ ካልን የገበሬው ኑሮም ሆነ የአጠቃላዩ የሀገሪቱ ሕዝብ ሕይወት ያሳዝናል ብቻ ሳይሆን ያስለቅሳል፡፡ እኔ ይህን መልእክት የምጽፍላችሁ ዜጋ በሀገር ቤት የምኖርና አልፎ አልፎ ወደገጠር ለሥራ ጉዳይ ወጣ የምል በዚያም ምክንያት የብዙ አካባቢዎችን ነዋሪዎች ሰቆቃና የዕለት ከለት ውጣ ውረድ የምታዘብ ሰው ነኝ፡፡ ስለዚህም የምለው ነገር በስማ በለው የተገኘ ሳይሆን በራሴም ሕይወት እየደረሰ ያለ እውነተኛ ሰቆቃ መሆኑን ላስታውስ እፈልጋለሁ፡፡ የገበሬው ኑሮ ከእኛ ከከተሜዎቹ የባሰ እንጂ የተሻለ እንዳልሆነ በውነት እመሰክራለሁ፡፡
የአንድ አምባገነን መንግሥት ትልቁ ሕዝብን የመግዣ መሣሪያ ሌላ ሳይሆን በማይምነትና በድንቁርና ሸብቦ በማስፈራራትና በማስራብ አንቀጥቅጦ ወደተናጋሪ እንስሳነት መለወጥ ነው፡፡ ወያኔም እያደረገ ያለው ይህንኑ ነው፡፡ በየትኛውም የኢትዮጵያ አካባቢ ብትሄዱ ለይስሙላ ትምህርት ቤቶች ይሠሩ እንጂ ጥራቱን የጠበቀ ትምህርት ባለመኖሩ መማር ካለመማር የሚለይበትን መሠረታዊ ነጥብ ፈልጋችሁ ልታገኙ አትችሉም፡፡ በመሆኑም ገበሬው ከትምህርት ርቋል፤ የጨለማ አዘቅት ውስጥም ከገባ ቆይቷል፡፡ በማይምነት አለንጋ እየተገረፈ፣ በብጥቅጣቂ እርሻ ላይ በሚዘራት አነስተኛ ሰብል እየተሰቃዬ፣ ከዚያችም ሰብል ላይ ከፍተኛ ግብር እንዲከፍል እየተገደደና ከብቱንና ንብረቱን ሸጦ ግብር እንዲያስገባ እየተጠየቀ የሚገኝ ገበሬ ወያኔን ጣዕረሞት ሲይዘው “በፍቅርና በትግስት ይሸከመዋል” ሳይሆን “የወያኔን ሬሣ ተሸክሞ ወደመቃብሩ ይሸኘዋል” ቢባል ነው ትክክለኛው፡፡  ገበሬው በቀን አንድ ጊዜም የሚቀምሰው በሌለበት ሁኔታ፣ ገበሬው የልጁን ወስፋት የሚሸነግልበት አንዳችም እህልና ጥሪት አልባ በሆነበት ሁኔታ፣ ገበሬው ከገጠር እየፈለሰ ወደከተሞች በመግባት ለወያኔ ሕንጻና ፋብሪካ ግንባታዎች የቀን ሠራተኛ እየሆነ ባለበት ሁኔታ፣ ገበሬው ልጆቹ ወደዐረብ ሀገር እየተሰደዱ ለዐረብ ጀማላ የሠይፍ እራትና የአስገድዶ መድፈር ሲሳይ እየሆኑ ባሉበት ሁኔታ፣ ገበሬው በማዳበሪያ ዕዳ የስንግ ተይዞ ኤሎሄ እያለ በሚገኝበት ሁኔታ፣ ገበሬው በአድሎኣዊ የመሬት ሥሪት ምክንያት መድሎ እየተሠራበት ማለፊያው የውሃ መሬት ለካድሬዎችና ለወያኔዎች እየተሰጠ ጭንጫውና መናኛው መሬት ግን ለድሃ ገበሬ እየተሸነሸነ ባለበት ሁኔታ፣ገበሬው ከማሳውና ከመኖሪያው እየተፈናቀለ መሬቱ በልማት ስም ለወያኔ ከበርቴዎች እየተቃረጠ ባለበት ሁኔታ፣ አህያ የተጫነችውን እንደማትበላ ሁሉ ገበሬውም ያመረተውን ምርት ለዕዳ ክፍያ ሲል ለጠገቡ የወያኔ ‹ልማታዊ ባለሀብቶች› በርካሽ እንዲሸጥና ጨርቁ በላዩ ላይ አልቆ በባዶ እግሩ እየሄደ በእሾህና በእንቅፋት አሣሩን እንዲበላ ተፈርዶበት ባለበት ሁኔታ፣ … በረከት የተናገረውን መስማት በርግጥም ተዓምር እንጂ ሌላ ምን ሊሆን ይችላል? በቀደመው ዘመን “እስመ አልቦ ነገር ዘይሰአኖ ለእግዚአብሔር” ነበር ሲባል እምንሰማ፡፡ አሁን ደግሞ “እስመአልቦ ነገር ዘይሰኣኖ ለወያኔ”ብንል እንሳሳት ይሆን? ወያኔ ጥቁሩን ነጭ፣ ነጩን ጥቁር፤ ልቅሶን ሠርግ፣ መርዶን ብሥራት ማድረግ የሚችል ልዩ ምትሃት ያለውና በአፍ ጤፍ የሚቆላ ፍጡር ነው፡፡ ወያኔን ለሚያውቅ የወያኔ ዲስኩርና ፕሮፓጋንዳ  ችግር የለውም – በወያኔ ፕሮፓጋንዳ የሚጃጃል ወያኔን የማያውቅ ወይም ማወቅ የማይፈልግ ብቻ ነው፡፡ ‹ብታምኑም ባታምኑም የኢትዮጵያ ሕዝብ ወያኔን ከእግር እስከራሱ ጠንቅቆ ያውቀዋል!›፡፡ እናም በተለይ በአሁኑ ወቅት ወያኔ ማንንም ሊያታልል በማይችልበት ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ሞቶ በሞቶ እርግጠኛ ሆኜ እናገራችኋለሁኝ፡፡
እናም ወያኔ ስለገበሬው የሚያወራውና እኛ ስለገበሬው የምናውኧው፣ ገበሬውም ስለወያኔ የሚለውና ስለራሱም ከራሱ ኑሮ የሚስተዋለው ለዬቅል መሆናቸውን ልብ ማለት ይገባል፡፡ ‹ይሉሽን በሰማሽ ገበያ ባልወጣሽ› ይባላል፡፡ በረከት የሚናገረው ለሌሎች ብቻም ሳይሆን ለራሱም ሀሰት መሆኑን ማንም አያጣውም፡፡ በረከትን በማታው ‹ክብ ጠረጴዛ› አግኝተን “ምነው ወዲ ስምዖን፣ እንደዚያ ያለ ነጭ ውሸት ማናፈስ ደግ ነው እንዴ ? ለመሆኑ አንተስ ታምንበታለህ? ኅሊናስ የሚባል ነገር የለ(ህ)ም እንዴ?” ብንለው መልሱ ቀላል ነው፡፡ “ወንድሜ፣ በፖለቲካ ኅሊና ብሎ ነገር የለም፡፡ ዋናው ማምለጥ ነው፡፡ የምታደርገውን አድርገህ፣ የምትናገረውን ተናግረህ በፊትህ ከተደቀነብህ ችግር ማፈትለክ እንጂ ስለምትናገረው ነገር እውነትነት ከተጨነቅህ ፖለቲካ ውስጥ ቀድሞውን መግባት የለብህም፡፡ በተለይ እንደኛ ዓይነቱን ችግር ለጠላትም አይስጥ ወንድሜ፡፡ የገባንበት አጣብቂኝ በቀላሉ የሚወጡት አይደለም፡፡ መጥኖ መደቆስ አስቀድሞ ነበር ወዳጄ፡፡ በደም ጨቅይተናል፤ በሙስና በክተናል፤ በዘረኝነቱም ረገድ ያጠፋነውን ጥፋትም ቆም ብለው ሲያስተነትኑት የአንጎልን ሚዛን የሚያዛባና የሚያሳብድ ነው፤ ወደትግል ከገባንበት ጊዜ ጀምሮ የገደልነውና ለስደትና ለእሥራት የዳረግነው ዜጋ የኅሊና ዕረፍት እያሳጣ መቆሚያ መቀመጫ ያሳጣናል፤ ለዚህም ነው ብዙዎቻችን ቢሯችን ውስጥ ሣይቀር በብርጭቆ ውስጥ መደበቅን የምንመርጠው፡፡ ሰው ወዶና ፈቅዶ ጉበቱን በመጠጥ ቦጫጭቆ ሞትን በራሱ አይጋብዝም፡፡ ታዲያ አሁን ምን እናድርግ? ነገር የተበላሸው ዱሮ ነው፤ አሁን ሁሉም ነገር ጠርዝ ከለቀቀ በኋላ ከመዋሸትና ከማምታታት ውጪ ምን አማራጭ አለን? አንድ ነገር ሲገቡበት ቀላል ነው፤ ለመውጣት ግን ከባድ ነው፡፡ የኛ ወደዚህ ሥፍራ መምጣትና አንድ ሰው ወደአደንዛዥ ዕፅ ሱስ መግባት ሂደቱ ተመሳሳይ ነው፤ ሁለታችንም እንደዋዛ እንገባለን – እንደዋዛ መውጣት ግን ለሁለታችንም ከባድ ነው፡፡…” አዎ፣ በረከት በዊስኪ ጨዋታው ለሁነኛው ልክ እንደዚህ እንደሚያጫውተው ‘subconscious’-ኡን በርቀት በማንበብ መረዳት ይቻላል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ለወደቀም ማዘን ተገቢ ነው፤ ‹ለሚወድቅ› ብላችሁ ልታሻሽሉትም ትችላላችሁ፡፡ እንደኔ ግን ወያኔዎች ሲነሱ ነው የወደቁት፡፡ ሰው ሲወለድ ነው የሞተው እንደምንል መሆኑ ነው፡፡ ወያኔዎችም ክፋትን መሥራት ሲጀምሩ፣ በቂም በቀል የተቃኘ የጥላቻ አገዛዛቸውን በስፋት ሲያጧጡፉ፣ ሀገርን ሲሸጡና ሲለውጡ፣ ምድርን በደም ረግረግ ሲሞሉ፣ አማራን ከትግሬ፣ ትግሬን ከኦሮሞ እዬለዩ አንዱን መጥቀምን ሌላውን መጉዳትን ባህላቸው ሲያደርጉ፣ ዳር ድንበርን እንዳወጣ ለባዕድ ሀገራት ሲቸበችቡ፣ ሀገርን ካለመውጫ በር ዘግተው የሚሊዮኖችን እስትንፋስ ሲዘጉ፣ … ያኔ ነው ወያኔዎች ገና በጧት ሳይወለዱ የሞቱት፡፡ እዚህ ላይ የሞት ዓይነት ብዙ መሆኑን ልብ ይሏል፡፡ እንጂ የአሁኑ እስትንፋሳቸውማ በ“ሥልጣን” ካሳለፉት ጊዜ አንጻር ሲታይ የደቂቃዎች ያህል ጊዜ ብቻ የቀራቸው ጉድጓዳቸው የተማሰ ልጣቸውም የተራሰ ስለመሆኑ ጨረቃና ፀሐያቸውን በማየት ብቻ የምንረዳው ነው – ዘመናቸው አልቋል፡፡ … የኔ አይደለም …የርሱ እንጂ፡፡ የፍርድ ሂደቱና ብያኔው ከታች አይደለም – ከላይ እንጂ፡፡
የኢትዮጵያን ገበሬ ኑሮ በረከት አያውቀውም ማለት ዘበት ነው፡፡ የኢትዮጵያን ገበሬ ወያኔ አያውቀውም ብሎ በዚህ ሰውዬ ንግግር መደመምም ከንቱ ነው፡፡ በገበሬው መቀለድ አምሯቸው እንጂ የሚናገሩት ነገር እውነቱ የተገላቢጦሽ መሆኑን አጥተውት አይደለም፡፡
ስለሆነም በረከት የሚለው ነገር “አይሰማም!” እንላቸዋለን ፡፡ በረከት ልፋ ብሎት ተናገረ የተባለውን ይናገር እንጂ የራሱ ስብሰባ አባላት ሳይቀሩ ሲችሉ በግልጥ ሳይችሉ ደግሞ በውስጣቸው ይስቁበታል፡፡ ለዚያውም ከትከት ብለው ነው እሚስቁበት – እንደጅል በመቁጠር፡፡ እርግጥ ነው – በረከት ጅል አይደለም፡፡ ጅል ለመምሰል የቆረጠው ግን ምርጫ በማጣት ይመስለኛል፡፡ አንድ ሰው ፀሐይ የሞቀውን እውነት ለመሸፈን በመሞከር በግልባጩ ለማውራት ከተገደደ አንድም ያስጨነቀው ነገር አለ ማለት ነው፤ አለበለዚያም የመዋሸት ተፈጥሯዊ ጠባይ  አለበት ማለት ነው – ልክ እንደመለስ ዜናዊ፡፡ መለስ ዜናዊ በሣይንስ የተረጋገጠ ላይሆን ይችላል እንጂ በእንግሊዝኛው ‘pathological liar’  የሚባል ዓይነት ግለሰብ እንደነበር መረዳት አይቸግርም፡፡ እርሱ በቲቪ ቀርቦ የሚናገራቸውን ንግግሮችና መሬት ላይ ይታይ የነበረውን እውነት በማስተያየት የዚህን ሰው ውሸት በመናገር የመርካት ጠባይ ወይም የተዛባ ተፈጥሯዊ ባሕርይ በቀላሉ መገንዘብ ይቻል ነበር፡፡ በዚህ መልክ ይህ ተጋቦታዊ ደዌ በትግል አጋርነትና በጥቅም ተጋሪነት ምክንያት ለበረከትም ተርፎ ይሄውና በረከትም አንድም ሰው ላያምነው – አንድም የራሱ ሰው ሳይቀር አምኖ ላይቀበለው – እንዲሁ ድከም ብሎት ሲወሻክት እናደምጠዋለን፡፡ እስከመቼ እየወሻከተ በሰው ስቃይ ሲደሰትና የሰውን ስቃይ ለሚዲያ ፍጆታ ያህል ለከንቱዎች በመሸጥ እንደሚኖር ገና የምናየው ይሆናል፡፡ ወደኅሊናው የሚመለስ አይመስለኝም እንጂ ከተመለሰ ግን የገበሬውም ሆነ የአጠቃላዩ የኢትዮጵያ ሕዝብ ካሉት በታች ከሞቱት በላይ የሆነ የሰቆቃ ሕይወት በሚያሳድርበት የእርግማን መዘዝ እንደይሁዳ ራሱን ሰቅሎ እንደሚገድል አምናለሁ፡፡ ያ ቀን ደግሞ በጣም ቀርቧል፤ ምን አለ በሉኝ እነዚህ ጉዶች የሥራቸውን የሚከፈሉበት ጊዜ በብርሃን ፍጥነት እየገሰገሰ በመምጣት ላይ መሆኑ ይሰማኛል፡፡ ቋቱ ሞልቷል፤ የሚቀረው የሚጠራርጋቸውን ማዕበል የሚያስነሣው የፈጣሪ ፊሽካ ብቻ ነው፡፡
የኃጢኣት ትንሽና ትልቅ ባይኖረውም አንድ ሰው ሰርቆ ቢበላ እርቦት ሊሆን ይችላልና ምንም አይደለም ሊባል ይችላል፤ ቢሳደብ ተናድዶ ሊሆን ይችላል በሚል ይቅርታ ሊደረግለት ቢችል ምንም አይደለም፡፡ ነገር ግን በመንግሥት ሠራሽ ርሀብና በግፈኛ አገዛዝ እያለቀሰ የሚኖርን ገበሬ በሚያስለቅሰው ዘረኛ ሥርዓት ተደስቶና ደልቶት እንደሚኖር በሚያስገርም አነጋገር ሰይጣናዊ ስብከትን በመገናኛ ብዙኃን መልቀቅ ከይቅርታ በላይ ነው፡፡ ብሶቱን ችሎ፣ የሚደርስበትን ግፍና መከራ ተቋቁሞ በሞትና በሕይወት እየተንጠራወዘ በሚኖር ሕዝብ ላይ ይህን የመሰለ ቀልድና ድራማ እየሠሩ መሣለቅ ለዘር የሚተርፍ መራራ ቅጣት ሊያስከትል እንደሚችል በረከትም ሆነ ግብረ አበሮቹ መረዳት አለባቸው፡፡ ይህ መሪር ቀልዳቸው ዛሬና ለነሱ ምንም ላይመስል ይችላል፡፡ ይሁንና እያንዳንዷ የምናደርጋት መጥፎ ነገር ሁሉ ትልቅ ዋጋ ሳታስከፍል እንዲሁ የምትቀር እንዳልሆነች ቀልደኞቹና በኢቲቪ የሚገኙ ሆዳም ወናፎች ሁሉ ሊገነዘቡት ይገባል፡፡ ዛሬ ገበሬውም ሆነ ከተሜው አንደበቱ ተለጉሟል፤ አይናገርም፤ ሊናገርም አይፈልግም፡፡ ሰሚ ስለሌለውና ፈጣሪው ፊቱን እንዳዞረበት ስለተረዳ ሁሉም በዝምታ  ተቀምጧል፡፡ ይህ ማለት ግን ዘመን አይለወጥም፣ ዝም ያለም ሁሉ ደንቆሮና አላዋቂ ነው  ማለት አይደለም፡፡ ወያኔ እንዳልነበር ሁሉ የማይኖርበት ጊዜ ሲመጣ ሊከሰት የሚችለውን ትዕይንት አለማየት ነው፡፡ ያኔ እንደዛሬው እዩኝ እዩኝ እንደተባለ ሁሉ ደብቁኝ ደብቁኝ የሚባልበት ጊዜ መድረኩን ይረከባል፡፡ ጥጋብ ደግሞ ወደራብ መንዳቱ ያለና የነበረ ነው፡፡ የጠገበ የሚራብ የማይመስለው የመሆኑ መጥፎ አጋጣሚ ግን አሳዛኝ የታሪክ ግጥምጥሞሽ እንደሆነ እስካሁን አለ – ሲገርም፡፡ አንዱ ከአንዱ ገመና ትምህርት ቢገበይ፣ የሚነሣው ከሚወድቀው ቢማር ግና የችግሮቻችን መንስኤዎች እንደጤዛ በረገፉ፣ እንደጉምም በበነኑ ነበር፡፡ ይህ አለመታደል እስከመቼ እንደሕግ ሆኖ እንደሚበጠብጠን አላውቅም፤ እስኪ የመጨረሻችን ያድርግልን፡፡
በማጠቃለያዬ ማሳሰብ የምፈልገው ነገር አለኝ፡፡ በረከትም ሆንክ ሌላ ጊዜ ሰጠኝ የምትል ባለሥልጣን ሁሉ ካለፈው ታሪክ ተማር፡፡ የሚያሳዝነኝ ነገር አፄዎቹ ከቀደሙት አፄዎች መማር ሳይፈልጉ ቀሩ፤ ቀሩናም ሕዝብን ሲንቁ ሲንቁ ቆይተው በናቁት ሕዝብ እርግማንና አመፅ ምክንያት እንዳልሆኑ ሆኑ – ዘር እንኳን አልወጣላቸውም፡፡ ደርግም ፈጣሪን ሣይቀር ከድቶና አስከድቶ ራሱን የፈጣሪን ያህል በመቁጠር ሕዝብን ሲንቅና ሲያዋርድ ቆይቶ በናቀውና ባዋረደው ሕዝብ እርግማንና ሁለንተናዊ የእምቢታ አመፅ ሰበብ እንደባቢሎን አይሆኑ ሆኖ ተንኮታኮተ – ስንትና ስንት ዘመናዊ ትጥቅ እያለው አንዱም አላዳነውም፤ ይንቃቸው በነበሩ መናኛ የጫካ ወሮበሎች በቀላሉ ተገፍትሮ ወደቀ፡- መጽሐፉ ‹ንጉሥ በሠራዊቱ ብዛት አይድንም› እንደሚል መዘንጋት አይገባም፡፡ እነዚህኞቹ ፀረ-ኢትዮጵያ ጉጂሌዎችም አይነጋ መስሏቸው የኢትዮጵያ ታሪክ መዝገብና ሕዝቡ ሊሸከሙት ያልተቻላቸው ግፍና በደል በሀገርና በሕዝብ ሠሩ፤ ዋናዎቹ የአገዛዙ ቁንጮዎች በሣምንታት ልዩነት ወደማይቀሩበት የሲዖል ሥፍራቸው ተጓዙ፤ ቀሪዎቹም በመኖርና ባለመኖር አጣብቂኝ ውስጥ ተሰንቅረው ያደርጉትን በማጣት ፈጣሪ ሩህያቸውን ጨርሶ እስኪወስዳት እየተንጠራወዙ ይገኛሉ – ይህን እውነት ማስተሃቀር ፈጽሞውን የሚቻል አይደለም፡፡ ለውስጥ አዋቂዎች ወያኔዎች በሕይወት እንደሌሉ ከገባን ቆይተናል፡፡ በሕይወት ያሉ እንዲመስሉ የሆነው ምናልባት ለበጎ ነው፡፡ እንጂ እንደእውነቱ ወያኔ አከርካሪው የተመታው ዋናውን የሥርዓቱን መሃንዲስ መለስ ዜናዊን ፈጣሪ ባልተጠበቀ ወቅት ገና በ‹ማለዳ ዕድሜ›ው ሲጠራው ነው፡፡ ልብ ከተገኘ “ሁሉም ከእያንዳንዱ፣ እያንዳንዱም ከሁሉም እንዲማር ጊዜ ለመስጠት ተብሎ ነው የወያኔ የማይቀር ኅልፈት አዝጋሚ እንዲሆን የተደረገው” ብሎ ማሰብም ይቻላል – ምንም ነገር ማሰብ በማንም አልተከለከለምና (ወያኔዎች ግን ይህንንም ተፈጥሯዊ መብት ሊነፍጉን ይቃጣቸዋል፤ ኢትዮጵያ ውስጥ እየኖርክ ወያኔን ስለመጣል ወይም በሀገሪቷና በሕዝቡ ላይ የጣሉትን ግፈኛ የአገዛዝ ቀምበር ስለመቃወም “ማሰብ”ም አትችልም – ማሰብህ በዐይነ ውኃህ የፊት-ንባብ ከተደረሰበት በአሸባሪነት ተጠርንፈህ ዘብጥያ ትወርዳለህ)፡፡ ማሰብ በቻልንበት ሃሳብ ውስጥ በጊዜ ሰጪነት የምንጠረጥረውን አካል ደግሞ ለሁላችንም እኩል በሚገባን ቋንቋ አቶ ታሪክ ልንለው እንችላለን፡፡ ታሪክ የሚያዳላ ይመስለናል እንጂ ለማንምና ለምንም በጭራሽ አያዳላም – የራሱ የጊዜ ቀመር እንዳለው ግን ማጤን ተገቢ ነው (እርግጥ ነው – ‹መብሰሉ ለማይቀረው ጭንቅላት እንጨት ይፈጃል› እንደሚባለው አንድ ታሪካዊ ኹነት ተከናውኖ ቀጣዩ ሌላ ኹነት እስኪከናወን የሚኖረው የጊዜ እርዝማኔ በትግስታችንና በሃይማኖታችን ጭምር አሉታዊ ጥላውን ማጥላቱ የማናልፈው የዘመን ቅጣት ይመስላል፤ ማን ነበረች – አዎ፣ ሜሪ አርምዴ – “ፍቅር ያዘኝ ብለሽ አትበይ ደንበር ገተር፤ እኛም አንድ ሰሞን እንደሱ አ’ርጎን ነበር፤› ያለችውን የዘፈን ግጥም አለመዘንጋት የአጽናኝነት ጠቀሜታ አለውና እናስታውሰው፡፡) ዕድሜ ይስጠን ሁሉን እናያለን፡፡ ሌላ ዘፋኝም “እናያለን ገና” ብሏል፡፡ ይህንኑ ዘፈን ልጋብዛችሁና እንለያይ፡፡ ጣሊያኖች ሲለያዩ “አሪቬዴርቺ” ይላሉ – በ“ሰላም ያገናኘን” ለማለት፡፡
ሰበር መርዶ!
ይህን ጦማር ጽፌ የጨረስኩት ሌሊት ነው፡፡ ጧት ወደሥራ ልሄድ ስነሳ እንደወትሮው ሁሉ ቤቴ አጠገብ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎቻቸውን ወደዬክፍላቸውን ከማስገባታቸው በፊት ሰንደቁ አጠገብ አሠልፈው ብሔራዊ መዝሙር በቴፕ ከፍተው ሲያጮኹ ሰማሁ፡፡ ይሄኔ ኮምፒውተሬን ከፍቼ ይህችን ሃሳብ በሰበር መርዶነት ለመሰንቀር ወደድኩ፡፡ የሀገር ሞት ከዚህ በላይ የለም፡፡ በጥንት ጊዜ ብሔራዊ መዝሙር ተማሪው ነበር በስሜት ተውጦ በመዘመር ወደክፍሉ የሚገባው፡፡ አሁን ዕድሜ ለወያኔ አዲሱ መዝሙር ሊያውም በመሣሪያ ብቻ የተቀነባበረው በቴፕ ይዘፈንና ወደክፍል ይገባል፡፡ ዛሬ ዛሬ የኢትዮጵያን ብሔራዊ መዝሙርና ባንዴራ የሚያውቅ ትውልድ እየጠፋ ነው፡፡ ራሱ መለስ ዜናዊ (በሕይወት ኖሮ) ይህን መዝሙር ውጣው ቢባል የሚችለው አይመስለኝም፡፡ ሌሎቹ የወያኔ ባለሥልጣናት ቢጠየቁም የሚያውቁት ስለመሆናቸው እርግጠኛ መሆን አይቻልም – ብቸኛ ዘመዳቸው ሆዳቸው በመሆኑ ስለሀገር ምንነት የሚያውቁት ነገር የለም ማለት ይቻላል፡፡ የሚሰቀለው ባንዴራ ደግሞ የተቀዳደደ፣ የነተበ፣ ቀለሙን የለወጠ፣ ከተሰቀለ የማይወርድና ተበጣጥሶ እስኪያልቅ 24 ሰዓት የሚውለበለብ የማን ሀገር ባንዴራ መሆኑም የማይታወቅ ነው፤ የጥንቱን የባንዴራ አሰቃቀልና አወራረድ ሥርዓት የሚያስታውስ ዜጋ የአሁኑን ሲያይ ያለቅሳል፡፡ ከአዲስ አበባ ወጣ በሚል ቦታ ደግሞ የኦሮሚያ ባንዴራና የኦሮሚያ ብሔራዊ መዝሙር በትምህርት ቤቶች እንደዚሁ በቴፕ ሲዘመር ወይም ልጆች በግዴታ አጥንተው እንዲዘምሩት ሲደረግ ታያላችሁ፡፡ ይህችን የነፃነት ምኩራብ የሆነች የታሪክ አምባ ሀገራችንን እንዲህ ባለቤት ያሳጧት የሰይጣን ልጆች ዋጋቸውን ሳያገኙ ከቀሩ በርግጥም ኢትዮጵያ ፈጣሪ የላትም፡፡ አላስችል ብሎኝ አሁን በእግረ መንገድ ትንሽ ለመናገር ፈለግሁ እንጂ ይህ ጉዳይ ብዙ የሚያናግር ነው – የጋራ የሚባለል አንዳችም ነገር እንዳይኖረን ከፍተኛ የጥፋት ሥራዎች በመሠራታቸው አሁንና ለጊዜው ጠፍተናል፤ አለን እንላለን እንጂ በርግጥም በወኔያዎች ደባና ሤራ የአብሮነት ኅልውናችን አደጋ ላይ ወድቋል – ብዙ የትስስር ገመዶች ተበጣጥሰዋል፡- የጋራ ቋንቋ፣ የጋራ መሪ(ዎች)፣ የጋራ የመከላከያ ጦር፣ የጋራ የፖሊስ ሠራዊት፣ የጋራ ድንበር፣ የጋራ ባህል፣ የጋራ ትውፊት፣ የጋራ ሥነቃልና ሥነ ጽሑፍ፣ የጋራ ቤተ መንግሥት፣ የጋራ መንግሥታዊ መዋቅር፣ የጋራ… የጋራ… የጋራ… የምንለው ነገር እንዳይኖረን ተደርገን አንዳችን አንዳችንን የጎሪጥ እንድናይና እንድንፈራራ ተደርገናል፡፡ ሌላው ሁሉ ቀርቶ የጋራ ስብዕና ወይም የሰውነት ደረጃ እንኳን የለንም፤ አንዱ ከሌላው የበለጠ ሰው ነው – ሌላውም ከአንዱ ያነሰ ሰው ነው፡፡ አንዱ የሰው ዘር ከሌላው በተለዬ ምርጥ ነው – ሌላው ደግሞ ውዳቂና ቢገድሉት የበቃ ነፍሱ ከእንስሳት ነፍስም ሳይቀር ያነሰ ዋጋ ያለው ነው – ሩቅ ተመልካቹ ጆርጅ ኦርዌል ጨርሶታል – “All animals are equal, but some are more equal than the others.”፡፡ በዚህ መልክ በፈረጁን ሰዎች ነው እንግዲህ አጥንታችን ድረስ ዘልቆ በሚጠዘጥዝ መሪር ፈረዖናዊ አገዛዝ እየተቀጠቀጥን የምንገኘው፡፡
ያን ደገኛ ኢትዮጵያዊ የአንድነት መንፈስ ለማምጣት እነቴዲ አፍሮን የመሰሉ የቁርጥ ቀን ልጆች ብቻ ሣይሆኑ ሁላችንም የየበኩላችንን ጥረት ማድረግ ይኖርብናል – ለራሳችንና ለልጆቻችን ስንል፡፡ ከራስ ወዳድነትና ከአህያይቷ የ‹እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል› ያረጀ ያፈጀ አስተሳሰብም ባፋጣኝ እንውጣ፡፡ አርቀን መመልከትን ባህላችን እናድርግ፡፡ ጎርፉ ሳይደርስብን ራሳችንን በኅሊና ጸጸት አጥበን ለመጪው መልካም ኢትዮጵያዊ ዘመን ዝግጁ ሆነን ለመጠበቅ እንሞክር፡፡ በየድረ ገጹ የሚታዬው ዘረኝነት ላይ የተመሠረተ ወያኔያዊ የዱባ ጥጋብ መሰል ቡራከረዩና ወንዝ የማያሻግር ከፋፋይ ፕሮፓጋንዳ ዘመኑን እያገባደደ በመሆኑ የአንዲት እናት ልጆች ነንና እንሶብር፡፡ ወያኔ የጋተንን ብርብራና መቅመቆ ማርከሻ እንፈልግለት፤ “ስሜት-ወለድ” ማስጠንቀቂያየን እዚህም ላይ ልድገመው – “እዩዩኝ ያለ ደብቁኝ ደብቁኝ ይላል”፡፡

ፍኖት – የአንድነት ፓርቲ አባል ከጠቅላላ ጉባኤ ምግስት ጀምሮ በእስር እየተንገላቱ ነዉ

አቶ አለማየሁ ለፌቦ የተባሉ በሲዳማ ጭሬ የአንድነት ፓርቲ አባል ከፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ማግስት ወደ ክልሉ ሲመለሱ አርሲ ሚጣ ነሴቦ ወረዳ ወርቃ ከተማ ታህሳስ 26 ቀን 2006 ዓ.ም እንደተያዙ መዘገባችን ይታወሳል፡፡ ከታሰሩበት ወረዳ ያንተ ጉዳይ የፖለቲካ ጉዳይ ስለሆነ እዚህ አይታይም በማለት ጥር 9 ቀን ወደ ሻሸመኔ ዞን ፖሊስ ተወስደው ታሰሩ፡፡
alemayehu_lessebo
ፖሊስ ጣቢያውም እንድትለቀቅ ከፈለግክ 1ኛ እስከዛሬ የታሰርኩበትን አልጠይቅም 2ኛ ከዚህ በኋላ ወደ ፖለቲካ አልገባም 3ኛ በተፈለኩኝ ሰዓት እቀርባለሁ ብለህ ፈርምና ውጣ የሚል ቅድመ ሁኔታ ቢያቀርብላቸውም አቶ አለማየሁ ግን በሰላማዊ መንገድ የሚታገልና በምርጫ ቦርድ ተመዝግቦ የሚንቀሳቀስ ፓርቲ አባል ነኝ ምንም ወንጀል አልፈጸምኩም፣ በፍጹም አልፈርምም ብለዋል፡፡
በ 5 ክስ ከሰንሃል 4ቱን ውድቅ አድርገናል በአንዱ ግን እንከስሃለን በሚል ለማስፈራራት ቢሞክሩም አቶ አለማየሁ በአቋማቸው ጸንተዋል፡፡ የሻሸመኔ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ተጫን ለምን እስካሁን ፍርድ ቤት እንዳልቀረቡ ለመጠየቅ በተደጋጋሚ ብንደውልም ልናገኛቸው አልቻልንም፡፡ አቶ አለማየሁ በአሁኑ ሰዓት ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ በሻሸመኔ ዞን ፖሊስ ጣቢያ በአደራ ታሰረው የሚገኙ እስረኛ ናቸው፡፡