Friday 3 January 2014

ያዋረደን ማነወ ? ? ?

ቅጥረኝነተ፤ የስልጣን ልክፍት፤ ዝቅተኝነትና እብደት፤ ቡድነኝነትና ጎጠኝነት፤ ዘራፊነት፤ ነፍሰገዳይና
ጨካኝነት አፋኝነትና አሸባሪነት፤ በታኝነትና ከፋፋይነት፤ ሗላቀርነትና ምቀኝነት፤ እምነት የለሺ
የታሪክና አገር ካሐዲነት ወዘተ ...የተሰኙት ቃላት ወያኔንና የሺፍታ ስርዓቱን በሚገባ ይገልፁታል። እኛ
ኢትዮጵያውያን ውርደታችን የሚጀምረው በዚህ ጨካኘና ካሐዲ ቡድን መዳፍ ስር ከወደቅንበት ጊዜ
ጀምሮ ነው። ወያኔና መሰሎቹ በኢትዮጵያና በሕዝባችን ላይ ባለፉት 22 አመታት የፈፀሙት ወንጀለኛ
ተግባሮቻቸው ዋንኛ መለኪያና ማረጋገጫችን ነው።
በየትኛውም የታሪክ አጋጣሚ እንደተመዘገበው መንግስትን ገልብጦ መንግሰት ማቋቋም ያለና የነበረ
አለማቀፋዊ ክስተት ነው። ነገርግን ወያኔንና የሺፍታ ስርዓቱን ከዓለማችን ታሪካዊ መዘውር ውስጥ
ልዩ የሚያደርገውውና በዛሬይቱ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚታየው ምስቅልቅል ስርዓቱም የሚጠቁመው
የገለበጠው አላፊውንና ጠፊወን ምድራዊ የኮሎኔል መንግስቱ ሐ /ማሪያምን መንግስት ሳይሆን ይልቁንም
የነበረውንና ወደፊትም የሚኖረውን የጋራ አገር፤ የጋራ ሕዝብ የጋራ ታሪካችንና ባሕልላችን ሆኖ
መገኘቱ ነው። ለዚሕም ነው ወያኔ ተፈጥሮዋዊ ውልደቱና እድገቱ መንግስት ተብሎ ለመጠራት
መመዘኛውን የማያሟላው። ይሕ ጎደሎው የመንግስትነት ስነምግባርና ሺፍታዊ መታወቂያው በመሆኑ
ብሔራዊ ሐላፊነት የማይሰማው ሐገርንና ሕዝብን ያዋረደ የጥቂት ሺፍቶች ማፍያ ቡድን ነው ብልን
አፋችን ሞልተን እንድንናገር የምንገደደው። የብሔራዊ ውርደታችን ምንጭም እራሱ ወያኔና አጋሮቹ
ለመሆናቸው ከተግባር የበለጠ ሌላ ገላጭ ቋንቋ ስለሌለ ማንንም የሚያጠራጥር ጉዳይ አይደለም
የወያኔውም አፈጣጠር ለዚሕ ጥፋት ታስቦና ተመቻችቶ ነው።
ቆምነገሩ ኢትዮጵያ ተብላ በምትታወቀው ምስራቅ አፍሪካዊት አገር ውስጥ ሐገሪቱን እንደሐገር
ሕዝቡን እንደህዝብ የሚያስከብር መንግሰት አለን ወይ ብሎ ለሚጠይቅ ዜጋ መልሱ የለንም ማለታችን
ብቻ ሳይሆን በዚሕ በኩል የነበረው እድል በ 4 ነጥብ መዘጋቱ ነው። ባንፃሩ ስናይ እኛን ኢትዮጵያንን
ያዋረደን ማነው የሚለውን ሰሞነኛ ጥያቄ ለመመለስ ወያኔ ነውና ደረታችን ነፍተን ከመናገር ውጭ
ከቶውንም ማነንም ቅን ዜጋ አያሳፍረውም። ሰሞኑን ደግሞ ያረጀ ጡርንባ እየተነፋ አየሩ ተበክሎል።
በውጭና በውስጥ ለምንገኝ ኢትዮጵያውያን ወገኖች ያረጀ ካርድ ተመዞ የተሰጠን አጀንዳ አለ። እሱም በዘመናዊ የባሪያ ፍንገላ ስልት በራሱ በወያኔው ተሺጠው በሳውዲ አረቢያ ውስጥ ስርተው በሚያድሩ
ወገኖቻችን ላይ የደረሰው አሰቃቂ እልቂትና ውርደት አንዱ ሲሆን ሁለተኛው የአማራውን ሕዝብ
ከኦረሞው ጋር የማጋጨቱ የቆየው የወያኔ አጀንዳ በቴዲ አፍሮ ዘፈን ምክንያት እንደገና በአዲስ መልክ
ተቀስቅሶ በውስጥም በውጭም በምንኖረው ኢትዮጵያዊያን ዘንድ አቧራው ጨሰ የተሰኘውን ወያኔዊ
የፕሮፓጋንዳ ሺብር አስከትሎ አጀንዳውን ጀባ ተብለናል።
ታዲያ የሰሞኑ አቧራው ጨሰ ወያኔዊ ሺብርተኛ ፕሮፖጋንዳ አጀንዳ ሚስጥሩ ምንድነው ብሎ መጠየቅ
ብልሕነት ነው። ሁላችንም እንደምናውቀው የኢትዮጵያ ህዝብ በወያኔው የጥፋት ውሳኔ መሰረት
ኢትዮጵያ የምትባል ሐገርና የዜግነት መብት የለህም ተብሎ በሕዋ ላይ መኖር ከጀመረ ይኸውና 22
ዓመታትን አስቆጥሮል።ኢትዮጵያዊነቱንና ሰው በመሆኑ ብቻ ነፃነቱን የጠየቀው ሕዝብ በወያኔና
መሰሎቹ በገዛ ሐገሩ ይገደላል፤የደበደባል፤ይታሰራል፤ ይሰደዳል፤ሐብትና ንብረቱን ይነጠቃል፤ትውልድ
ቦታውን በማስለቀቅ እንዲጋዝ ይፈረድበታል፤ በእምነቱ የማመን ነፃነቱ ይገፈፋል፤ ፍትህን ፍለጋ
ወደሰማይ እያነባ ያንጋጥጣል፤እራሐብና እርዛት ለሱ የተሰጠ ፀጋ ሆኖበታል፤ አኩሪ ባሕሉ ቆሺሾል፤
መጋባቱ መዋለዱ ተገድቦ ፈጣሪው የቸረውን ነፃነት ተነጥቆል፤ እርስበርሱ የመደጋገፍ ተስፋው
ተሟጧል፤ በየመንደሩ በተሰገሰጉ የወያኔ ጀሮ ጠቢውች እንዳይናገር ልሳኑ ተዘግቶል፤ የዘራፊወች የበይ
ተመልካች ሆኖ በራሐብ አለንጋ ይጠበሳል፤ ቤተሰቡን ማስተዳደር ተስኖታል፤ ባልተለመደ መልክ
ስብዕናን ለሚሸጡ የወያኔ ደላላወች ልጆቹን አሳልፎ እዲሰጥ ተገዷል፤ በየቀኑና በየደቂቃው ወያኔው
ለራሱ ህልውና ይጠቅሙኛል ብሎ በሕዘቡ ውስጥ በሚቀሰቅሳቸው ግጭቶችና ሺብር የመኖር
ዋስትናው ተናግቶ ተሰላችቶል፤ የወያኔው የውሸት ነፃ አውጭነት ፕሮፓጋንዳ ነጋ ጠባ ሆዱን ነፍቶ
አቅለሺልሾታል።
በዚሕ አይነት የወያኔው የግፍ ቀንበር ተጭኖት ሕዝባዊ ብሶቱ ለአመታት ተጠራቅሞ ቆይቶ ዛሬ
በሐገሪቱ የትኛውም ማእዘናት ሞልቶ እየፈሰሰ ነው። ታዲያ ይህ ብሶት የወለደው ሕዝባዊ ማዕበል
ማንም ሊገታው በማችል መልኩ ሊከሰት እንደሚችል ማመላከቱ ብቻ ሳይሆን ወያኔንና መሰሎቹን
መግቢያና መውጫ አሳጥቶ የሚጠራርግ ሕዝባዊ ማዕበል መሆኑ አይቀሬ ነው። ይሕ አይቀሬ የሆነው
የታሪክ ሒደት ወያኔን አስጨንቆ አሳብዶ የራስምታት በሺታ ጥሎበታል አባኖታል አንቀዠቅዦታል
የባህሩ ሞገድ ከድንጋይ ከቋጥኙ ጋር እያንከባለለ ያላትመዋል። የሕዝባዊ ብሶቱ የአደጋ ጥሪም በመረዋ
ድምፁ ተንቆርቁሮ ተዋርደን አንቀርም የሚለው ጩኸቱ ከወያኔው ጀሮ በመድረሱ የሚጨብጠውን
አሳጥቶታል። በእንቅርት ላይ ጀሮ ደግፍ እዲሉ ወያኔው በራሱ ውስጠ ሕይወት የተፈጠረው ታሞ
የማይድን አስተዳደራዊይ ግማቱ ታክሎበት አቀጣጣይ ክብሪቱን ለመለኮስ ተቀጣጣይ ቤንዚሉን
አርከፍክፎ የህዝባዊ ብሶቱን ቦንብ የመፈንዳት ፍጥነት እዲጨምር የበለጠ እየገፋው ነው። ታዲያ የጨነቀው እርጉዝ ያገባል እንደሚባለው ዛሬ ብለጣብልጡ ውያኔ ከተፈጠረበት ከፍተኛ እራስ
ምታት በሺታ የሚያድነው መዳሕኔት ባያገኝም ለጊዜውም ቢሆን ሊውጠው ሊሰለቅጠው የተቃረበውን
ሕዝባዊ ማእብል ለመግታት ማስታገሻ ኪኒን ይሆነኛል ያለውን ወያኔ ሰራሺ ኬሚስትሪ ማፈላለጉ
አልቀረም። ዘመድ ከዘመዱ አሕያ ካመዱ ሆነና አቅፈውና ደግፈው በቅጥረኝነት ያሰለፉትን አረቦች
ተመልሶ እጅ መንሳቱ ግድ ስለሆነበት የሜንጫ ፖለቲካ አራማጅ የሆኑ ኤጀንቶችን ከሲያድባሬ አክራሪ
እስላሚስት መኮንኖች ተውሶ ኦረሞ ፈርስት የተባለውን ቋንቋ ካረጁና ተስፋ ከቆረጡ ጥቂት የኦነግ
ሚሺነሪወች በማዳቀል በጀት መድቦ ጮሌ ካድሬወችን ቀጥሮ በሚቆጣጠራቸውና አዳዲስ በፈጠራቸው
ሚዲያወች በመጠቀም በውጭም በውስጥም እያተራመሰ ነው። ፈውስ ባያገኝም በጠና ከታመመበት
የእራስ ምታት በሺታ ለጊዜውም ቢሆን ጊዜ ለመግዛት ማስታገሻ ኪኒን እየወሰደ ነው። ደሮውንም
ወያኔ ሲወጠርና ሲጨነቅ ኮንዶሞቹን እንደደባል እቃ ማውጣትና ማግባት ዛሬ የተከሰተ ባለመሆኑ
ለሐገር ወዳዱ ሕዝባችን አዲስ ነገር አይሆንበትም በወያኔ ላይ ያነሳውን ሕዝባዊ አመፅ የሚያስቆም
አንዳችም ምድራዊ ሐይል የለም። የልቁንም የምስራቁ በረኛ የደጃዝማች ዑመር ሰመተርንና የደጃዝማች
ባልቻ አባ ነፍሶን የነራስ ጉብና ዳጨውንና የነ አፃ ምኔልክን የነ ራስ አበበ አረጋይንና የነ ጀኔራል
ኤጃማ ኬሎን የነ ጀኔራል ታደሰ በሩንና የነ ጀኔራል ደምሴ ቡልቱን የመሳሰሉ ጀግኖቻችን ያቆዩንን
ኢትዮጵያ አገራችን መዳፈር የዘመናት ታሪካችን አለማወቅ ይመስለኛል። ወያኔና ቅጥረኞቹ በአሁኑ
ወቅት እየደረሰባቸው ካለው ሕዝባዊ ማዕበል ለማገገም የቻሉ እየመሰላቸው አቧራው ጨሰ የተሰኘውን
የወያኔ ሰራሺ ሺብረተኛ ፕሮፖጋንዳ አጀነዳ አዲስ ግኝት አስመስለው በማራገብ ሕዝባዊ ጀግኖቻችን
ማዋረድና ማንቓሺ የወያኔውን ግባተ መሬት መቃብሩን ቁፈራ ቢያፋጥነው እንጅ ከቶውንም
ለጣረሞቱ ማስታገሻ ኪኒን ሆኖ አያገለግለውም። በውስጥም በውስጥም የምንኖር ቀለም ቀመስ
ኢትዮጵያውያን ሆይ !! ሕዝባቸህን ብሶቱ ገንፍሎ ወያኔንና ጀሌወቹን ከራሱ ላይ ለማውረድ እየታገለ
መሆኑን እናውቃለን ስለዚህ ሳናመነታ ሞላች ጎደለች ሳንጫወት የወያኔ የጥፋት ፕሮፖጋንዳ ማራገፊያ
ሳንሆን መከራ ተቀባይ የሆነውን ሕሕባችእንና ታሪካዊት ሕገራችን ከሺብርተኛ ቡድኖች ጥፋት
እንከላከል፤ እናድን !!
አገራችን በጎሳ ስም ዳግም ስልጣን ከሚናፍቁ ሺብርተኞችና
ሚሺነሪወች ጥፋት እንጠብቅ !!
መሰረት ቀለመወርቅ
አውሰተራሊ

South Sudan’s Warring Factions Meet in Ethiopia (AP)

South Sudan’s warring factions held preliminary meetings Friday ahead of the official start of negotiations in neighboring Ethiopia, mediators said.
Dina Mufti, a spokesman for Ethiopia’s Foreign Ministry, said the introductory meetings were necessary to bridge the groups’ differences ahead of direct talks expected to start Saturday. The meetings are being held at Addis Ababa’s Sheraton Hotel.
Meanwhile, both sides continue to fight in the world’s newest country, and the U.S. Embassy in Juba, the capital, said Friday the Department of State ordered a “further drawdown” of embassy personnel because of the “deteriorating security situation.” An evacuation flight was being arranged Friday, the statement said.
South Sudan’s government has declared a state of emergency in Unity and Jonglei, two states whose capitals are under rebel control. On Thursday the central government warned that rebels loyal to ousted Vice President Riek Machar were preparing to march to Juba from Bor, the capital of Jonglei state that has been the scene of fierce fighting between government troops and rebels.
South Sudan’s military said Thursday it had sent reinforcements to Bor, 120 kilometers (75 miles) from Juba.
South of Bor, thousands of families have been fleeing to the Nile River region of Awerial. Families are now camping out in the shade below any tree they can find. Aid groups estimate that tens of thousands of residents — perhaps between 60,000 and 75,000 — have streamed out of Bor in search of safety from a group of Lou Nuer attackers — fighters seen as loyal to Machar — referred to by some as the White Army.
“The White Army just took over after everybody left the village. They burned all the huts and they shoot people too during that fight. Even my mother got shot. She got a broken leg. She (is) OK,” said Phillip Madol, 33, who was one of Sudan’s “Lost Boys,” young men who were moved to the United States during the country’s old civil war when South Sudan was still part of Sudan.
“It’s hard to get medical (treatment) now,” said Madol, who studied at Grand Rapids Community College in Michigan. “All this place is way dirty. All the children are getting dirtier and sick. It’s kind of hard to tell how people survived and made it through to this side of the river.”
Toby Lanzer, the U.N.’s top humanitarian official in South Sudan, said Friday that the situation around Awerial is difficult. “We’re working to get as much aid to civilians there as possible,” he wrote on Twitter. The International Red Cross says Awerial is the “largest single identified concentration of displaced people in the country so far.”
Deng Ghai Deng, 19, fled Bor and crossed the Nile with his sister. He said fighting in Bor killed many, and he complained that the displaced families have no safe drinking water, food or shelter.
“Some of the children, even the small kids they are starving in the forest in Jonglei state,” he said. “They don’t have transport so they can cross the river into Lakes state where I am now. The situation is really very bad. My mum and dad, they are still in Jonglei state, they are still in the forest. They will not come because of money.”
President Salva Kiir insists the fighting was sparked by a coup attempt mounted by soldiers loyal to Machar on Dec. 15. But that account has been disputed by some officials of the ruling party who say the violence began when presidential guards from Kiir’s Dinka ethnic group tried to disarm those from the Nuer group of Machar. From there, violence spread across the country, with forces loyal to Machar defecting and seizing territory from loyalist forces.
South Sudan has been plagued by ethnic tension and a power struggle within the ruling party that escalated after Kiir dismissed Machar as his vice president in July. The rebels back Machar, who is now a fugitive sought by the military.
South Sudan peacefully broke away from Sudan in 2011 following a 2005 peace deal. Before that, the south fought decades of war with Sudan.

በቅሎና ፈረሰ እኩል ፈሰስ – ታደለ መኩሪያ

አቶ ዳኛቸው ቢያድግልኝ፤ ‘ልጓም የበጠሰው የፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም የስድብ ፈረስ’ በሚል አርዕስት ፕሮፌሰሩ ባቀረቧችው ሁለት ጹሑፎች ላይ ትችታቸውን አቅርበዋል። እነርሱም አበሻና ልመና፤ አበሻና ሆድ ናቸው።
አቶ ዳኛቸው የፕሮፌሰሩን ጽሑፎች መገመገማቻው ወደ ኋላ ተመልሼ አንደንድ የፕሮፌሰሩን ሥራቸው ለመከለስ አስችሎኛል፤ በዚህ አመሰግናቸዋለሁ፤ ከትችት ትምህርት ማግኘትን ግንኙነትንም ለመፍጠር መቻሉን ፕሮፌሰሩ የሚያምኑ መሆናቸውን ከአንዳንድ ጹሑፋቸው ለመረዳት ችያለሁ፤ ስለሥራቸው እንጂ ስለግድላቸው አላትትም፤ የአቶ ዳኛቸው ሐሣብ የራሳቸው መሆኑን እቀበላለሁ፤ ግን የሣቱትን በማስረጃ ለማሳየተ እሞክራለሁ፤ ጉዳዩ ስለ አቶ ዳኛቸው ወይም ስለፕሮፌሰሩ አይደለም ሁላችንንም ስለሚመለከተን የጋራ ችግር ነው።
እላይ ከቀረቡት አበሻና ልመና፤ አበሻና ሆድ ከሚሉት ውስጥ ትኩረት የሰጧቸውን ከማቅረቤ በፊተ ለግንዛቤ አቶ ዳኛቸው ቢያድግልኝ ለትችታቸው መደርደሪያ ያቀረቡት አረፍተነገር እነሆ፤ ‘ይህ ዕውቀትንና ሁኔታን ያላገናዘበ መፍትሄ የመጠቆም ፣ የማስተማር አቅምም የሌለው፣ ኢትዮጵያዊነትን የሚያዋርድ፤ ጅምላ ስድብን ሽሙጥ በተከታታይ ሲወርድብን አይቶ እንዳላየ ማለፍ ክብራችንን ለማግዶፍና ለማዋረድ ኢትዮጵያችንን ለማቋሸሽ ለሚተጉ ዱላ ማቀበል ይሆናል። ጸሐፊ እዚህ ላይ ሚናቸውን አለዩም ዱላ እያቀበሉ ያሉት፤ ክብራችንን ለአቋሽሹት ሀገራችንን ለአዋረዱት በሥልጣን ላይ ላሉት ወያኔዎች ወይስ ለፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም? ጅምላ ስድብ አበሻና ሆድ በሚለው ፡ ‘ሆድ ስላለው ወይም የሚበላው ስላለው አበሻ ነው’ ብለው በግልጽ አስቀምጠውታል፤ በጅምላ አይደለም ለማለት ነው። አእምሮውን ተጠቅሞ ከሆዱ በላይ ነፃነቱን ስለሚጠይቀው ስው ያለመሆኑን የሚጠቁም ነው። ይህን በምን አወከው? እመለሰበታለሁ። አቶ ዳኛቸው ከፕሮፌሰሩ ጹሑፎች ጨምቀው ያወጧቸውን እንይ፤ ‘በዓለም ሕዝቦች መሀከል ውድድር ቢደረግ ያለጥርጥር አበሻ አንደኛ ከሚወጣባቸው ነገሮች አንዱ ልመና ሳይሆን አይቀርም፣ ለአበሻ ልመና የኑሮ ዘዴ ነው’
ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም ከዚያ ድምዳሜ ላይ መድረሳቸው ነው አቶ ዳኛቸውን ያስቆጣቸው የሚመስለው፤ ድምዳሜ ላይ የደረሱትም ከግብተኝነት እንጂ በጥናት ላይ ያልተመሰረተ ክብራችንን ለማቋሸሽ ሆን ብሎ እንዳቀረቡት ለማመልከት ሞክረዋል።
መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ መስፍን ወልደማሪያም 2005 ዓ ም ከገጽ 194_195 ውስጥ እውነትን የመፈለጊያ ዘዴውን አስቀምጠውልናል። የተረጋገጠ እውነት ሊገኝ የሚችለው በዕውቀት ሲሆን ሌላው እውነት ከእምነት እንደሆነ ነው። ኢትዮጵያ የሃይማኖት ሀገር ሰለሆነች የእኛ እውነት የሚመነጨው ከእምነት ነው ማለት ነው። ለምርምር ለክርክር ክፍት አይደለም። ከዕውቀት የሚነሳው ደግሞ የተረጋገጠ እውነት ነው። ለምርምር ለጥያቄና ለክርክር ክፍት ነው።ፕሮፌሰሩ ያለጥርጥር አበሻው አንደኛ ከሚወጣባቸው ነገሮች አንዱ ልመና ሲሉ፤ ዕውቀቱን በተረጋገጠ እውነት ላይ መሠረቱን አድርጉ ሀብተ ሰቡን፣ ሀብተ ምድሩን ተጠቅሞ ያለማደጉንና በልመና መኖሩን ለማመላከት ነው። የዕውቀት ጉዳናን እንዳይከተል በሃይማኖት ብቻ በሚገኝ እውነት መሠረት አድርጎ ልመናን የኑሮው ዘዴ ለማድረጉ ምክንያቶችን አቅርበዋል።
‘ብልጦች እግዚአብሔርን የሚለምኑት ሥልጣን፣ ሐብትና ጉልበት ነው።እግዚአብሔር ፍርዱን እስኪሰጥ ድረስ የተለያዩ ስሞችን እየለጠፉ በተዋረድ የለማኞችን ሠራዊት ያደራጃሉ፤ ሕዝብ ሁሉ ከነዚህ የለማኞች ሠራዊት አንዱ ውስጥ ለመግባት በፉክክር ይተላለቃል፤ሠራዊት ውስጥ በመግባት የሚገኘው ጉርሻ ልጆቻቸውን እንኳን ከረሃብ የሚያድን መሆኑን ሳይገነዘቡ መብቻቸውን እያስረገጡ የሌሎችን መብት ለመርገጥ መሣሪያ ይሆናሉ።እነዚህ እንግዲህ ልመናን በማሕበረሰቡ ውስጥ ተክለው እየኮተኮቱ የሚያስፋፉ ናቸው፤ልመናን ባህል የሚያደርጉት እነዚህ ናቸው።’ በነገራችን ላይ ፕሮፌሰር መስፈን ወልደማሪያም የታወቁ ለማኝ ናቸው፤ 1950 አካባቢ የትግራይ ሕዝብ ተርቦ በግላቸው የሸዋ ገበሬዎችን ለምነው ለተራበው ሕዝብ አድረሰዋል፤ በ1966 ዓ ም ስለረሃብ አስከፊነት ለሕዝብ ሲያሰሙ በመንግሥት ታስረዋል፤ የኢትዮጵያው ዮሴፍ የሚል የቅጽል ስም አሰጥቷቸዋል።
‘አዳም አበሻ ሳይሆን አይቀርም ሁሉንም ነገር ብላ ከተባለው በቀር ብሎ ያስቀመጠው ይመስላል ፤ በላባችሁ ወዝ ብሉ ተብለው አዳምና ሔዋን መረገማቸውን አበሻ ገና አልሰማም አበሻ የተፈጠረው ገነት ውስጥ ቁጭ ብለህ ያለውን ሁሉ ብላ በተባለበት ጊዜ ነው፤እግዚአብሔር አበሻን ሁሉንም ብላ ሲለው ምንአልባት በጆሮው ጭራሽ አታስብ ብሎት ይሆናል።’ ነፃ ተፈጥሮው የፈጣሪውን ትዕዛዝ እንኳን እስከመጣስ ያደርሰዋል ግን የአበሻው አዳም ይህ ለምን ተሳነው ነው የፕሮፌሰሩ ጥያቄ፤ የሰራው ሁሉ እየተባረከለት ለሚኖርባት ፣ረሃብ፣ችጋርና በሽታ የሚባል ነገር ከማይታወቅባት ገነት ወይም ጄነት ከተባለች ሥፍራ ወደ አደገኛይቱና በውስጧም ያሉ ፍጥረታት ሁሉ በጥረቱ ካላሸነፈቸው በስተቀር ሊጎዱት ወደሚችሉባት ምድር መጣሉን የሃይማኖት ሰባኪዎች ይሰብካሉ፤ ሆኖም ፈጣሪው ሰውን ወደ ምድር ሲወረውረው ከነፃነቱ ጋር መሆኑን አይሰብኩም። አዳም ያላደረገውን እኛ ኢትዮጵያዊያን ነፃነታችን አስገፍፈን ለሆዳችን ማደራችን ስለአዳም የተነገረው አልገባንም ወይም በተሳሳተ ሁኔታ ወስደነዋል ማለት ነው። አዳም ነፃነቱን ባይሻ ኖሮ በገነት የቀረበለትን አየበላ ሆዱን እየሞላ ይኖር ነበር። ግን የማወቅ ነፃነቱን ፈለገ፣ ከሆድ ነፃነትን መረጠ፤ለዚህም ዋጋ ከፈለ፤ ከገነት ወይም ጄነት ተባረረ፤ በምድር ሰው በሰው ጭቆናን ለመቋቋም ብዙዎች ሕይወታቸውን ሰጥተዋል፤ በሀገራችንም ለነፃነታቸው ብዙዎች በእስር በግድያ እየተሰቃዩ ይገኛሉ፤ ፕሮፌሰሩ በመግቢያቸው እንደጠቀሱት ሆድ ሰላለው ወይም ሰለሚበላው አበሻ ነው ትንታኔ ያቀረቡት በአጭሩ ሕግ አዳምን ጥሶ ለሆዱ ያደረ ማለታቸው ነው። ለነፃነታችን ካልቆምን እኛንም ይጨምራል። በነፃነት፣ በፍትሕ፣ ሕግ አስከብረን እየኖርን ቢሆን ሆዳምነት ስድብ አይሆንም ነበር። አቶ ዳኛቸው ከነጮቹ በላይ ሆነን ነው ወይ የምንሰደበው ብለው በቁጭት ሐሣባቸውን ገልጸዋል፤ አሁን አሳቡ የገባቸው ይመስለኛል።
ከአቶ ዳኛቸው ቢያድግልኝ ጋር አንድ የምጋራቸው ሐሣብ አለኝ፤ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማሪያም የሚታወቁት ከንጉሡ ጀምሩ በአስተዳደሩ ላይ ቅዋሜ በማሰማት መፍትሄም በማቅረብ ነበር።መሪዎቹ አልሰማ ማለታቸውን ተረድተው ይመስላል ድርና ማግ ሆነው በመብት ግፈፋው ላይ ከተሰማሩት ስብስቦች ላይ ጹሑፋቸው ያተኩራል፤ ያም ሁኔታ ከወያኔ ጋር እየዘረፉ እያዘረፉ ገለው እያስገደሉ ከሰላማዊ ሕዝብ ጋር ተቀላቅለው ወያኔ ወያኔ የሚሉትን ነጥሎ ለማውጣት ያነጣጠረ ይመስላል።
የአቶ ዳኛቸው ቢያድግልኝ ወቀሳ መሰል ትችት ከቃላት አመራረጥ የቸግሩን ምንጭ ለማግኘት ያለመጣር ዳተኛነትን ያጸባርቃል። ብዕራቸው መልክቱ ላይ ሳይሆን መልክተኛው ላይ ያተኮረ ይመስላል። በኦሮሞኛ አንድ ተረት አለ ‘ኡዳን ኪያ ሚኒን ኪያሚቲ’ አይን ምድሩ የኔ ነው የኮሶ ትሉ የኔ አይደለም፤ ይህን ፓራሣይት የኮሶ ትል መራራውን ኮሶ ጠጥቶ ከማስወገድ ይልቅ ኮሶ ማታ በማለት ማባበሉ የኮሶ ትሉን አያስወግደውም።
tadele@shaw.ca

በቅሎና ፈረሰ እኩል ፈሰስ – ታደለ መኩሪያ

አቶ ዳኛቸው ቢያድግልኝ፤ ‘ልጓም የበጠሰው የፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም የስድብ ፈረስ’ በሚል አርዕስት ፕሮፌሰሩ ባቀረቧችው ሁለት ጹሑፎች ላይ ትችታቸውን አቅርበዋል። እነርሱም አበሻና ልመና፤ አበሻና ሆድ ናቸው።
አቶ ዳኛቸው የፕሮፌሰሩን ጽሑፎች መገመገማቻው ወደ ኋላ ተመልሼ አንደንድ የፕሮፌሰሩን ሥራቸው ለመከለስ አስችሎኛል፤ በዚህ አመሰግናቸዋለሁ፤ ከትችት ትምህርት ማግኘትን ግንኙነትንም ለመፍጠር መቻሉን ፕሮፌሰሩ የሚያምኑ መሆናቸውን ከአንዳንድ ጹሑፋቸው ለመረዳት ችያለሁ፤ ስለሥራቸው እንጂ ስለግድላቸው አላትትም፤ የአቶ ዳኛቸው ሐሣብ የራሳቸው መሆኑን እቀበላለሁ፤ ግን የሣቱትን በማስረጃ ለማሳየተ እሞክራለሁ፤ ጉዳዩ ስለ አቶ ዳኛቸው ወይም ስለፕሮፌሰሩ አይደለም ሁላችንንም ስለሚመለከተን የጋራ ችግር ነው።
እላይ ከቀረቡት አበሻና ልመና፤ አበሻና ሆድ ከሚሉት ውስጥ ትኩረት የሰጧቸውን ከማቅረቤ በፊተ ለግንዛቤ አቶ ዳኛቸው ቢያድግልኝ ለትችታቸው መደርደሪያ ያቀረቡት አረፍተነገር እነሆ፤ ‘ይህ ዕውቀትንና ሁኔታን ያላገናዘበ መፍትሄ የመጠቆም ፣ የማስተማር አቅምም የሌለው፣ ኢትዮጵያዊነትን የሚያዋርድ፤ ጅምላ ስድብን ሽሙጥ በተከታታይ ሲወርድብን አይቶ እንዳላየ ማለፍ ክብራችንን ለማግዶፍና ለማዋረድ ኢትዮጵያችንን ለማቋሸሽ ለሚተጉ ዱላ ማቀበል ይሆናል። ጸሐፊ እዚህ ላይ ሚናቸውን አለዩም ዱላ እያቀበሉ ያሉት፤ ክብራችንን ለአቋሽሹት ሀገራችንን ለአዋረዱት በሥልጣን ላይ ላሉት ወያኔዎች ወይስ ለፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም? ጅምላ ስድብ አበሻና ሆድ በሚለው ፡ ‘ሆድ ስላለው ወይም የሚበላው ስላለው አበሻ ነው’ ብለው በግልጽ አስቀምጠውታል፤ በጅምላ አይደለም ለማለት ነው። አእምሮውን ተጠቅሞ ከሆዱ በላይ ነፃነቱን ስለሚጠይቀው ስው ያለመሆኑን የሚጠቁም ነው። ይህን በምን አወከው? እመለሰበታለሁ። አቶ ዳኛቸው ከፕሮፌሰሩ ጹሑፎች ጨምቀው ያወጧቸውን እንይ፤ ‘በዓለም ሕዝቦች መሀከል ውድድር ቢደረግ ያለጥርጥር አበሻ አንደኛ ከሚወጣባቸው ነገሮች አንዱ ልመና ሳይሆን አይቀርም፣ ለአበሻ ልመና የኑሮ ዘዴ ነው’
ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም ከዚያ ድምዳሜ ላይ መድረሳቸው ነው አቶ ዳኛቸውን ያስቆጣቸው የሚመስለው፤ ድምዳሜ ላይ የደረሱትም ከግብተኝነት እንጂ በጥናት ላይ ያልተመሰረተ ክብራችንን ለማቋሸሽ ሆን ብሎ እንዳቀረቡት ለማመልከት ሞክረዋል።
መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ መስፍን ወልደማሪያም 2005 ዓ ም ከገጽ 194_195 ውስጥ እውነትን የመፈለጊያ ዘዴውን አስቀምጠውልናል። የተረጋገጠ እውነት ሊገኝ የሚችለው በዕውቀት ሲሆን ሌላው እውነት ከእምነት እንደሆነ ነው። ኢትዮጵያ የሃይማኖት ሀገር ሰለሆነች የእኛ እውነት የሚመነጨው ከእምነት ነው ማለት ነው። ለምርምር ለክርክር ክፍት አይደለም። ከዕውቀት የሚነሳው ደግሞ የተረጋገጠ እውነት ነው። ለምርምር ለጥያቄና ለክርክር ክፍት ነው።ፕሮፌሰሩ ያለጥርጥር አበሻው አንደኛ ከሚወጣባቸው ነገሮች አንዱ ልመና ሲሉ፤ ዕውቀቱን በተረጋገጠ እውነት ላይ መሠረቱን አድርጉ ሀብተ ሰቡን፣ ሀብተ ምድሩን ተጠቅሞ ያለማደጉንና በልመና መኖሩን ለማመላከት ነው። የዕውቀት ጉዳናን እንዳይከተል በሃይማኖት ብቻ በሚገኝ እውነት መሠረት አድርጎ ልመናን የኑሮው ዘዴ ለማድረጉ ምክንያቶችን አቅርበዋል።
‘ብልጦች እግዚአብሔርን የሚለምኑት ሥልጣን፣ ሐብትና ጉልበት ነው።እግዚአብሔር ፍርዱን እስኪሰጥ ድረስ የተለያዩ ስሞችን እየለጠፉ በተዋረድ የለማኞችን ሠራዊት ያደራጃሉ፤ ሕዝብ ሁሉ ከነዚህ የለማኞች ሠራዊት አንዱ ውስጥ ለመግባት በፉክክር ይተላለቃል፤ሠራዊት ውስጥ በመግባት የሚገኘው ጉርሻ ልጆቻቸውን እንኳን ከረሃብ የሚያድን መሆኑን ሳይገነዘቡ መብቻቸውን እያስረገጡ የሌሎችን መብት ለመርገጥ መሣሪያ ይሆናሉ።እነዚህ እንግዲህ ልመናን በማሕበረሰቡ ውስጥ ተክለው እየኮተኮቱ የሚያስፋፉ ናቸው፤ልመናን ባህል የሚያደርጉት እነዚህ ናቸው።’ በነገራችን ላይ ፕሮፌሰር መስፈን ወልደማሪያም የታወቁ ለማኝ ናቸው፤ 1950 አካባቢ የትግራይ ሕዝብ ተርቦ በግላቸው የሸዋ ገበሬዎችን ለምነው ለተራበው ሕዝብ አድረሰዋል፤ በ1966 ዓ ም ስለረሃብ አስከፊነት ለሕዝብ ሲያሰሙ በመንግሥት ታስረዋል፤ የኢትዮጵያው ዮሴፍ የሚል የቅጽል ስም አሰጥቷቸዋል።
‘አዳም አበሻ ሳይሆን አይቀርም ሁሉንም ነገር ብላ ከተባለው በቀር ብሎ ያስቀመጠው ይመስላል ፤ በላባችሁ ወዝ ብሉ ተብለው አዳምና ሔዋን መረገማቸውን አበሻ ገና አልሰማም አበሻ የተፈጠረው ገነት ውስጥ ቁጭ ብለህ ያለውን ሁሉ ብላ በተባለበት ጊዜ ነው፤እግዚአብሔር አበሻን ሁሉንም ብላ ሲለው ምንአልባት በጆሮው ጭራሽ አታስብ ብሎት ይሆናል።’ ነፃ ተፈጥሮው የፈጣሪውን ትዕዛዝ እንኳን እስከመጣስ ያደርሰዋል ግን የአበሻው አዳም ይህ ለምን ተሳነው ነው የፕሮፌሰሩ ጥያቄ፤ የሰራው ሁሉ እየተባረከለት ለሚኖርባት ፣ረሃብ፣ችጋርና በሽታ የሚባል ነገር ከማይታወቅባት ገነት ወይም ጄነት ከተባለች ሥፍራ ወደ አደገኛይቱና በውስጧም ያሉ ፍጥረታት ሁሉ በጥረቱ ካላሸነፈቸው በስተቀር ሊጎዱት ወደሚችሉባት ምድር መጣሉን የሃይማኖት ሰባኪዎች ይሰብካሉ፤ ሆኖም ፈጣሪው ሰውን ወደ ምድር ሲወረውረው ከነፃነቱ ጋር መሆኑን አይሰብኩም። አዳም ያላደረገውን እኛ ኢትዮጵያዊያን ነፃነታችን አስገፍፈን ለሆዳችን ማደራችን ስለአዳም የተነገረው አልገባንም ወይም በተሳሳተ ሁኔታ ወስደነዋል ማለት ነው። አዳም ነፃነቱን ባይሻ ኖሮ በገነት የቀረበለትን አየበላ ሆዱን እየሞላ ይኖር ነበር። ግን የማወቅ ነፃነቱን ፈለገ፣ ከሆድ ነፃነትን መረጠ፤ለዚህም ዋጋ ከፈለ፤ ከገነት ወይም ጄነት ተባረረ፤ በምድር ሰው በሰው ጭቆናን ለመቋቋም ብዙዎች ሕይወታቸውን ሰጥተዋል፤ በሀገራችንም ለነፃነታቸው ብዙዎች በእስር በግድያ እየተሰቃዩ ይገኛሉ፤ ፕሮፌሰሩ በመግቢያቸው እንደጠቀሱት ሆድ ሰላለው ወይም ሰለሚበላው አበሻ ነው ትንታኔ ያቀረቡት በአጭሩ ሕግ አዳምን ጥሶ ለሆዱ ያደረ ማለታቸው ነው። ለነፃነታችን ካልቆምን እኛንም ይጨምራል። በነፃነት፣ በፍትሕ፣ ሕግ አስከብረን እየኖርን ቢሆን ሆዳምነት ስድብ አይሆንም ነበር። አቶ ዳኛቸው ከነጮቹ በላይ ሆነን ነው ወይ የምንሰደበው ብለው በቁጭት ሐሣባቸውን ገልጸዋል፤ አሁን አሳቡ የገባቸው ይመስለኛል።
ከአቶ ዳኛቸው ቢያድግልኝ ጋር አንድ የምጋራቸው ሐሣብ አለኝ፤ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማሪያም የሚታወቁት ከንጉሡ ጀምሩ በአስተዳደሩ ላይ ቅዋሜ በማሰማት መፍትሄም በማቅረብ ነበር።መሪዎቹ አልሰማ ማለታቸውን ተረድተው ይመስላል ድርና ማግ ሆነው በመብት ግፈፋው ላይ ከተሰማሩት ስብስቦች ላይ ጹሑፋቸው ያተኩራል፤ ያም ሁኔታ ከወያኔ ጋር እየዘረፉ እያዘረፉ ገለው እያስገደሉ ከሰላማዊ ሕዝብ ጋር ተቀላቅለው ወያኔ ወያኔ የሚሉትን ነጥሎ ለማውጣት ያነጣጠረ ይመስላል።
የአቶ ዳኛቸው ቢያድግልኝ ወቀሳ መሰል ትችት ከቃላት አመራረጥ የቸግሩን ምንጭ ለማግኘት ያለመጣር ዳተኛነትን ያጸባርቃል። ብዕራቸው መልክቱ ላይ ሳይሆን መልክተኛው ላይ ያተኮረ ይመስላል። በኦሮሞኛ አንድ ተረት አለ ‘ኡዳን ኪያ ሚኒን ኪያሚቲ’ አይን ምድሩ የኔ ነው የኮሶ ትሉ የኔ አይደለም፤ ይህን ፓራሣይት የኮሶ ትል መራራውን ኮሶ ጠጥቶ ከማስወገድ ይልቅ ኮሶ ማታ በማለት ማባበሉ የኮሶ ትሉን አያስወግደውም።
tadele@shaw.ca

Tuesday 31 December 2013

ትንሽ ስለ ሜንጫ ፓለቲካ ባህሪያት (ሳምሶን. ብ. ለንደን )

        ባንዲራ ጨርቅ ነው ፤ የአክሱም
menchaሐውልት ለወላይታው ምኑ ነው ? ኢትዮጵያ ሀገራዊ ህልውና የመቶ አመት ጉዳይ ነው ፤ ያለ ‘ብሄሮች ፈቃድ’ የኢትዮጲያ ነገር አከተመለት ከተባለ 23 አመታት በሁዋላ ሰሞኑን ጎሰኝነትና የከርሞው ‘ ኢትዮጵያ ለምኔ’ ቱማታ እንደገና ‘በህዳሴ’ ብቅ ማለት የጀመረ ይመስላል። ምስጋና ‘ለወጣቱ ምሁር’ ጃዋር መሀመድ ይድረሰውና ! ጃዋር ብቻውን ስላይደለ እንቅስቃሴውም የተደራጀ እንደመምሰሉ ለዚህ ጽሁፍ ይሆን ዘንድ ‘የሜንጫ ፖለቲካ’’ ስል እሰይመዋለሁ። ይህን ስያሜ የመምረጤ አብይ ምክንያት የዚህ ቡድን አባላት ቢሳካላቸው ተፈጸመብን የሚሉትን የፓለቲካ አድልዎና በደል ሊያርሙ የሚመርጡት  መንገድ  ግፍን በግፍ የማረም መሆኑን ለማስገንዘብ ነው። አንባቢዎች በዚህ ምትክ ያሻቸውን ስያሜ ሰጥተው ሊጠቀሙ መብታቸው ነው።
በዚህ ጽሁፍ በኦሮሞ ማህበረሰብ ኢትዮጵያዊነት ላይ በሀገራችን ነገስታት የስልጣንና ሀብት ቅርምት በይበልጥም የግዛት ማስፋፋት ሂደት ውስጥ የተፈጸሙትን ሁነቶች በተመለከተ  የጭብጥ ክርክር ውስጥ ብዙም አልገባም።ለዚህም በርካታ ምክንያቶች አሉኝ፤፡ አንዱና ዋናው ምክንያት አዲሶቹ  ጎሰኞች በመረጃና ታሪክ ጠቀስ ክርክር  እምብዛም ስለሆኑ ነው፡፡ ለምሳሌ የታሪክ ነክ ክርክሮችን በኢትዮጵያውያን አዋቂዎች ድርሳናት ማመሳከር አይቻልም ፤  በእነርሱ የጨዋታ ሕግ መሰረት ኢትዮጵያውያን የታሪክ  አዋቂዎች ሁሉ ‘ደብተራዎች’ ናቸው ፤ ስራቸው ለምስክርነት የማይቀርብ ። የአውሮፓውያኑን  ድርሳናት ማመሳከር ደግሞ ፈረንጆቹን ‘በነጭ ነፍጠኝነት’ ያስከስሳል። ሁለተኛው ምክንያቴ ደግሞ የክርክራቸው አሰልቺነት ነው። የተዛባ ማስረጃና ጩሀት ተደጋግሞ ስለተነገረ እውነት የሚሆን ይመስል ውሃ ወቀጣ ይበዛዋል ፡፤ ኢትዮጵያ ከህወሃት መንግስት በፊት ከኦሮሞዎች  በቀር ለተቀሩት ብሄረሰቦች በተለይም ለአማራው ‘ምድራዊ ገነት’ እንደነበረች ነው ተደጋጋሚው ስብከቱ።  የባሌ ኦሮሞ በቀዳማዊ ሀይለስላሴ ላይ ሲያምጽ የጎጃም ሰው ቤቱ በሰላም ውሎ የገባ  ይመስል አልያም የወሎ ሰው በረሃብ ሲጠቃ ንጉሱ ‘ ወገኔን’ ብለው ያደሉለት ይመስል። እሺ ካለፈው የተማረ ስረአት መመስረት ላይ ለምን አይሆንም ውይይቱ ለሚል መልስ የለም ፤ ዘፈኑ ተመልሶ ወደ ሚኒሊክ ፤ ሲያሻው ወደ ሃይለስላሴ ይሄዳል ፤፡ የፊትን የማየት ነገር የሚባል ልማድ እዚያ አካባቢ የለም ፡ እንዲያውም ‘በትምክተኝነትና ሴረኛ አማራነት’ ያስከስሳል። ከሁሉም ከሁሉም ከእንደዚህ   አይነት ሰዎች ጋር ረብ ያለው ውይይት ማድረግ የማይቻለው የእልህና ቁጣ ፖለቲካ መልመዳቸው ነው። ለምን ማህበራዊ ድረ ገጽ ላይ አይሆንም የሀሳባቸውን ፋይዳ ቢስነት መተቸት ቁጣና ለከት የሌለው ዘለፋ ያስከትላል። እናም ለጊዜው  ይህን ጽሁፍ ሰሞኑን ፈገግ አለያም እንዴ ባሰኙኝ ጉዳዮች እንዲያተኩር አደርጋለሁ።
‘የሜንጫ ፖለቲካ’’ ዋንኛ ባህሪው እንደ አብዛኛው አፍሪካዊ  አፋጣኝ ስልጣን ፈላጊ  የፓለቲካ ልሂቅ የቆየ ብሶትን መቆስቆስ መሰረት ያደረገ ነው ። ፈረንጆች ግሪቫንስ ፓለቲክስ እንዲሉ። የአፍሪካ ፓለቲካ ልሂቃን  በዚህ የተካኑ ናቸው የ እኛዎቹን ጨምሮ : ታሪካዊ ፤ ነባራዊና ማህበራዊ ልዩነቶችን ፣ እነዚህ ውስጥ ያሉ ክፍተቶችን እንዴት ተጠቅመው ተከታዮቻቸውን ማባዛት በተለይም በምሬት ማነሳሳት ያውቁበታል። በሀገራችን ከድህረ ወያኔ መራሄ መንግስትነት  በሁዋላ ይሄ ስልት የፓለቲካ ወደጅና ጠላትን ከመፈረጅ  ባለፈ የፌዴራል አደረጃጀቱን ፤ የመሬት ስሪቱንን ያልተጻፈውን የኢኮኖሚ ፓሊሲና ከሁሉም ከሁሉም የፓለቲካ ስርአቱን ቅርጽና ይዘት ለማደራጀት ጠቀሜታ ላይ ውሏል። እንደ አብዮታዊ ዲሞክራሲያውያኑ እይታ ትልቁ የፓለቲካ ፋይዳቸው ‘ስልጣን ተመልሶ ነፍጠኞችና ትምክተኞችና ያለፈው ስርአት  ናፋቂዎች እጅ እንዳይገባ ማድረግ ነው። ያ እንዲሆን ደግሞ በየጎጡ የተሰለፈው የፓለቲካ ልሂቅና ጀሌው ትናንት ጡትህን ሲቆርጡህ የነበሩትን ፤ ትናንት እንዲህ ሲሉህ የነበሩትን እያሸንልህ ነው አንተም ክንድ አበድረን ይባላል። በፕሮፓጋንዳ ስሜቱ የተንቦገቦገ  ቆም ብሎም አያስብም  በክንድ ፈንታ የክላሹን ቃታ ነው የሚስበው፡፡
የሚገርመው እነ ጃዋር ይሄንን ለ23 አመታት ስንሰማው  የነበረውን ዜማ ከልሰው ፤ አራዶች እንደሚሉት ‘ሪሚክስ’ አድርገው በአዲስ መልኩ ሊያቀርቡት መፈለጋቸው ነው። ይህ ሕዝብን ከሕዝብ የማባላትና በሂደቱም ስልጣንን የማቆየት ዘዴ የዛሬን አያርገውና ‘ እኒያን ሽርጣም ሲሉዋችሁ የነበሩትን ነፍጠኞች በሉዋቸው ሲባል ተቀኝቶለታል በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ታምራት ላይኔ ። ይህንን ተከትሎ ዘርና ደም እየተቆጠረ ከስራ ማባረር ፤ እስርና ግድያ በብዙዎች ላይ ተፈጽሞአል።  እንዲህ አይነቱ ግፍ በቀደሙት ስርአት ግፉአን ነበሩ የተባሉትን ብሄረሰቦችና የማህበረሰብ ክፍሎች ቁስሎች ያሽሩ ይሆን ? የለም ! ወያኔ ስልጣኑን ለማደላደል በተጠቀመበት በዚህ አይነቱ የመስዋእት በግ አሰሳ ዋና ተሳታፊ የነበሩ እንደ ኦነግ ያሉ ድርጅቶች  ፤ ነፍጠኛው ነው የሚፈጀው እኛ ምን ከዳችን ሲሉ ከዳር ቆመው የነበሩ ኦሮሞዎችም በሁዋላ ላይ የስርአቱ አዶ ከበሬ ደምና የእስር ቤት ግብር ሲሻ ገፈቱን ቀምሰውታል ፤ ዛሬም ድረስ በሺዎች የሚቆጠሩ ንጹሃን የዝዋይና ሸዋ ሮቢትን እስር ቤቶች ታጉረውም ይገኛሉ።  የሽግግር ( እናታችን የችግር ትለዋለች) ስርአቱ ሲመሰረት ነጻ አውጪ ነን ሲሉ የተሰባሰቡት ፓለቲከኞች ከብሶትና በቀል ፓለቲካ አርቀው አይተው ብሄራዊ መግባባትን ፈጥረው ቢሆን ኖሮ ይሀው ዛሬም እቀድሞ ሲዜም የነበረው  ቢሊሱማና ወልቂጡማ  የሚኒያፓሊስን ተራሮች  አያንቀጠቅጣቸውም ነበር።
ከአስገራሚዎቹ ‘የሜንጫ ፖለቲካ’’ ባህሪያት መሀከል ዋናው ደግሞ ተጋፊነቱና ኢፍትሀዊ አመለካከቱ ነው። ሰሞኑን እንደምናነበውና እንደምንሰማው ከሆን የእነ ጃዋር ‘ኦሮሚያ’ እውን ትሆን ዘንድ የሌሎቻችን መብቶች ሁሉ መታቀብ አለባቸው። አዲሶቹ ነጻ አውጪዎች  ወገኖቻችን ለሚሉዋቸው  የህብረተሰብ ክፍሎችና ብሄረሰቦች ወደፊት ሊቸሩዋቸው ከሚያሰቡአቸው መብቶች ውስጥ የተወሰኑትን ለእኛ ለወደፊቱ ጎረቤቶቻቸው ባይነፍጉን ምናለ? እነ ጃዋር የኢትዮጵያ ሙስሊሞች (ሰሞኑን ወደ ኦሮሞ ሙስሊሞች ወረድ ብሎ ይሆናል ) በሀገሪቱ እኩል የእምነት ነጻነትን በሰበኩበት አንደበታቸው እነርሱ ሰፈር ቤተስኪያን ሊሰራ ላሰበ አማኝ ለምን  ሜንጫ ይመኙለታል ? እነርሱ የራሳቸውን የታሪክ ድርሳናት አማክረው በአደባባይ የሚዘልፉትን ፤ የተቀረው አለም ቢያንስ ቢያንስ ‘’በማያዳግም መልኩ የነጭን ሰራዊት ለመጀመሪያ ጊዜ ድባቅ የመታ  ሕዝብን የመራ ንጉስ’’  ሲል የመሰከረለትን መሪ የለም ስሙን በደግ አታንሱ ይላሉ። የእነርሱ ህልም እውን ይሆን ዘንድ ያለፈ ታሪክን መልካም ገጽ ማንቆላጰስና በሂደቱም ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት መታቀብ አለባቸው ። ለምሳሌ እነርሱ ሚኒሊክ ፈጸሙት የሚሉትን ግፍ ለማስታወስ ሙዙየም ማሰራታቸውን ፤ ሃውልት ማቆማቸውን ሌላው ማህበረሰብ በዝምታ ሲያልፈው ታሪክን በሌላ ገጽ የሚመለከተው  ማህበረሰብ ለምን የእነርሱን ያህል መብት እንዲያጣ ይፈለጋል? ከዚሁ በተጓዳኝ ከሁሉም የሚያሳፍረው ተግባር  ደግሞ የእነርሱን  ጽንፍ የነካ ዘረኝነት የማይጋሩ ኦሮሞዎች ላይ የሚያደርሱት ጫና ነው። ትናንት ከመገንጠል ውጭ አማራጭ የለም ሲሉ ይታገሉ የነበሩ ፤ ዛሬ ደግሞ የለም ከብሄራዊው ዳቦ የድርሻችንን ነው ለማግኘት መታገል  ያለብን የሚሉ ጎምቱ የኦሮሞ ፖለቲከኞች  አይደለም ሀሳባቸው ሊሰማ በመጀመሪያ ከሜንጫ ፓለቲከኞች  የኦሮሞነት መታወቂያ ማግኘት አለባቸው።  እንዲያ በማሰባቸው ብቻ ‘ጎበናዎች’ ይሆናሉ በአንድ ሌሊት ። ይሄ ተዋልጄያለሁ ተዛምጄያለሁ የሚለውን ኦሮሞማ ለጊዜው መተው ነው ፤ ሲጀመርም እንደ ‘አርያን ሜንጪስት’ አይቆጠርም።
ሌላው  ‘ የሜንጫ’ ፖለቲከኞች መለያ ፤ የተከታይን ቀልብ ይስባል ተብሎ የሚታሰበውን ሁሉ ፍለጋ ከዛፍ ዛፍ መዝለል። ባለፈው የስኮትላንዱ ፈረስት ሚኒስትር አሌክስ ሳልመንድ የስኮትላንድን የሪፈረንደም ማኒፌስቶ ባወጀ ሰሞን እነ ኦቦ ጃዋርም የወንድም ሀገር ስኮትላንድ  አርአያነት ለተከታዮቻቸው ይሰብኩ ገቡ። እነርሱ ዘንድ ዩናይትድ  ኪንግደም የአራት ሀገራት ህብረት እንደሆነች ፤ ስኮትላንድ ከሕብረቱ ወጣች አልወጣች የራሳ ብሄራዊ አስተዳደር እንዳላት አይታወቅም።  የትም ይሁን የት ብቻ (ቲቤት ይሁን ፑንትላንድ፤ ኪውቤክ ይሁን ሞኖሶታላንድ ) የብሄራዊ ማንነት ጥያቄ ይነሳ ከኢትዮጵያ ነባራዊ ሁናቴ ጋር ይዛመድ አይዛመድ  እነ ሜንጫ በፍጥነት ‘ ላይክ’ ያደርጋሉ። ይሄው ፈገግ አድርጎን ብዙም ሳንቆይ ደግሞ በማንዴላ እልፈተ ሞት ምክንያት  የእነ ጀነራል ታደሰ ብሩና ኮሎኔል ፍቃዱ ዋከኔ  ገድል መነሳት ጀመረ። እንደ ልማዳቸው የእኛዎቹ  ‘ የነጻነት ታጋዮች ’ አጋጣማውን ለግልብ የፓለቲካ ገበያ ሊጠቀሙበት ተንጠለጠሉበት፡፤ ማንዴላ እንደ ሁለተኛ ሐገሬ ነው የማያት ያሏት ኢትዮጵያ ፤ እነ ጀነራል ታደሰ ብሩና ኮሎኔል ፍቃዱ ዋከኔ  የተዋደቁላት ኢትዮጵያ ‘በፎቶ ሾፕ’ ከምስሉ ወጣችና የመኮንኖቹ  ጎሳና ደም ተቆጥሮ   በአንድ ሌሊት ታሪክ ተቀይሮ ማንዴላ ‘ከኦሮሚያ’ የጦር ልምምድ ስልጠና አግኝተው ነበር ተባለ።  የእነ ማንዴላ ቁስል አድራቂነት ፤ አስታራቂነት ፤ ዘርና ማህበራዊ ክፍፍል ያላሸነፈው የፓለቲካ ርእዮትማ  ማን ያስተውለው ? ለስሜትና ብሶት ፖለቲካ አይመችማ !
ዘግየት ብሎ ደግሞ ‘የሜንጫ ፓለቲካ’ የተመልካቾችን ቀልብ ይገዛልኛል ፣ ተከታዮቼንም ያበዛል በሚል  ስልት ታዋቂው አቀንቃኝ ‘ቴዲ አፍሮ’  ላይ እመር ብሎ ሰፍሯል።  እነ ጃዋር ቀድሞውንም ቢራ በአፋቸው  አይዞርም የሚባልላቸውንና  ከአማርኛ ሙዚቃ ከተፋቱ 23 አመት የሞላቸውን ‘ወገኖቻቸውን’ ፤ ቢራ አትጠጡ ሙዚቃም  አታድምጡ  እያሏቸው ነው። ለዚህ ዘመቻቸው ሰበቡ  ያው የፈረደባቸው ምኒሊክ ለምን ተወደሱ ነው። ይሄ እንግዲህ የፓለቲካ ‘ ስትራቴጂስቱ’ ኦቦ ጃዋር እንደ አስማተኛ ሊያጃጅለን እፊታችን  ያቀረበው  ‘ቀይዋን  ያየ’ መሆኑ ነው። በእርሱ ቤት  እኛ ‘የታላቂቷን ኦሮሚያ’  የመመስረት ቅዠት አናውቅም ፣ ይህ ሕልም እውን ይሆን ዘንድ ገና አንድ ሺ አንድ ሰበቦች እንደሚደረደሩም እሚገባን  አይደለንም። ከዚሁ ጋር በተያያዘ አስቂኙ የሜንጫ ፓለቲከኞች ሰሞናዊ ተግባር ደግሞ ይህቺን ጊዜያዊ ትርኢታቸውን ለማሳመር  በአርባና አምሳ ሺ እስር ቤት አጎረን ያሉት ወያኔን ‘አስኮቱ’ ማለታቸው ነው። ቴዲ አፍሮ ‘ በአስራ ሰባት መርፌ’                         ሲል የተዘባበተብህ እኛንም አጥንታችን ድረስ ዘልቆ ይሰማናል አሉታ ክንዱን ሊዋሱት። ህወሃት ምላጭ መሆኑን ከአጎቶቻቸው  ‘የሽግግር’ ጊዜው ታሪክ የተማሩም አይመስሉም ። ወያኔ ዛሬ ቴዲን ቢበላ በአንድ ጎጆ ሁለት አባወራ እንደማይኖር ስለሚያምን  ነገ የእነ ጃዋርን ጆሮ እንደሞቆረጥም ልብ ያሉ አይመስልም።  ለማንኛውም እነ ሜንጫ ፓለቲከኞች እደጃችን የቆመውን  አስቀያሚ  ሁነት እንድናውቀው ስለወተወቱን  እናመሰግናቸዋለን። ሲሆን  በአንድነት ቆመን ‘እምቢ ለዘረኝነት’ ብለን እናቆማቸዋለን ፣ አይሆንም እንደለመድነው እርስ በራሳችን እየተጯጯህን በሩን የምንከፍትም ከሆነ ሜንጫው የት እንደሚያርፍ ማሰቢያ ጊዜ አለንና ተመስገን ነው።
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር
ሳምሶን. ብ. ለንደን

የጃዋር መሀመድና የአንዳንድ አጨብጫቢዎች አደገኛ መንገድ በአጭሩ

December 31, 2013
ዋቅጅራ ሶሪ
“በእናቴ መንዜና ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ነኝ፤ በአባቴ የአርሲ ኦሮሞ እና ሙስሊም ነኝ፤ ከኔ ወዲያ ለኢትዮጵያዊነት ምልክት ሊሆን የሚችል የለም” ጃዋር ይህን ያለው ከዓመት በፊት ወጣቱ ተንታኝ እየተባለ በኢሳት  በተደጋጋሚ ይቀርብ የነበረ ሰሞን ነው።Jawar Mohamed Muslim fundamentalist
የተመቼው እና ፖለቲካዊ ንግዱ የደራለት  ሲመስለው ከኢትዮጵያውያን ጋር ተመሣስሎና አድፍጦ የቆየው ጃዋር  መሀመድ ፤በግብጽ የመንግስት ለውጥ መደረጉን ተከትሎ የሙርሲ ባለስልጣናት በአባይ ግድብ ያደረባቸውን ንዴት በግልጽ በቴሌቪዥን  ተሰባስበው እየፎከሩ በኢትዮጵያ ላይ እርምጃ ለመውሰድ ሲዝ ቱ  ሰማ። የሙርሲ ባለስልጣናት  ከሰነዘሯቸው አማራጮች አንዱ፦” የኦሮሞ ነፃነት ግንባርን የሙስሊም ክንፍ ወይም ኦብነግን ማስታጠቅና መርዳት” የሚል መሆኑን የሰማው ጃዋር ሳይውል ሳያድር በአልጀዚራ ላይ ቀርቦ በግልጽ “ኦሮሞ ፈርስት” በማለት የኢትዮጵያዊነት ቆቡን አሽቀንጥሮ ጣለ። ሜንጫው ተከተለ፤የሙስሊሞችን የመብት ትግል ከኦነግ ጋር እያገናኘ ተናገረ፣ ኢትዮጵያውያን ከኦሮሚያ ይውጡ! እያለ መፈክር ሲያሰማ ተደመጠ…
እባብ ልቡን ዐይቶ እግር ነሳው እንዲሉ፤ አምላክ የሙርሲን መንግስት በአጭሩ ቀጨው እንጂ፤ የሙርሲ ሰዎች በስልጣናቸው ቢቀጥሉ ኖሮ የጃዋር መንገድ ወዴት ወዴት እንደነበር መገመቱ ቀላል ነው።
ከክፉ መንገዱ ሊመለስ ያልቻለው ጃዋር በቅርቡ በሳዑዲ አረቢያ በወገኖቻችን ላይ የደረሰባቸውን መከራ ተከትሎ በኖርዌይ የሚገኙ ተከታዮቹ “እኛ ኢትዮጵያውያን አይደለንም! ወንጀለኞች አይደለንም!” በማለት ስለወጡት እና የበርካቶችን ልብ ስላደማው ሰልፍ “ትክክል ነው” ብሎ ፃፈ። ሌላም ኢትዮጵያዊነትን የሚፃረር በርካታ ነገሮች ፃፈ፣ ተናገረ።
ጃዋር በአጭር ጊዜ እነኚህን ሁሉ ስህተቶች አድርጓል። ፈጽሟል። ኢትዮጵያዊ ነኝ ለሚል እና በትክክል ስለ አገር ምንነት ለገባው ሰው ጃዋርን ለመኮነን እና ለመለየት ከነዚህ ስህተቶች አንድኛው ብቻ በቂ ነበር። ሆኖም ከልጅነት እና ከእልክ የመጣ ስህተት ይሆናል፣ ልጁ ነገ ጧት ከስህተቱ ተጸጽቶ መንገዱን እየመረመረና እያሻሻለ ሊመጣ ይችላል፤ ይህን ልጅ ብናቀርበውና በትክክለኛው መንገድ መሄድ ቢችል በዕውቀቱ አገሩንና ወገኑን ሊያገለግል ይችላል..  በሚል እሳቤ አንዴና ሁለቴ  አልፈነዋል። ይህን ለፍቅርና አብሮ ለመኖር እንደተሰጠ ዕድል ስላየሁት ምንም አልመሰለኝም ነበር። እሱ ግን ከስህተቱ ሊመለስ አልቻለም። በተቃራኒው ጭራሽ እየባሰበት መጣ። ጃዋር  እየሄደበት ያለው መንገድ፤ ከኢትዮጵያዊነት ጋር ያለውን ርቀት አንዴ ብቻ ሳይሆን በተደጋጋሚ ዓየን።  የጃዋር ችግር ከግለሰቦችና ከፓርቲዎች ጋር ቢሆን የፈለገውን ያህል ዘመን ቢወስድ መታገሱና ማባባሉ ሊያስኬድ ይችል ነበር። ጃዋር ደጋግሞ እየወጋ ያለው ግን ኢትዮጵያዊነትን ነው። መንገዱ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ለማፈራረስ ነው። ምንም ለማያውቁ ታዳጊ ህፃናት የፈጠራ ድርሰት እየተረከ ትውልድ እየለያየ ነው። አገር በጥላቻ እንዲናጥ እያደረገ ነው።
ያደቆነ ሰይጣን ሳያቀስስ አይመለስም እንዲሉ፤ ጽንፈኛው ጃዋር በአሁኑ ወቅት ከህወሀቶች ጋር በመሆን የዓፄ ምኒልክን ምስል ከሂትለር ጋር መሳ ለመሳ እያደረገ መበተን የደረሰበት ደረጃ ላይ ደርሷል። የማንነታችን (የኢትዮጵያዊነታችን) መሰረት፤ ማላገጫና መቀለጃ  መቀለጃ ሆኗል። በበኩሌ ከዚህ በላይ በኢትዮጵያዊነት ላይ መሳለቅ ያለ አይመስለኝም። ለምን ምኒልክ ተነኩ አይደለም እያልኩ ያለሁት። ህወሀቶችም ምኒልክን ለዓመታት ሲከሱ ሰምተናል። ደግሞም ምኒልክ ይህን ፈፅሟል፣ ይህን አድርጓል.. የሚለው ክስና ወቀሳ አግባብ ያለውና ለውይይት በር የሚከፍት  ስለሆነ ችግር የለውም። ጃዋርና ተከታዮቹ ግን  ወደ አደገኛ ጽንፍ በመሄድ “ምኒልክ ሂትለር ነው” የሚል  ጸያፍ፣ ርካሽና ጨርሶ ለውይይት የማይጋብዝ ቅስቀሳ ነው እያደረጉ ያሉት።  ጃዋር በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ይህን ሲያደርግ ኢትዮጵያዊነትን፣ነፃነትን፣ ማንነትን፣ እየናደና እያፈረሰ ነው ለማለት ነው የፈለግኩት። ስለሆነም ከሰፊውና ኢትዮጵያዊነቱን ለአፍታም ተጠራጥሮ ከማያውቀው ከወንድማችን የአሮሞ ህዝብ ጋር  በፍቅርና በአንድነት መኖራችን ይቀጥላል፡፡ ወይም በግልጽ ለመናገር ያህል እኛ በኢትዮጵያዊነታችን ቅንጣት ጥርጥር የሌለን ኦሮሞዎች ከወንድሞቻችን ጋር በኢትዮጵያዊነት ጥላ ስር በፍቅርና በአንድነት መኖራችንን እንቀጥላለን። አገር ለማፍረስና ለመገንጠል እንዲሁም በብሔረሰቦችና በሀይማኖቶች መካከል ጥላቻና ልዩነትን ለመፍጠር ተግተው እየትቀሳቀሱ ካሉት  ከጽንፈኞቹ ከነ ጃዋር ጋር  ግን ልዩነታችን ሰፍቷልና በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ልንታገላቸው ይገባል። ከወያኔ ጋር የሚደረገው ትግል፤ ልጆቹንና ጉዳይ ፈፃሚዎቹን እነ ጃዋርን ሊያጠቃልል ይገባል። አውቀውም ይሁን ሳያውቁት በወሳኝ ሰዓት የኢትዮጵያውያንን ትግልን በማደናቀፍ የወያኔን ዕድሜ የማስቀጠል ተልዕኮ እየፈጸሙ ያሉትን እነ ጃዋርን በቸልታ ልናያቸው አይገባም።
****
ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከላይ በጠቀስኳቸው ባለፉት  ሂደቶች እኔን ከጃዋር በላይ ሲገርመኝና ሲያበሳጨኝ የቆየው ታዲያ “ኢትዮጵያ አገሬ”  እያሉ ነጋ ጠባ የሚፎክሩ ሰዎች  ተግባር ነው።በተለይ አንዳንድ “አክቲቪስት” ነን የሚሉና ነፋሱ ወደነፈሰብት እየጋለቡ የሚያራግቡ  አጨብጫቢዎች፣ ነፃ ለመውጣት የምናደርገውን ትግል በመጎተትም ሆነ አገርን በማፍረስ እየተደረገ ባለው ሴራ ከጃዋር በላይ ተጠያቂ መሆናቸውን ሊያውቁት ይገባል። (ስማቸውን ያልጠቀስኳቸው ሁላችሁም ታውቋቸዋላችሁ ብዬ ነው HL & BT) ነው። ያልገባኝ ነገር  እነኚህ አክቲቪስት ተብየዎች አገር ለመገንጠል እየተጋ ካለ ጽንፈኛ ጋር የሚታከኩት ምን ትርፍ ለማግኘት ነው የሚለው ነው…  የሀገር ጉዳይ የምንሞዳሞድበት እና የምናመቻምቸው ጉዳይ አይደለም። በኢትዮጵያ ጉዳይ ቁማር መቆመርና እከከኝ-ልከክህ መጫዎት አይቻልም። ከፈለጉ ምርጫቸውን አስተካክለው ከጽንፈኛው ከጃዋር ካምፕ ይቀላቀሉ። ያ ካልተመቻቸው ደግሞ በኢትዮጵያ ባንዲራ ስም መነገዳችውን ያቁሙ።
የሀገር ጉዳይ የዕውቀት ስታንዳርድ እያወጣን  የምንሞጋገስበት፣ የምንኮፋፈስበት እና በፌስ ቡክ የምንጫዎትበት አይደለም።

በ”ዲሞክራሲና ሁለንተናዊ ልማት በኢትዮጵያ”ና በሁለት ተጨማሪ መጽሀፎች ላይ የቀረበ አጭር አስተያየት

December 31, 2013
ፋሲል የኔዓለም
በፖለቲካው ዓለም ጉልህ ስፍራ ያላቸው ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ “ዲሞክራሲና ሁለንተናዊ ልማት በኢትዮጵያ” በሚል ርዕስ የጻፉትን አዲስ መጽሃፍ ያነበብኩት ዘግይቼ ነው ፤ ለመዘግየቴ ሶስት መሰራታዊ ምክንያቶች ነበሩኝ፣ አንዱና ዋናው ዶ/ሩ በተለያዩ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን አመለካከት በመገናኛ ብዙሃን በስፋት ስላቀረቡ በመጽሀፉ ውስጥ እምብዛም አዲስ ነገር ያቀርባሉ የሚል እምነት ስላልነበረኝ ነው። ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ ዶ/ሩ ራሳቸው በከፊል የጠቀሱት ነው፣ “ በአገሪቱ ለዲሞክራሲያዊ ስርዓት የሚደረገው ትግል ውስጥ ጉልህ ሚና እየተጫወተ ያለ የተቃዋሚ ድርጅት አመራር አባል መሆኑን ሲመለከት፣ ከቅንጦትም ባሻገር በተወሰነ ደረጃ “ የስራ ፈትነት” ወይንም የበለጠ ጠርጣራ ( cynic) ለሆነ ሰው “ በተግባር ስራ ለመስራት ካለመቻል “ የመጣ፤ ተግባራዊ ድክመትን ለመሸፈን የሚደረግ ሙከራ ሊመስል ይችላል” የሚለው ነው። ሶስተኛው ምክንያቴ ደግሞ ፣ ፋሽን በሚመስል መልኩ በአገር ቤት የሚኖሩ ፖለቲከኞች በተከታታይ መጽሃፎችን በማሳተማቸው ለእነሱ ቅድሚያ ለመስጠት በመፈለግ ነው።Ethiopian books review
ዶ/ር ብርሃኑን ያነበብኩት ሁለቱ ታዋቂ ፖለቲከኞች፣ ዶ/ር መረራ ጉዲና “የኢትዮጵያ ፖለቲካ ምስቅልቅል ጉዞና የሕይወቴ ትዝታዎች -ከኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ እስከ ኢህአዴግ” እንዲሁም ኢ/ር ሃይሉ ሻውል “ ሕይወቴ እና የፖለቲካ እርምጃዬ” በሚሉ ርዕሶች ያሳተሙዋቸውን መጽሃፎች ካነበብኩ በሁዋላ በመሆኑ፣ በሶስቱም ስራዎች ላይ መጠነኛ ንጽጽር ለማድረግ አስችሎኛል።
ዶ/ር መረራ ከተማሪዎች እንቅስቃሴ እስከ ዛሬ ያለውን የአገራችንን ፖለቲካ ግሩም በሆነ መንገድ አቅርበዋል፤ መጽሃፉ ብዙ አስቂኝ ገጠመኞች የተካተቱበት በመሆኑ ፣ በቋንቋና በዓርትዖት በኩል የሚታይበትን ጉልህ ችግር አይተን እንዳላየን እንድናልፈው ያስገድደናል። መጽሀፉ በጥሩ ዓርታዒ እንደገና ቢታረምና ቢታተም “ የተዋጣላቸው” ከሚባሉት የአገራችን መጽሀፎች ተርታ የመመደቡ እድል ከፍተኛ ነው። ዶ/ር መረራ የአገራችንን ህልውና እየተፈታተነ የመጣውን፣ በ1960ዎቹ ተዘርቶ በእነ አቶ መለስ ዜናዊ አገዛዝ ተኮትኮቶ ያደገውን የብሄር ፖለቲካ መነሻ ፣ ያመጣውን ግሳንግስ እና የግሳንግሱን ማራገፊያ መፍትሄ አስቀምጠዋል። መፍትሄ ብለው ያስቀመጡትም በመጽሀፉ የመጨረሻ ገጽ እንደሚከተለው ሰፍሯል፣ “ …ለታሪክም ለህዝብም አስቀምጬ (ማለፍ) የምፈልገው መሰረታዊ ነጥብ ፣ አብዛኛው የትግራይ ሊሂቃን “ ስልጣን ወይም ሞት” ብሎ ስልጣን ላይ የሙጥኝ እስካለ ድረስ ፣ አብዛኛው የአማራ ሊህቃን በአጼዎች ዘመን የነበረውን የበላይነትን መልሼ አገኛለሁ ብሎ የሚገፋውን የሕልም ፖለቲካ እስካልተወ ድረስ፣ ብዙሃኑ የኦሮሞ ሊህቃን ኦሮሚያን ለብቻ የማውጣቱን ሕልም እስካልተወ ድረስ ሀገራችን ከአደጋ ቀጠና የምትወጣ አይመስለኝም። በሌላ ቋንቋ ለነዚህ መሰረታዊ በሽታዎቻችን መድሃኒት እስካላገኘን ድረስ ኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምም ሆነ ዲሞክራሲያዊ አስተዳደርን ፈጽሞ የምታገኝ አይመስለኝም።” ( ገጽ 264)። ምንም እንኳ “አብዛኛው” የሚለው ቃል አወዛጋቢ ሊሆን እንደሚችል ቢሰማኝም ፣ ዶ/ሩ ያቀረቡት የመፍትሄ ሃሳብ በትኩረት ሊታይ እንደሚገባው ሳላስታውስ አላልፍም፤ በተለይ” እነዚህ የሶስቱ ብሄሮች ሊህቃን ህልማቸውን እንዲተው ማድረግ የሚቻለው እንዴት ነው?” የሚለው ጥያቄ ለእኔ ቁልፍ ይመስለኛል። ዶ/ር መረራ በዚህ ዙሪያ የተብራራ መልስ ቢሰጡ ኖሮ መጽሃፋቸውን የበለጠ ሙሉ ማደረግ ይችሉ ነበር እላለሁ።
የኢንጂነር ሃይሉ መጽሀፍ የአገራችንን የፖለቲካ ችግር ከግለሰቦች ባህሪ ጋይ ያያዘው በመሆኑ ብዙም ክብደት የሚሰጠው ሆኖ አላገኘሁትም፤ ንድፈሃሳባዊ ትንተናዎች ይጎድሉታል፣ የተዓማኒነት ችግሮችም አሉበት( በተለይ ከቅንጅት መሪዎች ጋር ስለነበረው የሽምግልና ሂደትና ከዚያ በሁዋላ ስለተፈጠሩት ኩነቶች) ፤ ለተተኪው ትውልድ የሚሰጠው ትምህርት ስለመኖሩም በእጅጉ እጠራጠራለሁ፤ በእርግጥ ኢ/ር ሃይሉ ብዙ ውጣውረዶችን አልፈው እስካሁን በህይወት ለመቆየት መቻላቸው እድለኛ ሰው እንደሆኑ በመጽሃፋ ለማየት ችለናል፣ አገራቸውን የሚወዱ ሰው መሆናቸውንም አስገንዝቦናል። ኢ/ር ሃይሉ የዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳን መንገድ በመከተል መጽሀፉን በሌላ ሰው በማስጻፋቸው ስለጸሃፊነት ችሎታቸው አስተያየት ለመስጠት አያስችልም ።
የዶ/ር ብርሀኑ “ዲሞክራሲና ሁለንተናዊ ልማት በኢትዮጵያ” የሚለው ርዕስ ዘጊ ወይም ለማንበብ የማይጋብዝ ነው፤ በትምህርቱ አለም የዘለቁና የጥናትና ምርምር ወረቀቶችን ለማንበብ ፍላጎት ያላቸው ምሁራን ካልሆኑ በስተቀር፣ እንደ እኔ አይነቱ ተራ አንባቢ በርዕሱ ማልሎ መጽሀፉን ለማንበብ ስለመነሳሳቱ እጠራጠራለሁ። መጽሀፉ ውጫዊ ገጽታው ባያማልልም ውስጣዊ ይዘቱ ግን ድንቅ ነው። እንደምንም የጀመርኩትን መጽሀፍ እየተጨነቁና እየፈራሁ፣ እያዘንኩና ከራሴ ጋር እየተሟገትኩ፣ እግረ-መንገዴንም የጸፊውን እይታ፣ የትንታኔ እና የቋንቋ አጠቃቀም ችሎታ እያደነቁኩ ጨርሸዋለሁ። መጽሀፉን እንደጨረስኩ የተናደድኩበት ነገር ቢኖር ጻሃፊው የኢትዮጵያን ችግሮች እንዲያ አድርገው ካቀረቡ በሁዋላ መፍትሄውን በይደር በመተዋቸው ነው።
ከዚህ ቀደም የአገራችንን ሁለተናዊ ችግሮች ማለትም የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የተፈጥሮና የህዝብ ብዛትን በአንድነት አጣምሮ፣ በአገራችን ህልውና ላይ የደቀኑትን ፈተናዎች ቅልብጭ አድርጎ ያሳየ ከገብረህይወት ባይከዳኝ “መንግስትና የህዝብ አስተዳደር” በሁዋላ የተጻፈ መጽሀፍ ስለመኖሩ እጠራጠራለሁ፤ ይህን ስል ሌሎች ድንቅ የፖለቲካ መጽሃፎች አልተጻፉም እያልኩ አይደለም፤ የዶ/ር ብርሃኑን መጽሀፍ ለየት የሚያደርገው የተለያዩ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ችግሮችን ለይተው በማውጣት እርስበርስ ያላቸውን ትስስር ከግሩም ትንተና ጋር ሁሉም ሊረዳውና ሊጠቀምበት በሚችለው መንገድ ማቅረባቸው ነው ። (የምጣኔ ሀብት ትምህርት ( economics) የማይገባው ሰው እንኳ ቢሆን፣ መጽሀፉን አንብቦ ስለአገራችን ኢኮኖሚ ለመረዳት አይሳነውም።) መጽሃፉ የባራክ ኦባማን The Audacity of Hope እንዳስታወሰኝ ብገልጽ ያጋነንኩ አይመስለኝም፣ አጋነኸዋል የምትሉኝ ካላችሁም ” አንብቡትና ሞግቱኝ።
የዚህ መጽሀፍ ትልቁ መልእክት፣ ለእኔ እንደገባኝ፣ “የአገራችን ችግር ዲሞክራሲያዊ ስርዓትን በመገንባት ይፈታል” የሚለው አስተሳሰብ እንደሚታሰበው ቀላል አለመሆኑንና ከአሁኑ መፍትሄ ካልተበጀለት በሁዋላ ላይ ይዞት የሚመጣው ችግር ቀላል አለመሆኑን ማሳየት ነው ። የብሄር ፖለቲካው በዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ላይ የሚኖረው ተጽእኖ፣ በአገራችን ልማትን ለማምጣት የሚገጥሙ ፖለቲካዊና መዋቅራዊ ችግሮች፣ ከአካባቢ ውድመትና ከህዝብ ብዛት ጋር ተያይዞ በመጽሀፉ በዝርዝር ቀርቧል። በአሁኑ ጊዜ በአገራችን እየታየ ያለውን የገቢ አለመመጣጠንም 1500 ብር የሚያወጣውን የአንድ መለኪያ ውስኪ ግብዣ በምሳሌነት በማንሳት በደቡብ አፍሪካ እንደታየው በአገራችንም ለወደፊቱ ይዞ ሊመጣ የሚችለውን ጣጣ ጸሀፊው በደንብ አሳይተውናል።
መጽሀፉ የውጩ ፖለቲካ በአገራችን ፖለቲካ ላይ የሚያሳርፈውን ተጽዕኖ እንዲሁም የአለማቀፉ የንግድ ስርዓት በኢትዮጵያ እድገት ላይ ያለውን ተጽእኖ ቢያካትት ኖሮ የበለጠ ድንቅ ይሆን እንደነበር አስባለሁ ። ከዚያ በተረፈ ግን መፍትሄዎቹ በሌላ ክፍል እንደሚቀርቡ መገለጹ በመጽሀፉ ላይ በቂ ክርክር እንዳይነሳ ያደረገው ይመስለኛል። በመጽሀፉ በቀረቡት ችግሮች እና ትንተናዎች ላይ ተቃውሞ የሚኖረው ሰው ይኖራል ብየ አላስብም፣ ተቃውሞ የሚነሳው ችግሮችን ለመፍታት በሚቀርቡት የመፍትሄ ሀሳቦች ላይ እንደሚሆን በመገመት ቀጣዩ መጽሃፍ አወያይ ( አካራካሪ) ይሆናል እላለሁ።
ስለአገራቸው እንቅልፍ አጥተው የሚያድሩ ሁሉ መጽሀፉን እንዲያነቡት እመክራለሁ ( የዶ/ር መረራንም ጨምሮ)። በተለይ በሰላማዊው የትግል ሜዳ ለመፋለም የሚያስቡ ጀማሪም ሆኑ ነባር ፖለቲከኞች የብርሀኑን መጽሀፍ በማንበብና በምርጫ ክርክር ወቅት ይዞ በመቅረብ ( የመፍትሄው መጽሀፍ ቶሎ እንደሚደረስ በመገመት) ምርጫውን ሊያሸንፉ እንደሚችሉ አልጠራጠርም፤ ስልጣኑን ይረከባሉ ብዬ ባላስብም።

Sunday 29 December 2013

ዛሬ አረና/መድረክ በሽሬ የሚያደርገው ስብሰባ ጉዳይ… (ከትግራይ)

(ኢ.ኤም.ኤፍ) በዛሬው እለት የአረና/መድረክ ፓርቲ በሽሬ እንዳስላሴ ከተማ ስብሰባ ለማድረግ ፈቃድ አግኝቶ፤ ይህንኑ ህዝባዊ ስብሰባ ያደርጋል ተብሎ እየተጠበቀ ነው። ሆኖም በስፍራው የሚገኘው የድርጅቱ ህዝብ ግንኙነት፤ አብርሃ ደስታ እንደዘገበው… ስብሰባው ከመጀመሩ በፊት የህወሃት አባላት መግቢያው በር ላይ ግርግር እየፈጠሩ ናቸው። እንዲህ በማለት ይቀጥላል። “ህዝባዊ ስብሰባውን ለመጀመር አዳራሹ ሲከፈት ህዝብ በስብሰባው ለመሳተፍ መግባት ሲጀምር አስተዳዳሪዎቹ ደንግጠው ‘በስብሰባው መሳተፍ የሚችለው የቀበሌ መታወቅያ ያለው ሰው’ ብቻ መሆን እንዳለበት አወጁ። ይህ ብቻም አይደለም፤ መታወቂያውን እየመዘገቡ ለማስገባት ወሰኑ። ህዝቡ ተቃወመ። የዓረና አመራር አባላትም ድርጊቱ ተቃወሙ። መታወቂያ የሌለው እንዳይገባ ስለተወሰነ ብዙ ሰው ተቃውሞ ስላነሳና መግባት ስለፈለገ የአዳራሹ መግብያ በር ተዘጋ። አሁን የተፈቀደልን አዳራሽ ዝግ ነው። ዓረና ስብሰባው በአዳራሹ በር ባለው ሜዳ ለማካሄድ ወስኗል። ባደራሹ በር አከባቢ ብዙ ህዝብ አለ። ካድሬዎቹ ህዝቡን ለመበተን እየፈተኑ ነው። (ኢ.ኤም.ኤፍ ሁኔታውን እየተከታተለ ማቅረቡን ይቀጥላል)

እኔ ኣላውቅም ፈራሁ ጁሃር (ሄኖክ የሺጥላ )

የበደሌ ቢራ ፋብሪካ ከ ኣዲስ ኣበባ 483 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ኢሉ-ኣባ-ቦራ ( Eloo The father of Holstein Friesian) ኢልባቡር ከተማ በሁለት መቶ ሃምሳ ሺ ስኩውር ሜትር ይዞታ ላይ ስራውን እንደ ኣውሮጳውያን ኣቆጣጠር በ 1993 ማከናወን የጀመረ ትልቅ የቢራ ማምረቻ ድርጅት ነው።
ኢሊባቡር መልካም ምድራዊ ኣቀማመጡም ሆነ ምድራዊ ልምላሜው፥ እንደ በቆሎ ፤ ገብስ፤ ጤፍ፤ የቅባት እሎች፤ ማር፤ ከነ ቦራ ደሞ ወተት፤ ቅቤ እና ወዘተ የሚዘራባት፤ የሚታጨድባት፤ የሚቆረጥባት፤ የሚታለብባት ሃገር እንድትሆን ኣድርጉዋታል።
ኢሊባቡርን የጽሁፌ መንደርደሪያ ኣደረኩ እንጂ ዋናው ነጥቤ እሱ ኣይደለም። ዛሬ መናገ ወይም መጻፍ የፈለኩት ቴዲ ኣፍሮ በቅርቡ በመላው ኢትዮጵያ የሙዚቃ ዝግጅቱን እንዲያሳይ ወኪል የሆነውን የበደሌ ቢራን ያለመጠጣት ኣድማ ( boycotting) በመላው ኢትዮጵያ ይደረግ ዘንድ ኣንዳንድ ግለሰቦች የጀመሩትን ነገር ሰምቼ፤ ለምን በደሌን፤ ለምን ቴድን የሚል ጥያቄ ለሚጠይቁ፤ መልስ የሚመስለኝን ለመተየብ፤ ከተቻለም ለማሳየት መመኮር በመሻቴ ነው ።
ቴዲ ኣፍሮ በቅርቡ በ ጋዜጣ ላይ ስለ ኣድዋ ድል በሰጠው ኣስተያየት የተቆጡ፤ የተቀየሙ ግለሰቦች፤ ቴዲ ኣፍሮ ጥቁር ሰው ብሎ ንጉስ ሚኒሊክን፤ ከዛም በላይ የኣድዋ ድልን በመዘከሩ የተበሳጩ የህብረተሰብ ኣካሎች፤ ቴዲ ኣፍሮ ከዚህ ቀደም ጃ ያስተሰርያል ብሎ በመዝፈኑ ቂም የቁዋጠሩ ሰዎች፤ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በሊግ ኦፍ ኔሽን በ 1936 የኢጣልያንን የተለከለ የኬሚካል መሳሪያ መጠቀምን በመቃወማቸው፤ ኢትዮጵያን የ ዩናትድ ኔሽን ኣባል በማድረጋቸው፤ ቅራኔዎችን ኣብርደው ያፍሪካን ህብረት በመመስረታቸው፤ ለነዚህ ጉልህ ኣስተዋጾዎቻቸው በመዝፈኑ፤ ለነዚህ ለተጠቀሱት መልካም ስራቸው መታሰቢያ የጭንቅላቱ ውጤት የሆነውን ምዚቃ በማበርከቱ፤ ቴዲ ኣፍሮ ፤ ኣቀንቃኝ ና ኣዝማሪ ፤ ገጣሚና ሰኣሊ፤ ሃያሲና ደራሲ፤ ጸሃፊ ተውኔቱና ብላታው፤ ኣፉን በለጎመበት ዘመን፤ በብእሩ የታሪክ ጋሻ፤ በግጥሙ ለቆሰለ ታሪክ ማገገሚያ፤ በዘፈኖቹ ( ከ ማሊ ሱፊዎች ባልተናነሰ መልኩ) የነብስን ክር እየተጫነ ያላስለቀሰው፤ ያላስተከዘው፤ ሰው እንደሌለ የገባቸው ሰዎች፤ በይበልጥም የኣድዋ ድል፤ የጥቁር ኣንበሳዎች ድል መሆኑን ያሳየበት በመሆኑ እና ይህም የሚያማቸው ሰዎች፤ ዛሬ በደሌ ቢራ ቴዲ ኣፍሮን ስፖንሰር ስላደረገ፤ በደሌ ቢራን ያለመጠጣት ኣድማ ጠርተዋል። ኣሁን ቴዲ ኣፍሮን ኣብዶ በረንዳ ( የጫት ማከፋፈያ በረንዳ ነው) ቢሆን ስፖንሰር ያረገው ምን ሊሉ ነበር።። ባረገው እና የተከታዮቻቸውን መልስ ባየን። ኣንድ ጊዜ ቆይ ጠብቁኝ ሳቄ መጣብኝ ያለው ተናጋሪ ማን ነበር።
ኣዲሱ የቴዲ ኣፍሮ ኣልበም ( ጥቁር ሰው) የብዙዎቹን እትዮጵያዊያኖች ድምጽ ያስገኘለትን ያህል፤ ንጉስ ሚኒሊክ በድሎናል፤ ጡታችንን ቆርጦዋል፤ ወዘተ ወዘተርፈ ለሚሉት ደሞ፤ ከሚኒሊክ መፈጠር፤ ከታሪክ ኣንቅጽነቱና ኣኩሪ ገድሉ ጋር የጀመሩትን እጹብ ጸብ ውሃ የሚደፋበት በመሆኑ፤ ጠላት ሊያፈራበት እንደሚችል መገመት ብዙም ኣይዳግትም። እናም ‘ነዚህ ሰዎች ቀደም ብዬ እንደ ጠቀስኩት፤ በደሌ ቢራን ያለመጠጣት ኣድማ እናድርግ እያሉ ነው። ልክ ናቸው፤ ህዝብ በጥላቻም በቢራም ሰክሮ እንዴት ይሆናል፤ ባንዱ ብቻ ይበቃልና።
በነገራችን ላይ ይህንን ኣድማ ለማስመታት ከሚራወጡት እና ከሚሯሯጡት ሰዎች መሃከል ኣንዱ ጁሃር መሀመድ መሆኑን ሰምቼ ኣፍሬ ጥፍሬ ውስጥ ልገባ ነበር። ባንድ ወቅት ይሄ ወጣት ፖለቲከኛ ስለ ራሱ ሲናገር “እኔ እናቴ መንዜና የኦርቶዶክስ ክርስቲያን ነች ኣባቴ ደሞ ኦሮሞና ሙስሊም ነው ፤ ታዲያ ከኔ በላይ ኢትፖጵያዊነትን የሚወክል ምንነት ኣለ ወይ” ብሎ ነበር። መልሱ ሊሆን ይሚችለው ጁሃርዬ በውነትም የለም፤ እንዳንተው ኣቶ መለስም እኮ የተላቀቀ ነገርን ማጣበቅ የሚችል (ኡሁ የሆነ) (UHU…glue) ደም ነበራቸው፤ ግን ደሙ ሳይሆን የደሙ ባህሪ ነው ወሳኙ ነገር። የተሸከምነው ደም ሳይሆን በውስጣችን ያፋፋነው ስብዕና ነው ማንነት ፤ ማንነት ስራ ነው እንጂ ኣንተ እንዳልከው የ-ኢ-ተጎራባች ዘር ደም ውህደት (ኬሚስትሪ ውጤት ኣይደለም)፤ ክርስቶስ ( ኤሳው… ኣለይሁ ሰላም) በ-በረት ተወለደ ብለን እናምናለን፤ ግን እንደ ሰብኣዊ ፍጡር በ-በረት መወለዱ ሳይሆን ሰው ሆኖ ሲኖር ያደረገውን ነገር ነው የምናስበው፤ ስለ ነብዩ ሙሃመድ (ሰ.አ.ወ) ኣንድ ሙስሊም ሲያስብ ስለ ዘራቸው ሳይሆን ስለ ስራቸው ነው የሚያስበው ብዬ ኣስባለሁ ። ባንድ ወቅት ይሄው ሰው፤ ፹ ከ ፻ የሚሆነው የሃገሬ እስላም ኦሮሞ ነው፤ እናም የእሮሞ ህዝብን ኢምፓወር ማድረግ፤ እስልምናን ኢምፓወር እንደማረግ ነው ኣለን፤ ለመስማት ኣይደል የተፈጠርነው እናም ሰማነው፤ ባሜጃ ኣለን ዝም ብለን ሰማነው፤ ቀጥሎም ኢትዮጵያ ኣውቶ ኦፍ ኦሮሚያ ኣለን እሱንም ሰማነው። በነገራችን ላይ ኢትዮጵያ ኣውት ኣፍ ኦሮሚያን ወደ ፈርንጅኛ ስቀዳው ( the child give birth of her mother) ኣይመስላችሁም ? ለመተርጎም የተገደድኩት የመጀመሪያው ራሱ እንግሊዘኛ መሆኑን ስለ- ተጠራጠርኩ ነው። ለነገሩ ስታንፈርድና ኮሎምቢያ ዩንቨርስቲ እኮ መፈክር ኣያስተምሩም።
እና ዛሬ በደሌ መጣ እና ወንድሜ ጁሃር ሰማኒያ ከመቶ ካለው ሃሳብ ጋ ግንባር ለግንባር ተጋጨ ( head on collusion) እናም ሁለት የሚጋጩ ነገሮችን እንግዲህ እናስተውላልን።
፩) መቼም ፹ ከመቶው እስላም ኦሮሞ ነው ብለኽን፤ ኣንተም በዘር ብቻ ሳይሆን በእምነትም ጭምር ጠበኽ፤ ኣልገባኝም ታዲያ እንዴት ነው፤ እነማን ቦይ ኮት እንዲያረጉልኽ ነው ጥሪውን ያቀረብከው፤ ፳ ፐርሰንቱ እስላም ያልሆነው ኦሮሞ ? ደሞ ከ ፹ ከመቶ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ውስጥም ቢሆን ኣዲስ የበደሌ ኣድመናኛ ማግኘት ይቸግራል ብዬ ኣስባለሁ፤ ምክኒያቱም እነሱ ላንተ ሲሉ ሳይሆኑ ለዲናቸው ሲሉ ድሮም እንዲህ ኣይነቱን ነገር ይነኩት ነበር ብዬ ኣላስብም፤ በፍጽም ኣያደርጉትም፤ ታዲያ የማይጠጡ ሰዎችን ነው ኣድማ የጠራነው፤ ወይስ ሙሉ የኢትዮጵያዊነት ማሳያ ምሳሌ እንድትሆን ያደረገችህ የመንዜዋ እናትህን ዘመዶች፤ እኔ ኣላውቅም ፈራሁ ሄኖክ ነው ያለኝ የልጅነት ጉዋደኛዬ፤ ባንድ ትልቅ የውሃ ጉድጉዋድ ውስጥ እንሹለክ ስለው። እኔ ኣላውቅም ፈራሁ ጁሃር።
ዛሬ ጀርመን ያላትን ቅርጽ እንድትጠብቅ ወይም እንዲኖራት ያደረገው ኦቶ ቮን ቢስ ማርክ፤ የደም ትግል ውጤት ነው። ታዲያ ጀርመኖች በ ቢስ ማርክ ተናደው ፒሊሲነርን ( የጀርመን ታዋቂ ቢራ ነው) ቦይ ኮት እናርግ ኣላሉሉም። በፈረንሳይ እንዲህ የሚባል ታሪክ ኣለ፤ በኣሜሪካም፤ ኣረ ሆመር በጥንታዊያኖቹ የግሪክ ዘመን ስለነበረው ጦርነትም ጽፎዋል፤ ስለ ስርኣቱ፤ ስለ ኣገማምኖን እና የወንድሙ መንግስት፤ ስለ ሄለናዊው ስርኣት፤ ከዚያም በሁዋላ እነ ዳንቴ ስለ ጻፉት ስለ ዲቫይን ኮሜዲ፤ ፍሬድሪክ ዊልሃልም ኒቺ ስለተራቀቀበት የማህበረሰብ ስነ ልቦና፤ እነ ኣልበርት ካሙ ስለጻፉለት የፈረንሳይ ማህበረስብ እና በየስራቶቹ ውስጥ ስለ ነበርው ፍዳ፤ እነ ልዮ ቶሎስቶይ በሰላ ብእራቸው ስለዘገቡት የሩሲያ የጭቆና ቦለቲካ፤ እነ ፓብሎ ፒካሶ ጉሬንሽያ ብለው ስለገለጹት የስፔን ከተማ ስለ ስንቱ ለዚህ ለወጣቱ ፖለቲከኛ እንንገረው እስኪ ባክህ ጁሃርዬ ገረፍ ገረፍ ኣርጋቸው (በቃ እንደውም ለዚህ ክረምት ለፐርሰናል ዲቨሎፕመንት…ትመለከታቸው ዘንድ እጠይቅ፤ሃለሁ (ማሳሰቢያ በኣብዛኛው በኣማራ ጻሀፊ ኣይደልም የተጻፉት ቢሆኑም ደሞ ኣነተ ኣምሳ ፐርሰንት ኣማራ ኣይደለህ እንዴ፤ የምሬን እኮ ነው)
በታሪክ ላይ ጥላሸት መቀባት በፍጹም ለማንም ኣይሳካም፤ ወደድንም ጠላንም፤ ጠቅልለን የምንጎርሰውን እንጀራ የፈጠሩት ኣባቶቻችን ናቸው፤ ለሆዳችን ያለን ቅርበት ለታሪካችንም ይኑረን። ቴዲ እንዳለው ክፉውን በክፉ ለመመለስ ማሰብ ሌላ ክፉነት ነው። ሁለቱ ደሞች እንደ ደም ይሰሩ፤ ያስቡ ዘንድ ሰው እንሁን።

በደቡብ ሱዳን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን መንግስት እንዲታደጋቸው እየተማጸኑ ነው

ዩኒቲ በሚባለው ግዛት ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያን በጦርነት አጣብቂኝ ውስጥ መገኘታቸውንና ህይወታቸው አደጋ ውስጥ መውደቁን ተናግረዋል።
በግዛቱ ውስጥ በአንድ የመንገድ ስራ ድርጅት ውስጥ ተቀጥረው የሚሰሩ 6 ኢትዮጵያውያን እንደተናገሩት በሁለቱ ተፋላሚ ሀይሎች መካከል የሚደረገውን የተኩስ ልውውጥ ለማምለጥ ያለፉትን ሁለት ቀናት በከባድ ማሽነሪዎች ውስጥ በመደበቅ ለማሳለፍ ተገደዋል። በአካባቢያቸው 2 ኢትዮጵያውያን መገደላቸውንና 3ቱ ደግሞ መቁሰላቸውን ተናግረዋል።
እስካሁን ድረስ ምን ያክል ኢትዮጵያውያን እንደሞቱ ባይታወቅም፣ የአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ በአገሪቱ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን በማነጋገር እንደዘገበው የሞቱ ኢትዮጵያውያን ቁጥር እስከ ታህሳስ 17፣ 2006 ዓም ድረስ ቢያንስ 30 ይደርሳል።
ኢሳት ያነጋገራቸው ኢትዮጵያውያን እንደሚሉት መንግስት እስካሁን ድረስ ዜጎቹን ለመሰብሰብ ጥረት እያደረገ አይደለም። ጎረቤት አገሮች ኬንያና ኡጋንዳ ዜጎቻቸውን ሲያስወጡ የኢትዮጵያ መንግስት ምንም አይነት እርምጃ ለመውሰድ አለመፈለጉ ለብዙዎች እንቆቅልሽ ሆኗል። ኢትዮጵያውያን አሁንም መንግስት እንዲደርስላቸው ጥሪ አቅርበዋል
በጆንግሌ ግዛት የተደፈሩ 4 ኢትዮጵያውያን ጁባ ውስጥ በሚገኘው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሆስፒታል ውስጥ ህክምና እንዲያገኙ ተድርጓል።x
ይህ በእንዲህ እንዳለ የምስራቅ አፍሪካ መንግስታት በናይሮቢ ኬንያ ያደረጉትን ስብሰባ ተከትሎ የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር በግላቸው ተኩስ እንደሚያቆሙ አስታውቀዋል። አገራቱ የመንግስትን እርምጃ የደገፉ ሲሆን፣ የኬንያው መሪ ኡሁሩ ኬንያታ በዲሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠን መሪ በሀይል ለማውረድ የሚደረገውን እንቅስቃሴ እንደማይደግፉ ገልጸዋል።
የተቃዋሚዎች መሪ የሆኑት ሪክ ማቻርም በተመሳሳይ መንገድ ተኩስ እንዲያቆሙ የምስራቅ አፍሪካ መሪዎች ተማጽኖ አሰምተዋል። መሪዎቹ በሚቀጥሉት 4 ቀናት ፊት ለፊት ተገናኝተው እንዲወያዩ ኢጋድ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል።እስካሁን በተካሄደው የእርስ በርስ ጦርነት ከ1 ሺ በላይ ሰዎች መገደላቸውን አለማቀፍ የመገናኛ ብዙሀን ዘግበዋል;፡

በሳውድ አረቢያ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽህፈት ቤት ውስጥ ዘረኝነትና ሙስና ተስፋፍቷል ተባለ

-ኢሳት ከቆንስላው ባገኘው የውስጥ መረጃ በሃላፊነት ላይ የተመደቡት አምስቱ ዲፕሎማቶች በዘረኝነትና በሙስና ከመዘፈቃቸው ም በተጨማሪ ሊሴ ፓሴ ለማውጣት ወደ ቆንስላው የሚደውሉትን ስደተኞች በስብሰባ ሰበብ የሉም በማስባል ጉዳያቸውን እያስፈጸሙ እንደልሆነ ተመልክቷል። ከአንድ ወር በፊት ከ160 ሺ በላይ ህዝብ የተፈናቀለበትን ችግር ለማወቅ በቆንስላው የተገኙትና ከዲፕሎማቶች ውጭ ያሉ ሰራተኞችን ብቻ በመሰብሰብ ” የችግሩ ምንጭ ምንድነው በማለት?” የተወያዩት የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም፣ ለዚህ ሁሉ ችግር መፈጠር መንስኤ በሆኑት ዲፕሎማቶች ላይ አፋጣኝ እርምጃ እንደሚወስዱ ተናግረው የነበረ ቢሆንም እስካሁን የወሰዱት እርምጃ አለመኖሩ ታውቋል።
“የመኖሪያ ፈቃድ የላችሁም” በሚል ምክንያት ኢትዮጵያውያን ከሳውድ አረቢያ እንዲወጡ ሲታዘዙ፣ ከዚህ ቀደም በቋሚነት ተቀጥረው ይሰሩ የነበሩ 24 የቆንስላው ሰራተኞችን የሚያግዙ በአገሪቱ የሚኖሩ 40 ድጋፍ ሰጪ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞች ህዳር 12 ቀን 2006 ዓም ለ3 ወራት በሚቆይ የኮንትራት ጊዜ ተቀጥረዋል። ከተቀጠሩት 40 ሰራተኞች መካከል 30 ዎቹ  ሰራተኞች የተቀጠሩት የዲፕሎማቶች የቅርብ ቤተሰቦችና ዘመዶች ናቸው። አብዛኞቹ ሰራተኞችም የተቀጠሩት የዘር ማንነታቸው እየታየ ሲሆን ከተቀጣሪዎቹ መካከል እንግሊዝኛ፣ አማርኛና አርበኛ ከማይናገሩት ጀምሮ ማስተርስ እና የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው ይገኙበታል።
ከተቀጣሪዎቹ መካከል የተሻለ የትምህርት ደረጃና ብቃት ያላቸው 10 ሰዎች ከአንድ ወር በሁዋላ ታህሳስ 14 ቀን  ተመርጠው እንዲባረሩ ሲደረግ 30 ዎቹ የዲፕሎማቶች ቤተሰቦች እንዲቆዩ ተደርጓል። አስሩ ሰዎች እንዲባረሩ የተደረጉት ከመባረራቸው ከአንድ ሳምንት በፊት  ከውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ሰባቱበቋሚነት እንዲቀጠሩ ደብዳቤ መላኩን ተከትሎ ፣ በትምህርት ደረጃና በችሎታቸው የተቀጠሩትን አስቀድሞ በማባረር እና ውድድር ውስጥ እንዳይገቡ በማድረግ የዲፕሎማቶችን ቤተሰቦች  እድሉን እንዲያገኙ ለማድረግ መሆኑ ታውቋል። በቆንስላው ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች ከ1 ሺ 300 እስከ 1 ሺ 500 ሪያድ የሚከፈላቸው ሲሆን፣ ለአዲሶቹ የሚከፈላቸው 2000 ሪያድ ነው።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ቴዎድሮስ የቆንስላውን ዲፕሎማቶች በማግለል ሰራተኞችን በዝግ ስብሰባ ያነጋገሩ ሲሆን፣ ሰራተኞችም የሳውድ አረቢያ ችግር ከመፈጠሩ በፊት የነበረውን ችግር አንድ ባንድ ዘርዝረው በድፍረት ተናግረዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አፋጣኝ እርምጃ እንደሚወስዱ ለሰራተኞች ቃል ገብተው የሄዱ ቢሆንም እስካሁን ምንም እርምጃ ባለመውሰዳቸው ችግሩ ተባብሶ መቀጠሉ ታውቋል።
አንደኛው ዲፕሎማት 9 ዘመዶቹን ሲያስቀጥር፣ ሌላዋ ደግሞ 8 ቤተሰቦቿንና የብሄሩዋን ልጆች ብቻ በመምረጥ አስቀጥራለች። ቀሪዎቹ 13 ሰዎች ደግሞ የሌሎች ዲፕሎማቶች ዘመዶችና ወዳጆች ናቸው።
ዲፕሎማቶቹ በሳውድ አረቢያ የሚኖራቸው ቆይታ ከ4 አመት የማይዘል በመሆኑንም ጊዜያቸውን ሀብት በማከማቸት እንደሚያጠፉ ታውቋል። ምንም እንኳ መንግስት ወደ ሳውድ አረቢያ የሚደረገው ህገወጥ ጉዞ እንዲቆም ቀደም ብሎ መመሪያ ቢያስተላልፍም፣ በሳውዲ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ሊቀመንበር አማካኝነት የህገወጥ የሰዎች ዝውውር በዲፐሎማቶች አማካኝነት ሲካሄድ መቆየቱን መረጃው ያሳያል።
በእስር ቤት ውስጥ የሚገኙ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ሊሴ ፓሴ እንዲሰራላቸው በተደጋጋሚ ሲጠይቁ፣ ዲፕሎማቶቹ ” ስብሰባ ላይ ናቸው” በሚል ለጥያቄያቸው መልስ እንደማይሰጡ መረጃው ያመለክታል።  የሳውዲው ችግር እንደተፈጠረ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ለዲፕሎማቶቹ በሰጡት ጥብቅ ትእዛዝ ለአንድ ወር ያክል ፈጣን አገልግሎት በመስጠት ከ130 ሺ በላይ ሰዎች ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ለማድረግ ቢችሉም፣ በአሁኑ ጊዜ ወደ ቀድሞ ሁኔታቸው መመለሳቸው ታውቋል። በእስር ቤቶች ውስጥ የሚገኙ በርካታ ኢትዮጵያውያን አሁንም ሊሴ ፓሴ እንዲሰራላቸው በተደጋጋሚ ወደ ቆንስላው ስልክ እንደሚደውሉ ቢታወቅም፣ አገልግሎት እያገኙ አለመሆኑ ግን ታውቋል።