Tuesday 11 February 2014

“ጥቁሩ ሰው” – የጥቁር ሕዝብ አባት (ከስንሻው ተገኝ)

አንድ ዘመን ሥርዓተ መንግስቱ በመቆየትም ሆነ አባላቱ የአሥራ ሰባተኛው ክፍለ ዘመን የተረት ዓለም ሰዎች ስለ መሰሉን- ሁሉም ነገር ስለገለማን አዲስ ሥርዓት፣ አዲስ መሪ፣ አዲስ ዘመን መናፈቅ ይዘን ነበር። ሰዓሊ ሁሉ፣ ደራሲ ሁሉ፣ ጸሐፌ -ተውኔት ሁሉ እጁን የሚያሟሸው በቴዎድሮስ ሥዕል፣ ተውኔትና ታሪክ ሆነ። ብርሃኑ ዘሪሁን- የቴዎድሮስ እንባ -(መጽሐፍ) ከዚያ በፊት ደጃዝማች ግርማቸው ተክለሐዋርያት- ቴዎድሮስ (ተውኔት) አቤ ጉበኛ – አንድ ለእናቱ (ታሪካዊ ልቦለድ) ጸጋዬ ገብረ መድኅን – ቴዎድሮስ (ተውኔት)…ሥዩም ወልዴ -ሥዕል..ታደሰ ወ.አ….ቅርጻቅርጽ እና የሥነ ጥበባት ትምህርት ቤት ሥስት አራተኛ ተማሪዎች..የቴዎድሮስ ሥዕል ግጥም -ቅኔ- ሥዕል አለፈላት።
ከአሮጌና ከገለማ ሥርዓት ነፃ የሚያወጣ አመጸኛና አመጻ የሚመራ ጀግና ስንፈልግ ባጀንና ቴዎድሮስን አገኘን። ከመቶ አመት በኋላ ነው ቴዎድሮስ የተፈለገው። በአጤው ሥርዓት በአንዳንድ ደራስያንና የዘመን ታሪክን በውዳሴና በነቀፋ በሚያቀርቡ ግለሰቦች ዘንድ እንደጭራቅ ይቆጠር የነበረው መይሳው ካሣ በለውጥ መሪነት የተፈለገበት መሪ ነበር። አብዮታዊው መሪ ጓድ መንግሥቱ እንኳ፥ “ቴዎድሮስ” (ምናልባትም ዳግማዊ ቴዎድሮስ) እኔ ነኝ። የዚህን ሕዝብ አብዮት እንድመራም ከሙታን የተጠራሁ ነኝ” እስከ ማለት ደርሰው ነበር። በቴዎድሮስ መንገድ አልተጓዘም እንጂ። በተረተኞች፣ በተረበኞችና በዋልጌዎች፣ በጐታቾችና በክፍፍል በኖሩ ዘንድ ተወዳጅ ያልሆነው ሕልመኛው ቴዎድሮስ በእርግጥ ከዘመኑ አርቆና አልቆ የሚያይ ስለሆነ ከወቅቱ ደባትርና ከመሳሰሉት ጋር ስምምነት አልነበረውም።
የአገር አመራር በተበላሸና ሕዝቡ የሚያምነው መንግስት ባጣበት፣ ብሔራዊ አንድነቱና ዳርድንበር አስከባሪ በሚሻበት ሰዓት ከመሐሉ የወጣ የጐበዝ አለቃ ሲያደንቅ ይገኛል። እንዲያ ካልሆነ ደግሞ ከአባት መሪዎቹ መካከል ያደነቀውን፣ የሚያደንቀውናና የሚያከብረውን መናፈቅ ይጀምራል። ባያውቀውም። ዛሬን ያስቡአል። አገር እንደ አቃቂ በሰቃ (ኮሎናልቤ) ከስኩት ፍርክስክሱ በወጣበት፣ ሕዝብ እንዲከፋፈልና እንዲጨራረስ ማናቸውም ዓይነት ሴራ በሚጐነጐንበትና መቀበሪያ ሳይቀር “እናገኝ ይሆን” የሚል ስጋት በተጫጫነን ሰዓት “የአንድነትን ጌታ” የአገሪቱን እውነተኛ አባት መናፈቅ ያለ ነው። እነዚህማ ሸጡን። እነዚህማ ለወጡን። መሬቱን ጋጡት። ከትውልዱ አባልነት መብታችን አንዲቱንም አላከበሩልንም። የአንድነትን አባት፣ የዘላለም ኩራታችን ምንጭ፣ ሁሉንም አበሻ በእኩልነት የመራውን ጀግና እንድንናፍቅ ጊዜው አስገድዶአል። ምኒልክን! ይኸ ደግሞ ከመካከላችን እንደ ምኒልክ ያሉ የአንድነት እምነት አራማጆች እስኪንቀሳቀሱ ድረስ ነው።
ነፃነት አንድን ሕዝብ ወደፊትና ወደላይ የሚያንደረድር (የሚወስድ) ኅይል ይሻል። ስለዚህ እውነተኛና ከዚህ በኋላ የሚመሩን (ከዘመኑ ቀድሞ እንደ ተወለደው ምኒልክ) ሰዎችም ወደፊት ብቻ ሳይሆን ወደ “ላይም” ሊመሩን የተዘጋጁ ናቸው። እነዚህ ቆነጃጅት አልተወለዱም አይባልም። እንዲያውም አይተናቸዋል። ዳስሰናቸዋል። ዓለምም አውቆአቸዋል። እኛ ግን ከጥቃት፣ ከእሥራት፣ ከእንግልት…ከመከራ አላዳናቸውም፥ እስክንድርን፣ አንዱዓለምን፣ በቀለን…ካድናቸው። ለወያኔ ወረወርናቸው ለአውሬ። አገርን የሚያድን መሪ ብቻ አይደለም። ዋናው ሕዝቡ ነው። በአድዋ ወሳኙን የመሪነት ሚና የያዘው ምኒልክ ነበር። የተዋጋው ሕዝቡ ነበር። ሕዝባችን ቅንና ጀግና መሪ፣ መሪውም ታማኝና ቆራጥ ሕዝብ ያገኘበት አንድ ወቅት ይኸ ነው።
በአንጻሩ በአመራር የጊዜ ማኅፀን ውስጥ ያሉት ወይም ቢወለዱም በአመራር ጉልምስና ዘመን ላይ የሚገኙት “መልካካም የኢትዮጵያ ልጆች” ወደ አገር አዳኝነቱ መንበር ሲመጡ የሚገጥማቸው ፈተና የትየለሌ ነው። ሁላችሁም አስቡት። የተሸጠ አገርና መሬት የማስመለስ ግዴታ ሊሸከሙ ነው። የተከፋፈለ የሕዝብ ይዞታ ሊያስተካክሉ ነው። የኢኮኖሚውን ሥርዓት መስመር ሊያስይዙት ነው። “ወደ ላይ መምራት” ባልሁት የአመራር ፈርጅ ደግሞ የሚጠብቃቸው ከዚህ ሁሉ በላይ ነው። በታላላቅ ዲታዎችና መንግሥታት ትእዛዝና መሪነት ሥር የወደቀችውን አገር ዜጐችዋ ባለሥልጣናት ይሆኑ ዘንድ መንገዱን መጥረግ አለ። የሕዝብን ነፃነት፣ መብትና ሕዝቡ በአገሪቱ ላይ ያለውን ሉዓላዊነት ማወቅና ማክበር አንዱ ነው። የሕብረተሰቡን መንፈሳዊና ባሕላዊ መብቶች ማረጋገጥና የመንግስትን ጣልቃ ገብነት ማስወገድ፣ የጽሑፍና አሳብን በነፃ የመግለጥ ተፈጥሮአዊ መብቶቹን መንከባከብ፣ ፍትሕና ርትእ በራሳቸው ጐዳና ከመጓዝ እንዳይታወኩ ማድረግ ማለት ነው። ዝርዝሩ በዚህ ይቀጥላል። በመሰረቱ ደግሞ ታሪክ ስትቆፍሩ ብትውሉ አገር የሸጠ፥ የአገር መሬት የቸበቸበ መሪ ታይቶ ተሰምቶ አይታወቅም። በውጭ ምስጢር ባንክ የተቀመጠውን ገንዘብ ቁልፍ መለስ ለሚስቱ ካልሰጣት እሱም በሞቱ ከስሮአል። እኛም ያንን ለማስተካከል ብዙ ጥረት ማድረግ ይጠበቅብናል። የእሱን ወንጀል።
ጆርጅ ኦርዌል በ1984 መጽሐፉ በአምባገነኖች አገዛዝና ዘመን “እውነት ውሸት፣ ማይምነት እውቀት፣ ጥላቻ ፍቅር..ይሆናል” ይላል። ስለዚህ የወያኔን ባሕርያት የምንረዳው ዛሬ አይደለም። አብረን ኖረን የመንግስት ጠባያት ያልሆኑ- መሆንም የማይገባቸውን ስርቆትን፣ ተራ ውንብድናን፣ ቅጥፈትን፣ የጅምላ ግድያን፣ ፀረ ሃይማኖት አቋምን፣ የመብት ረገጣን…በየዓይነቱ እንደ ቡልኮ ተከናንቦ አይተነዋል። አንዳንድ ፀረ ሕዝብ ተግባራት ከየት መጡ ሳይባል እንኳ “የእሱ ሥራዎች ናቸው” ማለት ቀላል ሆኖአል። ትግርኛ ተናጋሪ ወገኖቼ ፀላዔ ሰናይ ይሉአቸዋል። አንዳችም በጐነት ያልተፈጠረባቸው ለማለት ነው። የሰሞኑን ደንባራ ፖለቲካ ለአብነት ማውሳት ለተነሳንበት ጉዳይ ብርሃን ይፈነጥቃል ባይ ነኝ።
በቅጥፈት የተካነው ሰውየ ከተለያቸው ወዲህ ወያኔዎች ያንኑ የተለመደ ውሸት ከመደጋገም በቀር ሌላ መፍጠር፣ በሌላ ስልት ማወናበድ አልሆንላቸው ብሎአል። ውሸት እንደ ቅርስ በነገሠበት አምባቸው ደግሞ ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያ ያላትና ያፈራችው መንፈሳዊና ስጋዊ ቅርስ ሁሉ አንደኛ መጥፋት አለበት፣ ዳግመኛም- አገሪቱ ካልጠፋች..ታሪክዋ ከዛሬ ተጀመረ መባል አለበት። ታሪክ ከእነሱ አልነሳ ሲላቸው አሁንም ያለፈውን በጐ ታሪክ፣ አኩሪ ባሕልና ጀግንነት፣ የአንድነት ጥበቃ መንፈስ…እንደ ቀላል ነገር ለመግደል ወጥተዋል።
ውሸታቸው ባያልቅም እውነት መናገር እንጀምር
ለዚህ ሥርዓት ማንኛውም ያለፈ ታሪክ፣ ታላላቅ ጀግኖች፣ ዳር ድንበር…የረከሰና የተናቀ፣ መለወጥና መደምሰስም አለበት። ሁላችሁም ለወያኔ ዓላማና ዛቻ፣ ቅጥፈትና ፀረ አንድነት እንግዳ አንዳለመሆናችሁ የሟቹንም ዛቻና አቋም ታስታውሳላችሁ። ስለ ሰንደቅ ዓላማ ምን አለ? ስለ አገሪቱ አንድነት ምን አለ? ምንስ ፈጸመ? ተከታዮቹስ ምን እያሉና ምን እያደረጉ ናቸው? በአጭሩ የሚነገረው ውሸት፣ የፈጠራ ታሪክና ከፋፋይ ፕሮፖጋንዳ አልቆ እናርፈዋለን ብለን ስናስብ ከቶውንም ወፍጮው ይበልጥ እየፈጨ ስለሆነ በውሸቱ መካከል ስለእነሱም እውነቱን መናገር መጀመር ያለብን ይመስለኛል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ትሩማን “ሪፐብሊካኖች ስለእኛ ውሸት መናገርን ካላቆሙ ስለእነሱ ያለንን እውነት መናገር መጀመር ያለብን ይመስለኛል” ብለው ነበር።
ስለ ዳግማዊ ምኒልክ ጥቂት ከመናገሬ በፊት ስለ መለስ ጥቂት-እጅግ ጥቂት ለማለት እወድዳለሁ። የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ሲዘልፍ..ዋና ዓላማው የኢዮጵያን ስም መለወጥ ነበር። ስለዚህ ለብዙ ዓመታት ኢትዮጵያን በስም ከመጥራት ይልቅ “አገሪቱ” ነበር የሚለው። ሥልጣን ሲጥመውና አገሪቱም የማትፈርስ (በቀላሉ) ስትመስለው “ኢትዮጵያ” ማለት ይዞ ነበር።
ቀደም ሲል ጆርጅ ኦርዌልን ያነሣሁበት ምክንያት “ውሸት እውነት” የሚሆንበትን ትክክለኛ አጋጣሚ መከሰት በሚመለተው ነው። እንደሚባለው በአምባገነን መንግሥት ሥር የመጀመርያው ጥቃት የሚደርሰው “በእውነት” ላይ ነው። በሕዝባዊ እውነት ላይ! በታሪኩ ላይ ነው። በጀግኖቹ ላይ ነው። ስለዚህ በአገር የተገኘው ቀጣፊ ሁሉ ዛሬ በፕሮፓጋንዳው ሰፈር፣ በአራት ኪሎ ቤተ መንግስትና በየክልሎቹ አመራር አምባ የተሰባሰቡት የሥነ አእምሮ ጠቢባን (pathological liars) የሚሉአቸው የሚታዘንላቸው ሕመምተኞች፣ እውነትን የሚፈሩ፣ እውነት ሲነገር የሚደነግጡ፣ እውነት ሲወጣ የሚረበሹ ናቸው። ስለዚህ “አንድነት” በተፈተነበትና የአገር ሽያጭ በደራበት ሰዓት አንዱ ማወናበጃ ስልት ያው ምኒልክን በወንጀል መክሰስ ነው። “አምስት ሚሊዮን ኦሮሞ ገደለ” ነው አዲሱ አማርኛ። ለመሆኑ በምኒልክ ጊዜ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር ከ5 ሚሊዮን ይበልጥ ነበር? ከዚህ ውስጥ የኦሮሞው ቁጥር ስንት ነበር? ለመሆኑ ምኒልክ ማነው? ምን ሰራ? ሕዝብን ከጫጫታው (ከዘመኑ) ለማዳን መሞከር አለብን ወይስ ታሪክ ነፃ ያወጣዋል በሚል አደብ እንግዛ?
“ ጥቁሩ ሰው” – እንደ ሰው
ታሪክ የበጐነት ምስክር – ወይም ለበጐነት የሚያደላ እማኝ ብቻ አይደለም። የአጥፊዎችን ጥፋት፣ የከሐዲዎችን አሳፋሪ ተግባር፣ የአምባገነኖችን ክፋትና ኢሰብአዊ አገዛዝ ጭምር ዘግቦ ለትውልድ ያስተላልፋል። ይሁንና ታሪክ የማያውቁ አዋቂዎች በመምሰል፣ አዳዲስ ድርሰት በመጻፍ ከሐቅ ግድግዳ ጋር የሚላተሙ፣ በባሕርያቸው ፀላዔ -ሰናይና የእውነት ጠላትነት ያላቸው ደካማ ፍጡራን መድረክ ሲደላደልላቸው የሚያዥጐደጉዱት ቅጥፈት መታለፍ እንደማይገባው እየተከሰተልን መጥቶአል። እስካሁን ግን “ለቅጥፈት ማስተባበያ” ወይም ማስተካከያ አያስፈልገውን በሚልና ውሎ አድሮ ሐቅ ይረታል በሚል እምነት ቅጥፈት ቅጥፈትን፣ ፈጠራና ድንፋታ ራሱን ሲፈጥርና እንደአሜባ ሲራባ በቸልታ ያለፍናቸው ጉዳዮች ሞልተዋል። ከሁሉም ከሁሉም አንድን ኅብረተሰብ የሚያቃጥለው የታሪኩና የጀግንነቱ መታወቂያ ሰነዶች፣ ግለሰብ ጀግኖችና ብሔራዊ መከበሪያ ሐውልቶቹና ቅሪቶቹ መደፈር ነው። በዚህ ረገድ ብዙ ተደፈርን። በዓለም አቀፍ ደረጃ የ”ታላቅ መሪነት”ን ደረጃ የተቀዳጁትን፣ ጠላት ሳይቀር የሰገደላቸውን መሪዎቻችንን ሳይቀር ዛሬ የራሳችን ልጆች በእነዚህ ላቅ ያሉ ሰዎች ላይ ሲያቅራሩ ስንሰማ እንቅልፍ መንሳቱ አልቀረም።
የወያኔ ቀዳሚ ሰልፍና ፍልስፍና ሕዝብን መከፋፈልና አገሪቱንም ማፍረስ መሆኑን ለመጀመሪያ ጊዜ ተጠራጥረው ይከራከሩን የነበሩ ሰዎች ዛሬ ከግንዛቤ በመነሳት ራሳቸው “አገር እየጠፋ” መሆኑን እያረዱን ነው። በወያኔዎች በኩል ደግሞ የአገሪቱንም ሲሳይ እያፈሱ መልሰው አገሪቱን ለማጥፋት ማናቸውንም ሴራ እየፈፀሙ ናቸው። የትሮትስኪ ታሪክ መዝጋቢና የሩሲያን አብዮት ክሽን አድርጐ ያቀረበው አይዛክ ዶቸር ስለ ሩሲያ አብዮት መሪዎች ሲጽፍ “እነዚህ ሰዎች የማያውቁትንና ሊያውቁ ያልቻሉትን አገር ተረከቡ። ወይም በእጃቸው አስገቡ። ቀጥሎም የሚያምኑበትን አቃጠሉት። አቃጥለውም ሰገዱለት” ይለናል። አዎን ወያኔዎች ጥገትዋን አልበው እየጠጡ፣ አርደው ሊበሉአትም ፈለጉ” ለማለት ይቻላል። በተአምር በእጃቸው የገባችውን አገር ማዳን የብዝበዛቸውና የዘረፋቸው ዋስትና በሆነ ነበር። ይልቁን እዚህ ከደረሱ በኋላ እንኳ የዚህን አገር አንድነት ማዳን ቢሞክሩ ቢያንስ ልጆቻቸው አገር አለን እንዲሉ ባስቻላቸው ነበር። ይልቁንም ኦሮሞዎች ነን የሚሉ በዕድሜም፣ በግንዛቤና በአእምሮ ያልበሰሉ ልጆችን በመመልመል የሚያንጫጩብን እነዚሁ አገር በእጃቸው የወደቀ ሰዎች ናቸው። ምኒልክን ለመወንጀል የክሱን ነጥብ ሁሉ ከየት አገኙት?
እውን እነዚህ ጨርቋ ሕፃናት – የጨርቋ አእምሮ ውጤት የሆነ ፕሮፓጋንዳ በጩኸትና ሰላላ መላላ በሆነ ልሳን ሲያስተጋቡ የዚህ አገር ዋልታና ወጋግራ የሆነው ኦሮሞው ኅብረተሰብ ምንኛ እንደሚያፍርባቸው ትገነዘባላችሁ? ለመሆኑ ከኢትዮጵያ ታሪክ ባለቤትነትና ክብር ሊነጥለን የሚችል ማነው? ጃዋር? አያት ቅድመ አያቶቻችን ደምና አጥንት የሰጡአት አገርኮ ናት! የወያኔ የመስዋዕት ጠቦቶች ለሆኑት እነዚህ ኅፍረተ ቢሶሽስ የኦሮሞን ውክልና ማን ሰጣቸው? ስለማያውቁት፣ ስላላወቁትና ሊያውቁትም ስላልፈለጉት ሕዝብ በድፍረት መናገርን ከየት አመጡት? እነዚህ ልጆች “ወገኔ ነው” የሚሉትን ኦሮሞውን ኢትዮጵያዊ ከሌሎች (ለምሳሌም አማራው) ብሔሮች ጋር በማጋጨት ሊያመጡ የሚችሉትን ትርፍ ሊነግሩን ይችሉ ይሆን? ወይ ልክፍት!
ከሶቪየት ኀብረት ኤምፓየር መፍረስ በኋላ አንዳንድ የአሜሪካ የፖለቲካ ፈላስፎች እንደ ሶስተኛ አገር የሚታዩ የኅብረተሰብ ጽናትና ሰላም ያላቸው አገሮች በተቻለ መጠን ተሸንሽነው ብዙ አገሮች እንዲወጣቸው ሰፋፊ ጽሑፎችን በገበያ አውለዋል። ከእነዚህም መካከል መለስ ዶላር ያፈስስለት የነበረው የሐርቫርዱ ሳሙኤል ሐንቲንግተን ይገኛል። ከዚያም ሌላ አንዳንድ የሲአይኤ ቅጥረኞች ጽሑፎች በየጥናቱ መደብር አሉ። ዩጐዝላቪያ የዚህ ፍልስፍና “ጊኒፒግ” ናት። ከ1991 ወዲህ ደግሞ ኢትዮጵያ የምትታመሰው በዚሁ ረቂቅ የጥፋት አውሎ ነፋስ መሆኑን አንዘንጋው። እነሆ እንደ ጃዋር ያሉ አለማወቃቸውን እንደ እውቀት፣ ጮኾ መናገርን እንደ ሐቅ፣ የፈለጉትን ጥጃ የአምልኮ ጸጋ በመቁጠር አየረ አየራቱን ሲያተረማምሱት ከእንግዲህስ “ተመከር! ተሳስተሃል! በአገር፣ በሕዝብና በታሪክ ላይ ያመጽህ ባለጌ ነህ” ማለት የሚገባ ይመስለኛል። ልድገመውና “በአባቴ ሙስሊምና ኦሮሞ፣ በእናቴ ክርስቲያንና አማራ ነኝ” በማለት ጅምሩን በማይጠቅመው መደምደሚያ ያበላሸዋል። ጃዋር መሐመድ። ሙስሊም፣ ክርስቲያን፣ አማራ፣ ኦሮሞ! ከኢትዮጵያዊነት ውጭ ምን ይሁን?
ጐበዝ በዚህ ዓይነቱ ጊዜ ከየጉድጓዱ ብዙ አይጦች ሊወጡ ይችላሉ። አትደነቁ። አንዳንዶቹ የመታወቅ አባዜ (የእንክብካቤ እጦት አባዜ…ወዘተ) የተከሰተባቸውና “እገሌ” ለመባል የሚጣባ ሕመም ተሸካሚዎች ናቸው። አንዳንዶቹ ቀጥታ ራሳቸውን ለማያውቁት ተልእኮ በመስዋዕትነት ለመሰጠት በምንዳ የተገዙ ናቸው። ለዚህ ዓይነቱ ተልእኮ የተመደበ በጀት ስላለ ሰው ከተገኘ ገዥ አለ። ሕሊና ለሌለው፣ ለሚሸጥ ወይም ለሚያከራይ ዘወትር ክፍት ቦታ አለ። እነ እንቶኔ በዚህ የሕመም ዘርፍ ላይ በመሆናቸው ሊታዘንላቸው እንጂ ሊታዘንባቸው አይገባም። ቀደም ሲል የተጠቀሰውን ጉብል አንድ ጊዜ በአንድ የቨርጂኒያ አዳራሽ ትልቅ ስብሰባ ላይ አይቼዋለሁ። እዚያ ስብሰባ ላይ ወደ ዘጠኝ መቶ የሚጠጉ ሰዎች ነበሩ። ይሁንና እስኪታወቅ ሳይሆን እስክንሰለቸው ድረስ የባጡንም የቆጡንም ሲናገር ቆይቶ “እዚህ ሥፍራ ኦሮሞና ሙስሊም ለምን አልተጋበዘም?” ይላል። መቸም “ከእናንተ መካከል ኦሮሞ የሆናችሁ ተነሱ! ሙስሊም የሆናችሁ ተነሱ!” አይባልም። ይኸ ደግሞ ከቅን አእምሮ የመነጨ ነው አይባልም። የሌሎቹንም “ዋልጌ ጭንቅላት” ባለዶላሩ ዋሐቢ፣ የሽብሩ ልጆች እነ…..በማናቸውም ሂሣብ ሊገዙአቸው አይፈልጉም አይባልም። ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን እስከ ተዋጉላቸው ድረስ።
አንዳንድ የዋሐን ወገኖቼ የእነዚህን በጥላቻ የተፀነሱ፣ በጥላቻ የተወለዱና የጥላቻን መርዝ በመካከላችን የሚዘሩ ሰዎችን ተጽእኖ እስከ መፍራት ደርሰዋል። ኦሮሞው ኅብረተሰብ እንዳይቀበላቸው ነው? ያፍርባቸዋል። ከአገር እድር ያስወጣቸዋል። ስለዚህ በሶሻል ኔትወርኩ ረገድ ኅላፊነት የወሰዱ ሁሉ ለኦሮሞ ወገኖቻችን የመናገር ዕድል (በሰፊው) መክፈት አለባቸው። በአንድ በኩል ደግሞ ታሪክ የሚያቆሽሹትና ወደ ኋላ እየተመለከቱ የሚናገሩት እነዚህ ወገኖች ርስበርሳችን ስለጀግንነት፣ ስለታሪክ፣ ስለታላቋ ኢትዮጵያ ማንነትና ምንነት….እንድንነጋገር ዕድል እያስገኙልን ይመስለኛል።
ጥቁሩ ሰው – ለጥቁር ሕዝቦች
ጀርመኖች በኦቶፎን ብዝማርክ፣ ጣልያኖች በጁሴፔ ጋሪባልዲ፣ ፈረንሳዮች በናፖሊዮን ቦናፓርቲ፣ በዣንዣክ ሩሶ፣ በዣን ደ አርህ፣ አሜሪካኖች በጆርጅ ዋሽንግተን፣ አብርሃም ሊንከን…..እንግሊዞች በዊልያም ዘኮንከረር፣ በዊንስተን ቸርችል፣..ይኰሩም ይኩራሩም ይሆናል። የእነዚህን ሰዎች ጀብዱ ስንሰማ፣ በትምህርት ቤቶች ዝናቸውን ስናወሳና ስናጠናቸው ስለኖርን የራሳችን ሰዎች እስኪመስሉን ድረስ በልባችን ጽላት ላይ ታትመዋል። ሰዎቹ በየዘመናቸው ለአገሮቻቸው ባበረከቱአቸው አስተዋጽዎችና የተለዩ አገልግሎቶች የየአገራቸው “አባቶች” እስከ መባል ደርሰዋል። በፖለቲካና በወታደራዊ መስክ ብቻ ሳይሆን እነዚህ አገሮች ብቻ ሳይሆኑ ሌሎችም አያሌ አገሮች ለአለም ጸጋ በሆኑ ልጆቻቸው አማካይነት በኪነ ጥበባት፣ በሳይንስ፣ በሥነ ጥበባትና በኬንያ (ቴክኖሎጂ) ባርከውናል። ልጆቻቸውን ተጋርተናል።
እንደገና ጀርመኖች በሒትለር፣ ጣልያኖች በሙሶሊኒ፣ ካምቦድያውያን በፓልፓት፣ ኡጋንዳውያን በኢዲአሚን፣ወዘተ እጅግ እንደሚያዝኑና እንደሚሸማቀቁ ይሰማኛል። እኛም የዚች አገር ጐስቋሎች ኢትዮጵያውያን በሃያ አንደኛው ምዕት ዓመት መለስ የሚሉት እኩይ ነፍስ ለኢትዮጵያ የዛሬው ትውልድ በመስጠታችን ጭብጥ ልናክል ነው። ሞተ ከተባለ ወዲህ እንኳ አገር እየሰጠ፣ አረብና ሕንድ እያነገሰብን፣ ምውት መንፈሱ እንዳሸበረን ነው። ሁላችንም የዓለም ዜጎች ይቺን የጋራ መሬት እኩል እንደምንባረክባት ሁሉ ጀግንነታቸው ያሞቀን የሃያኛው ክፍለ ዘመን ግዙፋን ባለታሪኮች ነበሩ። ጀኔራል ድዋይት አይዘንሐወርን፣ ጀኔራል ጆርጅ ፓተንን፣ ፊልድ ማርሻል ሞንትጐመሪን…እንደራሳችን እንጋራለን የሚል እምነት አለኝ። “እነዚህ ሰዎች ምነው ኢትዮጵያውያን ቢሆኑ ኑሮ” ብዬ በቁጭት አልናገርም። የአንዲት ምድር (ራችን) ልጆች በመሆናቸው ብቻ እንደራሳችን ጀግኖች- የሁላችንንም እምነት በተግባር ያዋሉ፣ የሁላችንንም ጦርነቶች ተዋግተው ያሸነፉ ስለሆኑ “የሁላችንም” እናደርጋቸዋለን። እንደ ምኒልክ ያሉ – እንደ ጐበና ያሉ- እንደ አሉላ ያሉ- እንደ አበበ አረጋይና በላይ ዘለቀ ያሉ ጀግኖች አባቶች ያሉት አገር ልጆች በመሆናችን እኛም ለዓለም ባበረከትናቸው ጀግኖቻችን ኩራት ይሰማናል። በምኒልክ የተመራው የኢትዮጵያ ሠራዊት በአንዲት ጀንበር የአንድ አውሮፓ ኅይል ካንኮታኰተ በኋላ በማግሥቱ የጠቅላይ ሚኒስትር ክሪስፒ መንግሥት (በኢጣክያ ሕዝብ እንደጐርፍ መውጣት ምክንያት) ከሥልጣን ከመወገዱም በላይ በናፖሊ ከተማ የነበረውን የንጉሡን (አምቤርቶ) አልጋ ወራሽ ሕዝቡ በትከሻው ተሸክሞ “ታላቁ ምኒልክና የአድዋ ጀግኖች ኢትዮጵያውያን ለዘላለም ይኑሩ ብለህ ጩኽ” በማለት ቀኑን በሙሉ በዚህ መልክ ሲያንባርቅ እንዲውል አድርገውታል። በማግሥቱ የወጡ የኢጣልያ ጋዜጦች ኢጣሊያ ራስዋ እንደተማረከች አድርገው ጽፈዋል። ምኒልክ!
አንዳንድ የጦርነት ዘገባዎችን፣ መጻሕፍትንና ታሪኮችን ለተከታተሉ ጀግኖች የሠራዊት አዛዦች ድል ካደረጉ በኋላ “ጠላት ነው” በማለት አይንቁትም። ወይም በእጄ ገብቶአል ብለው አይበቀሉትም። እንዲያውም በ”ተቃራኒ መስክ” የተሰለፈውን በክብር ያስተናግዱታል። በጦር መሪነታቸው እጅግ የተደነቁና በመሠረቱ በተቃራኒ ዐውድ ተሰልፈው ታሪክ የሰሩ ጄኔራል መኰንኖችን ላስታውስ እወዳለሁ። በአሜሪካ የሲቪል ጦርነት የኮንፌደሬሽኑ ጦር አዛዥ ሮበርት ሊ በአሜሪካ ሕዝብ ዘንድ ከሜጀር ጄኔራል ጆርጅ ማክሊላን የበለጠ ይታወቃል። በየከተማው መንገዶች ተሰይመውለታል። የጦር ምሽጐች በስሙ ተጠርተዋል። ከስለጠነው ዓለም ሌላም ማስረጃ ለማምጣት ይቻላል።
የሁለተኛው ዓለም ጦርነት ከሚያውቃቸው ታላላቅ ጄኔራሎች መካከል ሒትለር በሰሜን አፍሪካ በዋና አዛዥነት ያሰለፈው ፊልድ ማርሻል አርዊን ሮሜል (የበረሃው ተኩላ) በምዕራብም ሆነ በምሥራቅ- በአክሲስ ፓወርስም ሆነ በአላይድ ፎርስስ እጅግ የተደነቀ ነው። በመሠረቱ ለጀግና ሠራዊት ባላንጣው የተከበረ ነው። በሬሳው አይጫወትም። ወይም ወያኔዎች በኢትዮጵያ ሠራዊት ሬሳና የደከመ አካል ላይ ቆመው እንደ ፈነደቁትና እንደሸለሉት ሳይሆን የሰብአዊነት ክብርና መገመቻ ጠላትን እንደአግባቡ ማድነቅ መቻልም ነው። ለተፋላሚ ክብር መስጠትና እንክብካቤ ማድረግ ነው። እነዚህ ሰነፎች ገዥዎቻችን ምንኛ ደካሞች እንደሆኑ አያችሁት?
ከአገራችንምኮ ለዚህ ክርስቲያናዊ አርአያነትና የሰለጠነ ወታደራዊ ባሕል ምሳሌ አንቸገርም። አድዋ ላይ በአንድ ጀምበር በርከት ያሉ ጄኔራል መኰንኖችን ድባቅ የመታውና ያንኑ ያህል የማረከው እምዬ ምኒልክ በእጃቸው የገቡትን ምርኮኞች ማለፊያ ምግብ እየሰሩ (ፓስታ፣ ሞኮሮኒ ወዘተ) በደንብ ከመመገብ ባሻገር ራሳቸውና ደገኛይቱ ባለቤታቸው እቴጌ ጣይቱ እንደ ሐኪም ቁስል መጥረግ፣ ፋሻ ማሠርና የመሳሰሉትን የሕክምና አገልግሎቶች ጐንበስ በማለት ፈጽመዋል። ጦርነቱ እንዳለቀ ምሽት ላይ በየድንኳኑ እየተዘዋወሩ “ገደልን ብላችሁ እንዴት እንዲህ ያለ ፍከራና ሽለላ ታደርጋላችሁ?” በማለት ኅዘናቸውን እስከ መግለጥ ደረሰዋል። (አንቶኒ ሞክለር ኅይለስላሴስ ዋር በሚለው መጽሐፉ በመጀመሪያው እትም እንደ መግቢያ አድርጐ ገልጦታል።
በሌላው ታሪካቸው እንደ ተገለጠው አጤ ምኒልክ ከንጉስ ተክለሃይማኖት (ራስ አዳል ይባሉ ከነበሩት) ጋር እምባቦ ላይ ሲዋጉ የጐጃሙ ገዥ ቆስለው ሲማረኩ ራሳቸው ከመሬት ተቀምጠው ቆስሉን በጨውና በአልኮል እየጠረጉ እንዳስታመሙአቸው ይታወቃል። በኋላ ደግሞ አጤ ዮሐንስ ያለ የሌለ ጦራቸውን አስከትተው ጐጃምን ወርረው፣ ሥፍር ቁጥር የሌለውን ሕዝብ ዓይን በጋለ ብረት አቃጥለው፣ ሠራዊታቸው ቤት እየዘረፈ፣ በወንዱ ፊት ሚስቱን እየደፈረና ጐተራ እያራገፈ በጠቅላላው ንጉሰ ነገሥቱ እያዩ ሲያቃጥሉ አጤ ምኒልክ “እባክዎ ጃንሆይ ከንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ጋር ተጋጨሁ ብለው ሕዝብዎን አይጨርሱት” በማለት እንደተማጸኑአቸው የተጻፈ ታሪክ ሞልቶአል። እንዲያም ቢሆን የትናንት የአገሪቱን መሪዎች ለመወንጀል አልሻም።
ወደ ሃምሳ ዓመት የሚገመት ሙያዬ ከብዙ ሰዎች ጋር አገናኝቶኛል። እንደ ደጃች ኅይለ ሥላሴ ጉግሳ ካሉ ከሐዲዎች- እንደ ራስ መስፍን ካሉ አርበኞች- እንደ ጋዜጠኛ (ከንቲባ) ደስታ ምትኬ ካሉ በየአድዋው ጦርነት ላይ ከዋሉ የታሪክ ምስክሮች፣ እንደ ፊታውራሪ ተክለሃዋርያት ካሉ በ20ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ አንስቶ አገሪቱን ከፊውዳል ሥርዓት ለመጠራረግና የፖለቲካውን ሥርዓት ግልብጥብጡን ለማውጣት ከደከሙ ምሁራንና መሪዎች ጋር ትከሻ ለትከሻ ባልተሻሽም አጠገባቸው ተቀምጨ ያልነበርሁበትን ዘመን ልኖረው ሞክሬአለሁ። የሁሉም የጋራ ምስክርነት (የጀግናውም የባንዳውም) ኢትዮጵያ እንደ ምኒልክ ያለ መሪ ታድላ አታውቅም። እግዚአብሔር ይመስገን፤ ጻድቁ ዮሐንስ በጐ አእምሮ የወለደው ነው።
አዎን የዚህ መጣጥፍ አጀማመሬ አውሮፓውያንና አሜሪካውያን (ሌሎችም ሕዝቦች) የሚኮሩባቸው መሪዎችና በመሰረቱም የሚያፍሩባቸው አምባገነኖችም ሊኖሩባቸው እንደሚችል ላመለክት ሞክሬአለሁ። እንዲያውም አገር በችግር ማጥ ውስጥ ስትገባ ልባቸውን፣ ጭንቅላታቸውንና እጃቸውን አስተባብረው ሕዝብን በአንድ ጐራ አሰልፈው ከታላቅ ውጤት ላይ ያደረሱት እንዲህ ያሉ መሪዎች የየአገሮቻቸው አባቶች እስከ መባል ደርሰዋል። ጆርጅ ዋሽንግተንን አላነሣሁምን? የመቶዎች ባሪያዎች ባለቤት ቢሆን እንኳ ሁሉም አሜሪካዊ የአገሪቱ አባት ይለዋል። በዚሁ ልክ የኢትዮጵያን ታሪክ የመረመሩ የውጭ አገር የታሪክ ስዎችና ኢትዮጵያውያን ምሁራን ሁሉ አጤ ምኒልክንና አሳዳጊ አባታቸው አጤ ቴዎድሮስን የኢትዮጵያ አባቶች ይሉአቸዋል። ለከፈሉት የሞት ዋጋ፣ ለተሸከሙት የኢትዮጵያ ግዙፍ ተራራ፣…ይኸ የሚበዛባቸው ክብር አይደለም። ሁለቱ ሰዎች (ባይሆን ጣይቱን እንጨምራለን) ይህን ክብር ካልተቀዳጁ ማን ሊቀዳጅ ነው? ጣይቱን እናታችን ብንል ምንኛ ደስ ባለኝ!
ያለፈው ወር የእምዬ ምኒልክ መቶኛ ሙት ዓመት ነበር። አሸናፊዎች ሁሉንም እንደ ፈለጋቸው በሚያደርጉበት፣ በብር በወርቁ በሚያዙበት፣ ታሪክ ድርሰት ሆኖ በማረሻ በሚጻፍበት፣ የአገር ዳር ድንበር ያለ ጠባቂ በሚቀርበት፣ ጀግኖች የወደቁለት አንድነት መጫወቻ በሆነበት፣ ዜጐች እየተነቀሉ ነጩ፣ ብጫው፣ ጠይሙ…የባዕድ አገር ነጋዴ የሚምነሸነሽበት መሬት ጥንቡን በጣለበት ዘመን ላይ፣ መንግስት ሌባ፣ ሌባም መንግሥት በሆነበት ወቅት-እንደ መገኘታችን ብዙ ብዙ -የለም፤ ሁሉም በጐ አገራዊ ባሕል ትርጉም ባጣበት ሰዓት በሕዝብ ዘንድ ያለው ሐቅ ሁሉ ተጠቂ መሆኑ አንድና ሁለት የለውም። እነሆ ከሃያ ሦስት ዓመታት ወዲህ የኢትዮጵያ ታሪክ ተለውጦ ስለኢትዮጵያ አንድነትና ታሪክ የቆመው ሕዝብና ተቃዋሚ ኅይሎች ከሐዲ ሲባሉ…ወርቁም ሚዛኑም እንዳልነበረ ሆኖአል። ስለዚህ በምኒልክና በጣይቱ ላይ የሚወርደውን የፕሮፓጋንዳ መዓት፣ የፈጠራ ድርሰትና ልብ ወለድ ድርሳን ስታስቡት ለመሆኑ ከወያኔ አምባ የተጠበቀው ሌላ ንግርት ምን ነበር? በግልጽ የኢትዮጵያን አንድነት ተቋቁመው ከዚህ ደረጃ ያደረሱት ግለሰቦች በረከት፣ ስብሐት ነጋ፣ ዐባይ ጸሐይና ግልገል ወያኔዎችና እንደ ወያኔ የማሰብ በሽታ ከሸመቱ ግለሰቦች ምን ይጠበቅ ነበር? የኢትዮጵያን አንድነት አባቶችና ጠባቂዎች እንዲያወድሱ ነበር? ቀደም ሲል እንዳልሁት ታሪካችንን በጽሞና እንድንመረምር ዕድል የሰጡን ይመስለኛልና በበጐነት እንጠቀምበት።
ቀደም ሲል ስማቸውን ያነሣኋቸውን ጋሪባልዲንና ቢዝማርክን ለምክንያት ነበር የጠቀስሁአቸው። ጋሪባልዲ ኢጣልያንን ለማዋሐድ፣ ቢዝማርክ ተበታትና የቆየችውን ጀርመንን አሰባስቦ አንድ አገር (ኔሽን) ለማድረግ ሲወጡና ሲወርዱ የነበሩበት ሰዓት (በዘመነ ጓድነት) አንድ ነው። አፍሪካዊው መሪ (ጥቁር ሰው) ምኒልክ በተመሣሣይ ጥሪ በታሪክ መድረክ ላይ የታየውም በዚሁ የታሪክ ወቅት ነው። በዚህ ታሪካዊ ወቅት ምን ተፈጠረ? በዘመናት ውስጥ ተሸርሽራና ተበጣጥሳ የቆየችውን ኢትዮጵያ ዳር ድንበር አንድ አደረጉ። ሰበሰቡአቸው። በእነዚህ ተግባራት ብቻ ዓለም ካደነቃቸው ከነጋሪባልዲ ጋር ታሪክን ሊሻሙ የሚገባቸው ምኒልክ ዛሬ በወያኔና አንዳንድ አጫፋሪዎች ምን እየተባሉ ነው? አንዱና ጥሩ ውሸት መፍጠር ያልቻሉት ፀረ አንድነቶች የጡት ቆረጣ ወንጀል ነው። ይኸ ከየት የመጣ ነው? ለመሆኑ ወንጀሉስ የት ነው የተፈጠረው? ትክክለኛም ሆነ አልሆነ መልስ የመስጠቱን ዕዳ የሚሸከሙት ወያኔና ሁሉም ፀረ አንድነት የሚያቀነቅንበት ዜማ የሚጫወቱት ናቸው።
በሌላ በኩል ደግሞ የኦሮሞ ሴቶችን ጡት ስለማስቆረጥ የተፈጠረው አጉል ነጥብ ከአማራው (ማለትም ከክርስቲያን) ባሕልና እምነት ጋር ጨርሶ የሚሄድ አይደለም። በአንጻሩ ለጋብቻና ለመሳሰለው ዕድሜና እጆቹ እርፍ ለመጨበጥ የደረሰ ኦሮሞ ገበሬ ሚስት ሊያገባ የሚችለው አማራ በመስለብ መሆኑን እንኳ ለመስማት ፈልጌ አላውቅም። በእውነቱ ግን ወንጀሉ በየዘመኑ ለሚፈጠር ኦሮሞ ሁሉ እንዲቆየው አልሻም። በዚሁ ዓይነት አጤ ዮሐንስ ወሎንና ጐጃምን “ፈጅተውታል፣ አቃጥለውታል” በሚል የዛሬና የወደፊቱ ጐጃሜና ወሎየ ሁሉ ትግሬንና አጤ ዮሐንስን እንዲጠላ አላደፋፍርም። በውነቱ ደግሞ ዘወትር የምናወድሰው ታሪካችን አላስፈላጊና አሳፋሪ ጓዝም አለው። ቀደም ሲል ያነሳናቸው የኢጣልያንና የጀርመን የዛሬ ትውልዶች የየራሳቸው አንካሳ ታሪክ አላቸው። እኛ ላይ ሲደርስ ነው ከተደረገውና ከተፈጸመው ሁሉ በላይ የታሪክ ድሪቶና ቡትቶ ያየነው።
ኢትዮጵያዊነት አረጀ?
ኢትዮጵያን፣ ኢትዮጵያዊነትንና የዚችን አገር ቁሳዊና መንፈሳዊ ሀብታት፣ ዜግነትንና እሴትን የሚጸየፍ አንድ ምስኪን ልጅ በአልጀዚራ ሲናገር ብዙ ኢትዮጵያውያን ሰምተውታል። የጋናው ኒክሩማህ፣ የኬንያው ኬኒያታ የኮትዲቮሩ ሑፌትቧኘ፣ የማላዊው ካሙዙባንዳ…በጆርጅ ፓድሞን መሪነት..ወደ አንድ የለንደን የስብሰባ አዳራሽ (በ1953 እ.አ.አ) የገቡበት ሁኔታ ትዝ ይለኛል። አዳራሹ በኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ አሸብርቆአል። እነዚህ በኋላ የአፍሪካ ታላላቅ መሪዎች የሆኑ የዚያን ዘመን የነፃነት ታጋዮች አረንጓዴ፣ ብጫና ቀይ የሆነውን የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ እያውለበለቡ ወደ አዳራሹ ሲገቡ የነበረበትን የክብር ሰልፍ ሳስብ በቦታው ለመገኘት እንደ ታደለ ሰው ዛሬ የልቤ ኩራት ወደር ያጣል! የጃንሆይ አጤ ኅይለሥላሴን ምስል በኮታቸው ክሳድ ላይ ያደረጉት እነ ንክሩማህ ሁኔታ ወለል ብሎ ይታየኛል። አዳራሹ በአእምሮዬ ይመጣል። ኢትዮጵያዊነትና “ኢትዮጵያዊ ነኝ” የዓለም ጭቁን ሕዝቦችና በተለይም የጥቁር ሕዝብ ኩራት እንደሆነ እነ ጃዋር ሰምተው ያውቃሉ? ለጥቁር ሕዝቦች ሁሉ “ኢትዮጵያ” ምን ትርጉም እንደምትሰጥ ለመሆኑ እነዚህ ይቺን አገር ካላፈራረስን እንሞታለን የሚሉ ሰዎች በመጠኑስ ቢሆን ያውቁ ኖሮአልን? “ኢትዮጵያዊነት” ከተራ ስያሜና ከአንድ ተራ አገር መጠሪያ በላይ መሆኑን ያውቁ ኖሮአልን? ለእነዚህ ሕዝቦች ዞሮ መግቢያና መመኪያ …መንፈሳዊ ቤታቸውና ምስለ-ገነት የመሆንዋን ሐቅ ምን ያህል ሰምተዋል? የማርከስ ጋርቪን ፍልስፍና ያውቁታልን? ዛሬ ዛሬ ደግሞ እግዚአብሔር (ያህዌ ኤሎሒም) ለአዳምና ለሔዋን የፈጠረላቸው ገነት በአንደኛዋ የኢትዮጵያ ክፍል የመሆንዋ ግልጽነት አማራውን፣ ኦሮሞውን፣ ትግሬውን፣ ከምባታውን፣ ሐድያውን…ለሁሉም የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ አባላት ተጨማሪ ኩራት በሆነ ነበር። (ከላይ የነካካኋቸውን ነጥቦች በይበልጥ ለማወቅ ማርከስ ገርቪንና ዱቢድ ሜሬዲትን ያነብቡአል።) በነገራችን ላይ ማርከስ ገርቪና ራስ መኮንን ይባል የነበረው ጃሜይካዊ ጓደናው በጃንሆይ ቅሬታ ያደረባቸው እነሱ ካሰናዱአቸው 3ሺ ዓለም አቀፍ ተጋዳዮች ይልቅ በእንግሊዝ ጦር በመጠቀማቸው መሆኑ ይነገራል።
በኢትዮጵያዊነት ማፈር እንደ አልጀዚራው ጉብል ባሉ የሐቅ ማይማን እየተነገረ ነው። ያ ጉብል – ጃዋር ደግሞ በሌላ ጊዜ በመቅለስለስ መልክ “ እኔ በአባቴ ኦሮሞና ሙስሊም፣ በእናቴ አማራና ክርስቲያን ነኝ።” ሲል አድምጨዋለሁ። የልጅነት ተማሪዬ ሌንጮ ለታ የደረሰበትን አጉል አጋጣሚ ያስታውሰኛል። የኦነጉ መሪ ኢትዮጵያ ውስጥ እንደ ልብ ሲዘዋወር በነበረባቸው ወራት በጣም የተከበሩ አባቶች ወደ ነበሩበት ወደ ጅባትና ሜጫ ሄዶ ነበር። ያ አካባቢ እጅግ አስተዋይ የሆኑት ፊታውራሪ አባዶዮ ሠርገኛ ጤፍ አስመጥተው “ከዚህ መካከል ነጩንና ጥቁሩን ለይልኝ” ብለው ጥላቻንና ጠላትነትን ያወገሁበት አካባቢ ነው። ታዲያ ሌንጮ “አማሮች ያገኙን እንደእነዚህ እንስሳት ከብቶች አድርገውን ነው” ብሎ ሲጀምር “ልጆቻችንና ወንድሞቻችን..አንተ የምትላቸው አማሮች ናቸው። እኛም አማሮች፣ አማሮችም ኦሮሞዎች ናቸው።” ብለው በማስጠንቀቂያ ሸኝተውታል። የሮይተርን ቀጥታ ምስክርነት ለመጥራት እችላለሁ። ታዲያ ጃዋር እንደ ነገረን፣ ኦሮሞም ነው። አማራም ነው። ሙስሊምም ነው ክርስቲያንም ነው። ኢትዮጵያዊ ካልተባለ ምን ሊሆን ፈለገ? ቅጥ አምባሩ የጠፋበት አይደለም ትላላችሁ?
እነዚህን ሰዎች ሳስብ ኢሳይያስና መለስን አስባለሁ። የኦሮሞ ነፃነት ግንባር የሚለውን ድሪቶ የለጠፈባቸው ኢሳይያስ አፈወርቂ ነው። ወይም ኦነግን ጠፍጥፎ የሰራው እሱ ሲሆን “ኦሮሚያ” የሚለውን በታሪክም በተረትም የማይታወቅ የሕልም ዓለም ክልል ስያሜ ደግሞ በዳቦ ስምነት ያሸከማቸው አስመሮም ለገሰ የተባለው የእኛው ዩኒቨርሲቲ ውጤት ነው። በነገራችን ላይ የአስመሮም ለገሰ የገዳሥርዓት መጽሐፍ እስኪወጣ ድረስ ኦሮሚያ የሚባል ቃል አላውቅም ነበር። እንደ ነገሩ ደግሞ መጽሐፍ አገላባጭ ሰው ነኝ፥ እላለሁ።
የኢትዮጵያ የፖለቲካ መድረክ-ይልቁንም መንግሥታዊው መድረክና አጀንዳ የፀረ አንድነቱ አቋም ማራገቢያ እንደ መሆኑ አገሪቱን ወደ ማፍረስ እየረሸጋገሩም ይመስላል። ለሱዳን፣ ለሳዑዲ፣ ለሕንድ፣ ለቻይና፣ ለፓኪስታንና ዶላር ላለው ሁሉ ተከፋፍሎ የተረፈውን ማለቴ ነው። ከዚህ መሠረትነት በመነሳት የሺህ ዘመናት ሥልጣኔ የነበረው የኦሮሚያ በአማሮች ተወርሮ “ኢትዮጵያ” የተፈጠረችው ከአንድ መቶ ዓመታት ወዲህ በዚያ መንግስት ፍራሽ ላይ ነው እየተባልን ነው። የዜጐች፣ የታሪክ ተመራማሪዎች ዝምታ ለተረትና ለቧልት መፈጠር፣ ለልብ ወለድ ታሪክ መፈብረክ አስተዋጽዖ አድርጐአል። ኦሮሞው ኅብረተሰብ (በብዙዎች አካባቢዎች- ለምሳሌ በወሎ ወዘተ ጋላ ማለት ስድብ ሳይሆን የተከበረና ትርጉሙም ትልቅ ማለት ነው) የዚህ አገር ታሪክ ተጋሪ፣ ፈጣሪና በግንባር ቀደምም እንደ አገሪቱ ዳር ድንበር ተከላካይና መከታ ሆኖ የቆየ ነው። አንዲት የምኒልክ ስንኝ በማስታወሻነት ከእናንተ ጋር ባቆይስ? እነሆ!
“ጐበና ጐበና ጐበና የኔ
የጦር ንጉሥ አንተ ያገር ንጉሥ እኔ” አዳዲሱ ድርሳናቸው ከዚህ ሐቅ ጋር የሚጋጭባቸው ደራስያን “አዳዲስ ታሪክ የመጻፍን የአሸናፊዎች አንበሶችን ሚና” ይዘዋል። እኛም ማፈሪያዎች እነሱም ማፈሪያዎች ነን። ይህን እንቀበል!
ስለ ጥቁሩ ሰው
ወደ ሌላ ከመሻገሬ በፊት ከምኒልክ የተለያዩ ጠቅላይ ገዢዎች መካከል ዋነኞቹ (ሦስቱ) ስለ አገርና ስለ ምኒልክ የነበራቸውን ቁምነገሮች ለማንሳት እወድዳለሁ፤
“ምኒልክ ትንሽዋን ወላይታ ወስዶ ትልቂቱ ኢትዮጵያን ሰጠኝ። በእውነት ምኒልክ የእኔም የኢትዮጵያም አባት ነው። – ካዎ ጦና ጋጋ – የመላው ወላይታ ርእሰ መሳፍንት ልጅ እያሱ ቀድሞ ኩምሳ ሞረዳ ይባሉ የነበሩትን የደጃች ገብረእግዚአብሔር ሞረዳን ልጅ ለማግባት ጥያቄ ሲያቀርቡላቸው – “ ምነው! ምነው ጌታዬ! እኔና እርስዎ ኮ ወንድማማች ነን። እኔ በመንፈስ ከአጤ ምኒልክ ተወልጃለሁ (አበልጅ) ስለዚህ እርስዎና እኔ ወንድማማች ነን። የእኔን ልጅ ሊያገቡ አይችሉም። ( አንዳንድ የወለጋ አረጋውያን በዚህ ላይ ሲጨምሩ ሰምቻለሁ። ተጨማሪው ቃል “ሲሆን ባል ሲመጣለት አባት ሆነው የሚለመኑ፣ ቆመው የሚድሩ መሆን ይገባዎታል”)
የደጃዝማች አባ ጅፋር አባ ጆብር (የከፋው ገዥ) ዘመድ የሆነ አንድ ሰው ዘወትር ይሹሙኝ እያለ ደጅ ይጠናቸው ነበር ይባላል። እንዲያውም አንድ ቀን እጅግ አምርሮ “ለመሆኑ እነዚህ ለሹመት ያበቁአቸው ሰዎች ከእኔ ይቀርቡዎታልን? ለእኔ አንድ የሹመት ቦታ አጥተው ነው?” ይላቸዋል።
አባ ጅፋር በተለመደው ስል አነጋገራቸው “የሕዝብ አደራን በተመለከተ ምኒልክ እጄን ይዞ ነው የነገረኝ። ያ ባይሆን ኖሮ እኔ እዚህ አልገኝም ነበር። ምኒልክ እጁን ይዞ “ሹመት የሕዝብ ነው- ሹመት ሺህ ሞት ነው” ብሎናል። ወንድሜ! ወደ ሥልጣን የገቡት እንዴት በነፃነት እንውጣ እያሉ ይጨነቃሉ። ይህንን የማያውቁ ደግሞ እየዘለሉ መግባት ይመኛሉ። እንድታውቅልኝ የምመኘው ከዓለም መንግስታት እኩል ያደረገን ምኒልክ አደራ ከባድ መሆኑን ነው።”
በነገራችን ላይ አጤ ምኒልክ ዘወትር ምሳና ራት ሲበሉ አብረዋቸው ማዕድ የሚቀርቡ (ሁል ጊዜ) ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ፣ ደጃዝማች ወልደሚካኤል ጉዲሳ (የአጤ ኅይለሥላሴ አያት)፣ ፊታውራሪ ቱሉ፣ አፈ ንጉሥ በዳኔና ብላታ አቲከም ነበሩ።
በአንድ ነጥብ እንለያይ። አጤ ምኒልክ በአንድነት አሰባሳቢነትና ተበታትና የቆየች አገራቸውን ወደ አንድ ኅብረት በማምጣት ረገድ የየአካባቢው መሪዎችን ትብብር በግድን በውድም ተቀዳጅተዋል። ስለዚህም በወለጋ ደጃዝማች ገብረ እግዚአብሔር፣ በከፋ ደጃዝማች አባጅፋር፣ በወላይታ ካዎ ጦና ጋጋ አካባቢያቸውን ይዘው፣ የውስጥ አስተዳደራቸውን አደራጅተው ሕዝቡን ይመሩ ነበር። ይሁንና በአርሲ በኩል ለጊዜው ሕዝብ የሚቀበለው ጐላ ያለ ተወላጅ በመታጣቱ አጐታቸው ራስ ዳርጌ ተመደቡ። ራስ ዳርጌ ደግሞ እጅግ ሃይማኖተኛ፣ ሕዝቡን በርኅራኄ የሚመለከቱ የአባትነት ተቀባይነት የነበራቸው ስለሆኑ አንዳች ዓይነት ግፍ ለመፈጸም ባሕርያቸው የማይፈቅድላቸው ሰው ነበሩ። እንግዲህ “አጤ ምኒልክ ጡት አስቆረጡ” የሚባለው አነጋገር አርሲ ውስጥ መሆኑ ነው። ማንም እንደሚገምተው ጡት የመቁረጥ የአረመኔ ተግባር የአማራ ባሕርይም የክርስቲያን ሕዝብም ተግባር አይደለም። በአንጻሩ እነ አባ ባሕርይና ሌሎችም ሥፍር ቁጥር የሌላቸው የታሪክ ጸሐፊዎችም ለአካለ መጠን የደረሰ አንድ ኦሮሞ ጐልማሳ ከማግባቱ በፊት ብልት እስከ መስለብ፣ ጡት እስከ መቁረጥ የደረሰ “ጀብድ” መቁጠር መቻል አለበት፥ ይሉናል። ይኸም የትናንት ታሪክ ነው።
ለማንኛውም ተረት እየፈጠሩ ታሪክ፣ ድርሳን እየጻፉ በሕዝብ ዴሞክራሲ ስም ወደ ኋላ እየሄዱ የአገር ጊዜና ዕድሜ ከማባከን ይልቅ ጥላቻን ቀብረን፣ ፍቅርንና አንድነትን አንግበን ሰላም የተጠማችውን አገር ወደ ሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ማሸጋገር አይበጅም ኖሮአል? ዓለም እየታዘበን አይደለምን? ምን ይሁን ነው የምንለው?
በሕብረተሰብ ትክክለኛ አመራር ባሕርይ መንጸባረቅ ያለበት አንድ ክስተት “የነገው ከዛሬው” የተሻለ፣ ብሩሕ፣ አሰባሳቢ፣ እኩልነት የዳበረበት፣ ነፃነት የከበረበት መሆን አለበት። ያለፈው ጓዝና ጉዝጓዝ እንደ ጸሐይ ማብራት የሚገባውን “ነገ”ን በጨለማማ ገጽታው ሊያደበዝዘው አይገባም። ከትናንትና ከዛሬው ይልቅ “በነገው” ተስፋና አለኝታ መጣል ይገባናል። እንዲያም ቢባል ከትናንቱ ብሔራዊ ውርስና ቅርስ -ከትናንቱ የእድገትና የአንድነት መሠረት መካከል- ምኑም ማናምኑም በዛሬና በነገው ቀጣይ ታሪካችን ውስጥ ሥፍራ ሊኖረው አይገባም አይባልም። ታሪካችንም ሆነ የነገው “ጸጋችን” ምንም ዓይነት ተቀባይነት አይኖረውም አይባል። አያቱንና አባቱን የማያውቅ ትውልድ በፈንታው ለነገው ትውልድ አባትነትና አያትነት አይሰማውም። አዎን የምንኰራባቸው አባቶችና እናቶች አያቶችና ቅም አያቶች ያሉንን ያህል አሳፋሪዎች፣ ፈሪዎችና ደካሞች፣ መልቲዎችና ሰነፎች የሆኑ ዜጐችም ነበሩብን። አሉብንም።
እነዚህን ማወቁ-ታሪካችንን ጠንቅቀን መረዳቱ፣ ጀግንነትን ለማደስና ከቶውንም ያንን አዳብረን የዓለም “ጨው” እስከምንባል ድረስ ለመጓዝ ዓለማቀፋዊነት መሠረት ይሆነናል። አፍሪካውያን ብቻ ሳይሆን፣ ጥቁር ዓለምንም ብቻ ሳይሆን- የዓለምን ነፃነት ወዳጅና አክባሪ ሕዝቦች ሁሉ የሚያደንቁት “ምኒልክ” ከዚች አገር የጐን አጥንት የተከፈለ ነው። አንድን አገር ታላቅና ገናና፣ የተከበረችና የታፈረች የሚያደርጉአት ሕዝብዋ ሲሆኑ ለዚያ ሁሉ ታሪካዊ ሥፍራ ተቀዳጅነት የሚያስፈልጉ መሪዎች ናቸው። ኢትዮጵያ ውስጥ በመሪነት የተነሡትን ልዩ ልዩ ነገሥታትና የዛሬዎችንም አምላክ ለቅጣት የሰጠንን ጨምሮ- ለኢትዮጵያ አንዳች ክብር ያመጣውን ዋነኛ ሰው ለማግኘት ብዙ ማሰስ አስፈላጊ አይደለም። የዶክተር ሥርግው ሀብለ ሥላሴን “አጤ ምኒልክ” ማንበብ የአሰሳው ፍጻሜ ሊሆን ይችላል። ደራሲው በዚህ መጽሐፍ ከሳባ ንግስት አንስቶ እስከ ቀዳማዊ ኅይለሥላሴ ድረስ ይዘልቃል። ለዚህ አገር ታዋቂነት- ይልቁንም ዳር ድንበርዋንና ነፃነትዋን በማስከበር ረገድ ድንቅ አስተዋጽዖ ያደረጉ፣ በመንፈሳዊና ቁሳዊ ሥልጣኔ ታስደመሙ መሪዎችን ታሪክ ለላንቲካ ያቀርባል። ከሙሉው- ከዚያ ሁሉ ጀግናም ሆነ ሰነፍ መሪ መሐል አንድ ሰው ነጥሮ ይወጣል። በፀረ አንድነት ኅይልነት ጸንቶ ያለው ወያኔ ይንጨርጨር እንጂ- ወያኔና ሻዕቢያ የፈጠሩአቸው ትንንሽ ጩዋሒዎች ይንጨርጨሩ እንጂ ሰውዬው ወጣቱ አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን “ጥቁሩ ሰው” የሚለው ነው።
ይቺ አገር በነፃነት የተፀነሱ፣ በነፃነት ያደጉና ድሀም ቢሆኑ በነፃነት የሚራመዱ ዜጐች እናት ናት። ያቺ አገርና ሕዝብዋ ከምን ጊዜውም በላይ ያልተጠናቀቀ ብሔራዊ ዕዳ፣ ለትውልዶች የሚጠቅም ቅርስ ለማቆየት በጥድፊያ ላይ ያሉ ወገኖች እናት ናት። እዚህ መሬት ማሕፀን ውስጥ የተከበሩ ጀግኖች ተኝተዋል። በዚች ዛሬ የታሪክ መጫወቻ በሆነች አገር ማኅፀን ውስጥ ታላላቅ ጀብዱ ፈፅመው ያንቀላፉ፣ በልዩ ልዩ ሙያና በፍልስፍናም ጭምር ልቀው ያላቁን ታላላቅ ነፍሳት የእናት አገራቸው እቅፍ ሞቆአቸው ተኝተዋል። ዓምደ ጽዮን፣ ያሬድ፣ በካፋ፣ ቴዎድሮስ፣ ዮሐንስ፣ ምኒልክ፣ ሀብተ ጊዮርጊስ፣ አሉላ፣ አብዲሳ አጋ፣ በላይ ዘለቀ፣…የተኙባትና እረፍት ላይ ስላሉም መሬቲቱ በጥንቃቄ መረገጥ ያለባት ናት። እነሱን ያህል ለመሥራት ያልቻልን ሰነፎች እንደ መሆናችን ቆምብለን ራሳችንን መርገምም የሚገባን ነን። ይኽ ሁሉ የወያኔ ልዑካን ጫጫታ አያሳፍርም? ይኸ ድምፅ ከየት መጣ? ወሮበሎች አያሰኝንምን? ስድ አደግ ማለት- የእምነት ድህነት ማለት- የሕሊና ባዶነት ማለት- የአቋም ምስኪንነት ማለት ምን ማለት ነው? ይኸው በአደባባይ እየታየ ነው። (በዚህ ጉዳይ ላይ እመለስበታለሁ)

አስገራሚው የሳውዲው “ኮራጅ ” አባት ምክር እና የኢትዮጵያ ሰርከስ መስራች በሳውዲው ስደት ! – ነቢዩ ሲራክ / የካቲት 2006 ዓም

አስገራሚው የሳውዲው “ኮራጅ ” አባት ምክር
ነገሩ እንዲህ ነው …ከ20 ዓመት በፊት ሳውዲው ወጣት ራሱን ለሁለተኛ ደረጃ ፈተና ከማዘጋጀት ይልቅ በረቀቀ መንገድ ለፈተናው መልስ የሚሆነውን ማጭበርበሪያ የመልስ ወረቀት አዘጋጅቶ ለፈተና ይቀርባል። ፈተናውን በረቀቀ መንገድ አጭበረብሮ ሰርቶታልና ፈተናውን በተገቢ ውጤት አልፎ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ለማለፍ በቃ ! ከዚያም በታዋቂው ዩኒቨርሲቲ ትምህርቱን ተከታትሎ ይመረቃል። ይህ ሁሉ አልፎ ስራ ይዞ እና ጎጆ ቀልሶ ለወግ ለማዕረግ በቃ ! ከጎጆም አልፎ የሰመረው ህይወቱ የልጆች አባት እስከ መሆን ታደለ !
በያዝነው ሳምንት የድሮው ተማሪና የዛሬው አባወራ ጆሮውን ያልተለመደና የማያውቀው ህመም ያሰቃየው ገባ ። ወደ ሃኪም ቤት ጎራ በማለት ምርመራ ሲያደርግ ለህምሙ ዋና ምክንያት በጀሮው ውስጥ ቁራጭ ወረቀት እንደሆነ የሚያስረዳው አስገራሚው ውጤት ተነገረው … አረጋዊው አባት በወጣትነት እድሜው ተግቶ በማጥናት ለፈተና ቀርቦ ማለፍ ሲገባው አስነዋሪ የማጭበርበር ድርጊት መፈጸሙን እያስታወሰ አልተደሰተም ፣ አዘነ እንጅ ! ዛሬ ለማጭበርበሩ የተጠቀመበትን ወረቀት በጀሮው እንዴት ሊያስገባው እንደቻለ ማመን ቢያዳግትም ከ20 አመታት በፊት ለኩረጃ እና ለማጭበርብር የተጠቀመበት ወረቀት በቀዶ ጥገና ከጀሮው እንዲወጣ መደረጉ አስገራሚውን ዜና እየተቀባበሉ እየዘገቡ ካሉት የአረብ መገናኛ ብዙሃን ለመረዳት ችያለሁ … ! ከሁሉም የሚያስገርም የሚያስደስተው በሰራው ስራ የሚያፍር እንጅ የማይኮራው አባት ልጆቹንና ወጣቶችን ሲመክር “ልጆቸ ሆይ ፈተና ለማለፍ አታጭበርብሩ! ” ማለቱ ተጠቅሷል ። የትናንቱ ተማሪ የዛሬው አባወራ ሳውዲው አባት በሰራው ስራ ተጸጽቶ ቀሪውን ለመምከር ወደ አደባባይ መውጣቱ ቢያስደስተኝ በዝንቅ መረጃየ ስር መረጃውን ላካፍላችሁ ፈቀድኩ !
ሳውዲውን አባት መልካም ምክር ካነሳሁ አይቀር ሰሞነኛ የማለዳ ወጌ እንግዳ ለማድረግ ስለፈቀድኩት አንድ ከ20 አመት በፊት በኢትዮጵያ ሰማይ ስር ባንድ ወቅት አንቱ የተባለ ስም ስለነበረው ብርቱ ወንድም ላጫውታችሁ … አብደላ አህመድ ኦመር ይባላል ። ቀዳሚው የኢትዮጵያን ሰርከስ መስራች ነው ። በስራው ቻይናን ጨምሮ በርካታ ሃገራትን ጎብኝቷል … ብርቱ ስፖርተኛ ከመሆን ባለፈ አንድን ሙያ ልያዝ ብሎ ከተነሳ በፍጥነት ክህሎትን የማዳበር ልዩ ተፈጥሮ ያለው ወንድም እንደሆነ ሰምቻለሁ ! ዛሬ በእርግጠኝነት መናገር የምችለው ነገር ቢኖር ብዙሃን ኢትዮጵያውያን የኢትዮጵያ ሰርከስ መስራች ማን እንደሆነና የት እንዳለ የሚያውቁ አይመስለኝም ! … ብርቱው የቀድሞው ስፖርተኛ እና የሰርከሱ መስራች አብደላ ግን ሳውዲ አረቢያ ጅዳ ትዳር መስርቶ እና ልጆች ወላልዶ በስደት ህይዎትን በመግፋት ላይ ነው ።
አብደላን ሳላውቀው… ላውቀው!
መልከ መልካምና ደልዳላ ተክለ ቁመና ካለው ወንድም ጋር ለአመታት ልጆቸን በማስተምርበት በጅዳ የኢትዮጵያውያን አለም አቀፍ ትምህርት ቤት እንተያያለን ፣ ግን አንተዋወቅም ። በአንድ ወቅት ከአንድ ወዳጀ ጋር የትምህርት መለቀቂያ ሰአት ደርሶ ልጆቻችን ስንጠባበቅ አብደላ ሰላምታ አቅርቦልን አለፈ … አብደላን አንድ ወዳጀ ያውቀው ነበርና እንዲህ አለኝ … ” ለመሆኑ ይህን ሰው ማን እንደሆነ ታውቀዋለህ? ” ሲል ጠየቀኝ አረ አላውቀውም ስል መለስኩለት … ” አየህ ሳውዲ ያልያዘችው ፣ ያላቀፈችው ሃበሻ አይነት የለም፣ አንተ ደግሞ የሩቅ የሩቁን ፣ በበርሃ የምታገኘው ዘፋኝና ግፉዕ ተምር ለቃሚ ግመል ጠባቂ እህቶችን እንጅ እንዲህ በቅርብ ያለውን አየታይህም ” ሲል የመሰለውን አስተያየት ሲሰነዝር እንደ መቀለድ እያለ በፈገግታ ተሞልቶ ነበር እና እኔም እንደመሳቅ አልኩ ! ወዳጀ ወጉን ቀጠለ …
” አንደላን በትንሹ ከአስራ አምስት አመት በላይ አውቀዋለሁ። ስፖርተኛ ፣ አስማተኛ ፣ የስነ ጽሁፍ ክህሎትን የተካነ በሁሉም የሙያ መስክ የምታገኘው ሰው ነው። ዛሬ እንዲህ አንገቱን ደፍቶ ፣ ሰውነቱ ገዝፎ ስታየው የዋዛ አይምሰልህ (ፈገግ ብሎ) ፣ ከበርካታ አመታት በፊት ታዋቂው የአካል እንቅስቃሴ አሰልጣኝ ግርማ ቸሩ ለአመታት በአሰልጣኝነት ይሰራባቸው ከነበሩ በወቅቱ ታዋቂ ቱጃር በነበሩት የሸህ አልዙማን ስራ ተሰናብቶ ሳውዲን ሲለቅ የተተካው ፈርጣማው ጎልማሳ አብደላ ነበር ። ከዚያም የባለጸጎቹን ቤተሰቦች በአካል እንቅስቃሴ አሰልጣኝነት እና በልዩ ጥበቃ ለአመታት በመስራት ያልዞረበት ሃገር የለም ። በአዕምሮው በሳል ፣ በአካል ፈርጣማ ስፖርተኛ ነው ። አየህ ነቢዩ በሳውዲ ስደት የታቀፈው ግፉአን እህቶችና ወንድሞች ብቻ አይደሉም። እንዲህ አይነት ባለሙያም ሳውዲ ውስጥ ይኖራል። ታሪኩን ለመናገር ፈቃደኛ ከሆነ ለቀረው ትውልድ አስተማሪ ነውና አንድ ቀን አስተዋውቅህና እንዲያጫውትህ አደርጋለሁ! ” አለኝ ። … አብደላን ሊያገናኘኝ ከአንድ አመት በፊት እንዲህ ቃል የገባልኝ ቅን አሳቢ ወንድም ግን ዛሬ ከአካባቢው የለም … ኑሮው ቢከብደው ቤተሰቦቹን ይዞ እና ጥሪቱን አጠረቃቅሞ የአቅሙን ያህል ለመስራት ሃገር ቤት ገብቷል … ካንድም ሁለት ሶስት ጊዜ በፊስ ቡኩ መስመር ብንገናኝም ሃገር ገብቶ የሚይዝ የሚጨብጠው እንዳጣ መረጃ የሚያቀብለኝን ወንድም” አብደላን አገናኘኝ?” ብየ ማስቸገሩ ከብዶኝ መክረሙ እውነት ነው! መቸም ዘንድሮ መንገድና ፊስ ቡክ የማያገናኘው የለም ፣ የኢትዮጵያውን ሰርከስ መስራች በቀጭኑ የስልክ መስመር በሌላ ጉዳይ አግኝቸው ስናወጋ ማንነቱን ሲያጫውተኝ ማመን አልቻልኩም ። ፎቶዎችን ፣ ሰነዶችን በመረጃ ማስረጃነት ሲያጋራኝ ግን የማይታመነውን አጋጣሚ ለማመን ተገደድኩ ! ከወንድም አብደላ ጋር ልንገናኝ ቀጠሮ ይዘናል ። … በቀይ ባህር ዳርቻዎች ከቤተሰቦቻችን ጋር ተገናኝተን ፣ ልጆቻችን ሲጨዋወቱ ነፋሻውን የባህር አየር እየማግን የኢትዮጵያ ሰርከስ መስራቹን የአብደላን ዠንጉርጉር ህይወት እኔ እየጠየቅኩ እሱ በትዝታ እየነጎደ እስኪያወራኝ ቸኩያለሁ …
መልካም ቀን
ነቢዩ ሲራክ / የካቲት 2006 ዓም

አሥራ አንድ ሰዓታት የፈጀው ክርክር – ሃብታሙ አያሌው (የአንድነት ፓርቲ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ)

ክፍል አንድ
በቀናት አቆጣጠር ሰባተኛው እረድፍ በምትይዘው በዕለተ ቅዳሜ ከዚህ ቀደም በጸረ ሽብር አዋጁ ዙሪያ ካደረግነው የተሟሟቀ ክርክር በኋላ ከገዥ ፓርቲ ጋር በሃሳብ ክርክር ለ11 ሰዓታት የተሟገትነው ቅዳሜ ጥር 17 ቀን 2006 ዓ.ም ባለፈው ሳምንት ነበር፡፡ ይህ መድረክ የተዘጋጀው በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በጋዜጠኝነት እና ኮሚዩኒኬሽን የድህረ ምረቃ ተመራቂ ተማሪዎች ከትምህርት ቤቱ ጋር በመተባበር እንደነበረ ከደረሰን የመጥሪያ ደብዳቤ ለመገንዘብ ችለናል፡፡
በዚህ ወቅት በዚህ ጉዳይ ሲምፖዚየም ማዘጋጀት ያስፈለገበት ምክንያት ምንድነው ? ለሚለው ጥያቄያችን የሲምፖዚየሙ ርዕስ ግልፅ ምላሽ ነበረው፡፡ ‹‹ የዴሚክራሲያዊ ልማታዊ መንግስት እና የመገናኛ ብዙኃን ግንኙነት›› (Nexus) ማጠንጠኛው ነበር፡፡
የኢህአዴግ መንግስት ‹‹በአቢዮታዊ ዴሞክራሲ ›› ፍልስፍና (ፍልስፍና ሊባል ከቻለ) እስከ 1991 ዓ.ም ከተንገዛገዘ በኋላ የባድሜውን ጦርነት እና የህወኃትን መሰንጠቅ ተከትሎ የፓርቲው የኃይል አሰላለፍ ሲቀየር ተቀጥላ ልማታዊ የሚለው ሥያሜ ጎላ ያለ ስፍራ እንዲያዝ መድጉ አይዘነጋም፡፡
ልማታዊ መንግስት ሲሉ አቢዮታዊ ዴሞክራሲ የሚለውን ስያሜ ለአንጃው ለመተው የፈለጉት አቶ መለስ ይህንን መጠሪያ የገነገነ ጥላታቸውን በመበታተን ተሸንፈው ከቆሙበት ጥግ ወደ መሃል ለመግባት ወሳኝ ብልሃት አድርገውት ነበር ማለት ይቻላል፡፡ አቶ መለስ ለኤርትራ መንግስት ያሰዳዩ የነበረው ከፍተኛ ወገንተኝነት ኢትዮጵያን ያለወደብ ከማስቀረት ተሸግሮ በኢትዮጵያ ምርቶች ኤርትራ በአለም የንግድ ገበያ ስሟ መጠራት መጀመሩ፤ በኢትዮጵያ ብር እየተገበያየች የዶላር ክምችቷን ከፍ ማድረጓ እና በወጪ እና ገቢ ሸቀጦች እረገድም በምንም ዓይነት የታክስ ሥርዓት አለማለፏ እና የመሳሰሉት አንደኛው የኩርፊያ መሰረት እንደነበረ ይታወቃል፡፡
ይሁን እንጂ የአንደኛው የሃሳብ የበላይነት ብዙ እርቀት ሳይሔድ በቀጭን ትዕዛዝ ጦርነቱን ያስቆሙት አቶ መለስ መንግስታቸው ልማታዊ መሆን ሲገባው ጦረኝነትን እንደመረጠ እና እንደበሰበሰ በመግለፅ የታይላንድ፤ ታይዋን እና ደቡብ ኮርያን መንግስታት ሥርእት በመተንተን ከአንጃው ካምፕ ብዙዎችን ማረኩ፡፡ ከዚያም ያልተደራጁ እና ስልት አልባ የነበሩ ተቃዋሚዎቻቸውን በታትነው ጥቂቶችን ዘብጥያ በመጣል አሸናፊ ሆነው ብቅ ያሉበት ነበር፡፡
‹ልማታዊ መንግስት›
አቶ መለስ ልማታዊ መንግስት ሲሉ መከራከሪያቸው ‹‹በውቅቱ የኤርትራ ወታደሮች የኢትዮጵያን ሉዓላዊ ግዛት ድፍረው በገዛ ምድራችን ምሽግ ቆፍረው ሊወጉን እየተዘጋጁ እንደነበረ ብናውቀውም ወደ ጦርነት ያልሄድነው ልማት ይቀድማል ከሚል ትክክለኛ አስተሳሰብ ነው፡፡›› የሚል ነበር፡፡ ይህ ግን ጥሩ የማደናገሪያ ስልት እንኳ መምረጥ እንዳልቻሉ የሚያሳይ እንጂ የሃሳብ የበላይነት እንደነበራቸው የሚያመላክት አልነበረም፡፡ አንደኛ በወቅቱ ምንም አይነት የልማት አጀንዳ ያልነበራቸው መሆኑ፤ በሌላ በኩል የሀገር ሉዓላዊ ድንበር ተደፍሮ፤ የሌላበ ሀገር ሰራዊት ምሽግ እየቆፈረበት ልማት ስላሳሰበኝ ሀገር አልጠብቅም ማለት ጀነራል ሳሞራን እና እነአባዱላ ገመዳን ካልሆነ በቀር የኢትዮጵያን ህዝብ የሚያሳምን ሃሳብ አይደለም፡፡
የምንረዳው ቁምነገር ቢኖር እንደ ሀገር ለኢትዮጵያ ከነበራቸው የተንሸዋረረ አመለካከት እና ከያዙት የተሳሳተ አቋም በመነሳት በጫካ ውላቸው መሰረት ኤርትራ ራሷን የቻለች እና የበለጸገች ሀገር እንድትሆን እንደ አቶ ኢሳይያስ ምኞት ‹‹በ10 ዓመታት ውስጥ ኤርትራ አፍሪካዊዋ ሲንጋፖር ትሆናለች፡፡›› ከሚለው ቅዠት ጋር እየቃዡ የነበረ መሆኑን ነው፡፡
ለኢትዮጵያ ሉዓላዊ ግዛት፤ ለታሪክ እና ለብሔራዊ አንድነት ግድ የማይሰጣቸው አቶ መለስ ጦርነቱ ተጀምሮ በኤርትራ ላይ ጉዳት እንዳይደርስ የተከላከሉበት ‹‹የልማታዊ መንግስት የፖለቲካ ኢኮኖሚ ጉዳይ›› የሙት መንፈሳቸው እንደገና በያዝነው የ2006 ዓም የመጀመሪያ መንፈቅ አጀንዳ አድርጎታል፡፡ ይህ ወቅት በሙት መንፈሳቸው የሚመራው የኃይለማርያም መንግስት ታሪካዊ የሆኑ የኢትዮጵያ ግዛቶችን ሰቲት ሑመራን፤ ምዕራብ አርማጭሆን እና ቋራን ለሱዳን አሳልፈው በመስጠት ድነበር ለማካለል እያሴሩ ያሉበት ወቅት እንደሆነ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡
የልማታዊ መንግስት አጀንዳ የባድሜን መሬት ለመስጠት በተሰላ ጊዜ ከገነነ በኋላ የፊት ሌቱን ገፅ ለቆ ቢቆይም የጎንደርን መሬት ለመስጠት ሲታሰብ እንደገና አብይ አጀንዳ ሆኖ ብቅ በሏል፡፡ ጥር 17 ቀን በኢንተር ኮንትኔንታል የተካሄደው ሲምፖዚየምም፤ የዚሁ የልማታዊ መንግስት አጀንዳ ማደናገርያ ክፍል አንድ ሊባል ይችላል፡፡
አሥራ አንድ ሰዓት የፈጀው ውይይት
ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት ገደማ የጀመረው ውይይት የተጠናቀቅ ከምስቱ 1፡35 ደቂቃ ነበር፡፡ ከፍተኛ ምስጋን የሚገባቸው የድረህረ ምረቃ ተመራቂ ተማሪዎች ካዘጋጁት መድረክ በስተጀርባ የተደገሰውን የፖለቲካ ዓላም ግን በግልፅ የተገነዘቡት አይመስልም፡፡ በፍጸም ገለልተኝነት የሃሳብ ክርክር እንዲደረግ የተቻላቸው ሁሉ ሲያደርጉ ተገንዝቤያለሁ፡፡
በውይይቱ ማጠናቀቂያም የጋበዟቸው የገዥው ፓርቲ ሰዎች አጀንዳውን ወደ ፖለቲካ ጎትተው ለፖሊሲ ስርጸት ለመጠቀም መሞከራቸው ተገቢ እንዳልነበረ በድፍረት አስተያየት ሰጥተውበታል፡፡ ከገዥው ፓርቲ፤ ከተቃዋሚ ፓርቲዎች፤ ከዩኒቨርስቲ መምህራን ከመገናኛ ብዜሃን አካላት እና ሌሎች ምሁራን መካከል ጥሪ ተደርጎላቸው እንደተገኙ በተገለጸው በዚህ መድረክ ከገዥው ፓርቲ አቶ ሽመልስ ከማል፤ አቶ ዛድቅ አብርሃ፤ አቦይ ስብሃትን እና በስም የማላውቃቸውን አስተውያለሁ፡፡ ከምሁራን መካከል ዶክተር ዳኛቸው አሰፋ፤ ዶክተር ያዕቆብ ኃ/ማርያም ፤ ዶክትር ነጋሶ ጊዳዳ፤ ዶክተር በድሉ ዋቅጅራ ሲሆኑ በስም የማላውቃቸው ሊኖሩ እንደሚችሉ እገምታሉ፡፡
በእኔ ግምት በጋዜጠኝነት እና ኮሚዩኒኬሽን ድህረ ምረቃ ተማሪዎች ሲምፖዚየሙን አዘጋጀን ካሉበት አላማ አንጻር በዶክተር አብዲሳ ዘርዓይ {Media in Democratic Developmental State the Ethiopian Quandary } በአቶ ታምራት ኃ/ጊዮርጊስ The concept of democratic developmental state vis-a- vis The Ethiopian constitution እና በአቶ ሙሼ ሰሙ freedom of the press in the environment of a democratic developmental state የሚሉት ሞያዊ ዝንባሌ የታየባቸው academic discourse ከሚባሉት የሚመደቡ ነበሩ ማለት ይቻላል፡፡
በአንጻሩ በአቶ ወልዱ ይምሰል እና በአቶ ዛድቅ አብርሃ የቀረቡት ደግሞ ከተማሪዎቹ ሃሳብ በስተጀርባ የሙት መንፈስን ሃሳብ ለመጫን ያለሙ political discourse ነበሩ፡፡ በዚህ ሲምፖዚየም በልማታዊ መንግስት ፅንሰ ሃሳብ እና በሚድያ ነጻነት ዙሪያ ሰፊ ክርክ ተደርጓል፡፡ በአቶ ታምራት ኃይለጊዮርጊስ የቀረበው ጥናት በኢትዮጵያ የሚዲያ ነጻነት አለመኖሩ እና ይልቁንም በህገ መንግስት የተሰጡ የሚዲያ ነጻነቶችን ገዥው መንግስት በሌሎች ህጎች እንዳፈናቸው ዝርዝር ማብራሪያ ቀርቦበታል፡፡ እንደ አቶ ታምራት ገለጻ የኢትዮጵያ ህገ-መንግስት የቡድን መብት ሲል ካስቀመጣቸው ጥቂት ተቀባይነት የሌላቸው አንቀጾች በቀር ጥሩ እና ሊበራል አስተሳሰብን ከፍ የሚያደርግ ነው ሲል መከራከሪያ አቅርበውታል፡፡ ይህ ሃሳብ ከገዥው ፓርቲ ተወካይ ከአቶ ዛድቅ ቁጣ የተቀላቀለበት ምላሽ የተሰጠበት ሲሆን አቶ ዛድቅ ሊበራል ሳይሆን ህገ መንግስታችን ካፒታሊስት ሥርዓት የሚገነባ ነው በማለት ካፒታሊዝም ለሊበራሊዝም ተቃርና እንደ ሆነ አድርገው ሲከራከሩ ተገርመን አስተውለናል፡፡ (እንደ አቶ ዛድቅ ገለጻ ከሆነ አዲሱን ልማታዊ መንግስት ለማነበር ካፒታሊስቱን ህገ መንግስት መሻር ግድ ሊለን ነው፡፡)
በዶክተር አብዲሳ ዘርዓይ ከተሰነዘሩ ሃሳቦች መካከል በ1980ዎቹ አካባቢ የታየው የሚድያ ነጻነት ክፉኛ እንደተመታ እና በአሁኑ ወቅት ያለው የሚድያ ነጻነት ደረጃ እጅግ አሳሳቢ እንደሆነ በጥናታቸው አስምረዋል፡፡ በዶክተሩ ጥናት ላይ መከራከሪያ የሚመስል ሃሳብ በማቅረብ አጸፋ ያሉትን ያቀረቡት የፋነው ስራስኪያጅ አቶ ወልዱ በበኩላቸው በ1980ዎቹ የነበረው የሚድያ ነጻነት መረን የለቀቀ እና በጦርነት የተሸነፈው የደርግ ኃይል በሚድያ ጦርነት የጀመረበት ወቅት ነበር ሲሉ ተከራክረዋል፡፡
በዚህ ወቅት ከፍተኛ ክርክር የተጀመረው በዚህ ጽሑፍ ጸሐፊ እና በኢህአዴግ ተወካዮች መካከል ነበር፡፡ የተበተነው የደርግ ሰራዊት በእጁላይ በነበረው መሳሪያ በሀገር እና በህዝብ ላይ ጉዳት ሳያደርስ የኢትዮጵያን የመከላከያ ሰራዊት ጨዋነት ማስመስከሩ ሊያስመሰግነው እንደሚገባ፤ እዚህ ኢህአዴግ እንደሚከሰው ወደ ሚዲያ ጦርነት ሂደው ከነበረም መሳሪያ ጥለው በብዕር ክርክር ፍልሚያ መካፈላቸው ጠላት ሊያሰኛቸው አይገባም ነበር፡፡ ነገሩ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ‹‹ኢህአዴግ አንድን ጋዜጠኛ ከአንድ ባታሊዎን ጦር በላይ የፈራል›› እንዳለው ሆነ እንጂ ፡፡ በአንጻሩ የተበተነው ሰራዊት ወይም የኢሰፓ አመራሮች ሳይሆኑ በሚድያ ሃሳብ ይሰነዝሩ የነበሩት ምሁራን እና የ1960ዎቹ የሃሳብ እኩዮቻቸው እንደነበሩ መከራከሪያ ቀርቧል፡፡
በተለይም ከዚህ ክርክር የተረዳነው ቢኖር ገና በጠዋቱ ኢህአዴግ በሚዲያ ላይ የያዘው የተዛባ አመለካከት ከፍተኛ መሆኑን እና የተለየ አስተሳሰብን በሚድያ ማንጸባረቅ እንደ ወንጀል የሚቆጠጥር ነው፡፡ (በተሻሻለው የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እንደተከሰሰ ልብ ይሏል፡፡) በሲምፖዚየሙ ከፕሬስ ነጻነት አንጻር ክፉኛ የተተቸው የፕሬስ አዋጅ፤ የጸረሽብር አዋጅ፤ እንደተጠበቀ ሆኖ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ሲሻሻል የፕሬስን ጉዳይ በሚመለከት የተካተተው ህግ በሲምፖዚየሙ ትኩረት የሳበ ሆኖ ውሏል፡፡
በወንጀለኛ መቅጫ ህጉ ላይ የሰፈረው ፕሬስን የሚመለከት አንቀጽ ሆን ተብሎ ሚድያውን ለማፈን እና ጋዜጠኞችን ለማሳደድ የተካተተ በግልጽ በህገ መንግስቱ የተቀመጠውን የሚድያ ነጻነት የሚጥስ እና የሚደፈጥጥ ነው፡፡ በሚል መከራከሪያ ቀረበ፡፡ በዚህ ጊዜ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በአይኔ ላይ ውል አለ፡፡ በዚህ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ተወንጅሎ ፍርድ ቤት እየተመላለሰ እንደሆነ አውቃለሁ፡፡ ጥያቄና አስተያየቱም ቁጡነት እና እልህኝነት ይታየበት የነበረውም በዚሁ ምክንያት እንደሆነ ይሰማኛል፡፡
ይህንን የወንጀለኛ መቅጫ ህግ አስመልክቶ የፎርችኑ አቶ ታምራት ህጉ በግልፅ ህገ መንግስቱን የጣሰ እና ተገቢ ያልሆነ ህግ እንደሆነ አስረግጦ ተከራክሯል፡፡ ከሁሉ የሚገርመው ግን ለዚህ ምላሽ የሰጡት የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ሚንስትር ድኤታ አቶ ሽመልስ ከማል ‹‹በእርግጥም የወንጀለኛ መቅጫ ህጉ ላይ ፕሬስን በተመለከተ የተቀመጠው አንቀጽ ከህገ መንግስቱ ጋር የሚቃረን እና ተገቢ ያልሆነ መሆኑን እንደ መንግስትም ተገንዝበናል፡፡ እንደ እኔ ግምት ይህንን ወንጀለኛ መቅጫ ህግ ያሻሻሉ ሰዎች በጭንቅላታቸው ቆመው የሰሩት ይመስለኛል፡፡›› ሲሉ በግርምት አድምጠናል፡፡
በዚህ ጊዜ አቶ ታምራት ኃ/ጊዮርጊስ እንዲህ በማለት ሃሳባቸውን አቅርበው ነበር፡፡ ‹‹ ክቡር ሚነንስትር ድኤታ በእርግጥ ስህተት ነው ባለው በግልዎም እንደ መንግስትም ማመንዎን አደንቃለሁ፡፡ ነገር ግን ይህ ስህተት በህግ አሻሻዮቹ አለማስተዋል እንደተሰራ ማስመሰል ተገቢ አይደለም፡፡ ይህ አንቀጽ ሆን ተብሎ ሚድያውን ለማፈን ዜጎች በህገ መንግስት ያገኙትን መብት ለመንፈግ የወጣ ነው፡፡ በእኔ ግምት ያሻሻሉት በጭንቅላታቸው ስለቆሙ አይመስለኝም፡፡ ዳኞች ይህንን አንቀጽ እየጠቀሱ ዜጎች ታስረዋል፤ ብዙዎች እንዲሰደዱ እንዲንገላቱ ምክንያት ሆኗል……››
በእርግጥ ወንጀለኛ መቅጫ ህጉን ያሻሻሉት በጭንቅላታቸው ስለቆሙ ነው ወይስ የፕሬስ ህግ፤ የጸረሽብር ህግ፤ የሲቪል ማህበራት ህግ ወዘተ…ጭምር ሲረቀቁ አቶ መለስ በአርቃቂዎች ጭንቅላት ላይ ስለቆሙ ? በቀሪዎቹ እና በአወንታዊ ነጥቦች ላይ እመለስበታለሁ፡፡

አንድ የአየር ሃይል ባልደረባ የአርበኞች ግንባርን ተቀላቀለ

 ኢሳት ዜና :-የደብረዘይት አየር ኃይል አባል የነበረው ምክትል መቶ አለቃ ዳንኤል የሽዋስ የኢህአዴግን ስርአትበመቃወም የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊትን መቀላለቀሉን ግንባሩ ለኢሳት በላከው መግለጫ አስታውቋል።
ም/መ/አለቃ ዳንኤል የሽዋስ የ L-39  ስኳድሮን ተዋጊ ጀት አብራሪ እንደነበር መረጃው ያመለክታል።
ም/መ/አ ዳንኤል የሽዋስ “ተቃዋሚዎችን ትደግፋለህ ከእነሱም ጋር የጠበቀ ግኑኝነት አለህ በሚል ምክንያት ተጠርጥሮ ያለምንም ወንጀል ለአምስት ወር ያህል ታስሮ እንደነበርና ከእስር እንደተለቀቀም በደህንነት አባሎች አማካኝነት በአይነ ቁራኛ ክትትል ሲደረግበት ቆይቶ ፣ እንደገና ለ23 ቀናት በደብረዘይት እስር ቤት መታሰሩን፣ገልጿል፡፡ የአየር ሃይል ባልደረባው በዚህ መሃል ከእስር ቤት አምልጦ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊትን መቀላቀሉን” የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
የአየር ሃይሉ ባልደረባ መኮብለሉን በተለመለከተ መንግስት የሰጠው መግለጫ የለም።
ግንባሩ በላከው ሌላ ዜና ደግሞ  በሁመራ አካባቢ  የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ደጋፊዎች ናችሁ በማለት ታስረው በነበሩ 10 ሰዎች ላይ ከ6 ዓመት እስከ 25 ዓመት እንደተፈረደባቸውና  ወደ መቀሌና ሽሬ እስር ቤት እንደተወሰዱ ገልጿል።
አርበኞች ግንባር ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሰሜን ጎንደር አካባቢዎች ወታደራዊ ጥቃቶችን በመፈጸም ላይ ይገኛል።

በ500 ብር ደሞዝ የሚተዳደረው የህወሃት ታጋይ ከ10 ሚሊዮን ብር ያላነሰ ሃብት ማካበቱ ተገለጠ

ኢሳት ዜና :-የደህንነት ሃላፊ ከነበሩት ከአቶ ወልደስላሴ ወልደ ሚካኤል  ጋር በግብረ-አበርነት የተከሰሱት የህወሃት ታጋዮች ከደሞዛቸው ጋር ፈጽሞ የማይመጣጠን ሃብት አግበሰው መገኘታቸው ታውቋል።
በተለያዩ አለመግባባቶች የተነሳ እየተመሰረቱ ያሉ ክሶች የህወሃት ተጋዮች በህገወጥ መንገድ የሰበሰቡትን የሃብት መጠን ለማወቅ እየረዳ መሆኑን የገለጸው ዘጋቢያችን ከአቶ ወልደስላሴ ጋር በግብረ አበርነት የተከሰሱት የህወሃት ታጋዩ የአቶ ወልደስላሴ ወንድም አቶ ዘርአይ ወልደስላሴ የመከላከያ ሚኒስቴርን ሲለቁ በመጨረሻ ይከፈላቸው የነበረው ወርሃዊ ደሞዝ 532 ብር ብቻ እንደነበር አመልክቷል ፡፡  ይሁንና፣ ጸረ-ሙስና ኮሚሽን ባደረገው ማጣራት ግለሰቡ በተለያዩ ባንኮች በስማቸው 5 ሚሊዮን ብር ከማስቀመጣቸውም በተጨማሪ፣ አዲስ አበባ ቤቴል ሆስፒታል አካባቢ በ74 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ግንባታ እያካሄዱ ፣ በአፋር ክልል ደግሞ ከ1 ሚሊዮን 400 መቶ ሽ ብር በላይ በሆነ ወጪ የእርሻ ኢንቨስትምንት እያከናወኑ መሆናቸው እንዲሁም  በስማቸው 2 ሚሊዮን 700 ሺ ብር ግምት ያላቸው 2 ሎደር መኪኖች መገኘታቸውን ገልጽዋል።
የአቶ ወልደስላሴ እህት የሆኑት ወ/ሮ ትርሃስ ደግሞ የ8ኛ ክፍል ተማሪና ምንም ስራ ያልበራቸው ሲሆን፣ በወንድሞቻቸው ድጋፍ ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገዛ አንድ ስካቫተር፣መኪና እንዲሁም   በአዲስ አበባ በየካና ቦሌ ክፍለ ከተሞች፣ በለገጣፎ፣ መቀሌና አክሱም 3 ሺ 266 ካሬ ሜትር ቦታዎች በስማቸው መገኘቱ ተመልክታል ፣እንዲሁም  በተለያዩ ባንኮችም 8 ሚሊዮን ብር ተቀማጭ ማድረጋቸውን  አንድ ተጨማሪ ዘመናዊ መኪና በስማቸው ተመዝግቦ መገኘቱን ጸረ ሙስና ኮሚሽን በምርመራ አረጋግጧል።
ዋናው ባለስልጣን አቶ ወልደስላሴ ደግሞ ስራ ሲጀምሩ ደሞዛቸው 1600 ብር የነበረ እና በእድገት እስከ 6000 ሺ ብር ሲከፈላቸው የቆየ ቢሆንም ያካባቱት ሀብት ግን ፈጽሞ ከደሞዛቸው ጋር የማይመጣጠን ነው ተብሏል። ባለ 4 ፎቅ ህንጻ ባለቤት የሆኑት አቶ ወልደስላሴ በ1 አመት ከ2 ወራት ቤቱን አከራይተው 790 ሺ ብር ገቢ አግኝተዋል።
አቃቢ ህግ ያቀረበውን ክስ የእስረኞች ጠበቆች፣ አዲስ የተጨመረ ክስ ነው በማለት አቤቱታ አቅርበዋል።
አቶ ወልደስላሴ ከወ/ሮ አዜብ ጋር በነበራቸው መቀራረብ ከፍተኛ ሃብት ማፍራታቸውን ፤ አቶ መለስ ዜናዊ ከሞቱ በሁዋላ ግን የእርሳቸው ዋነኛ ተቀናቃኝ የሆኑት የደህንነቱ ዋና አዛዥ አቶ ጌታቸው አሰፋ ግለሰቡን በሙስና ከሰው እንዳሳሰሩዋቸው አንዳንድ የመገናኛ ብዙሀን ገልጸው ሲዘግቡ ቆይተዋል።
ህወሃቶች እርስ በርስ በሚያደርጉት ሽኩቻ እየተካሰሱ ፍርድ ቤት መቅረባቸው የካበቱትን ሃብት ለማወቅ እየረዳ ነው የሚለው ዘጋቢያችን፣ በጸረ ሙስና ኮሚሽን ያልተመረመረና በፍርድ ቤት ቀርቦ ያልታወቀ ከዚህም የባሰ የሙስና ታሪክ እንደሚኖር መገመት ይቻላል ሲል አስተያየቱን አስፍሯል።

Monday 10 February 2014

A Glimpse of the Creeping Famine in Ethiopia

Alemayehu G Mariam
Behold the rider of the Black Horse (famine) eyeing Ethiopia once again
[Ethiopia] is the face of the world food crises. In a village in Southern Ethiopia, mothers cue with their malnourished children for emergency rations of food. They can’t afford to feed their babies and now it seems neither can the outside world. The distended stomachs, a symptom of the hunger so many here are suffering after two poor harvests in a row, and there are more new cases everyday… They were given food rations ten days ago… The government reserves ran out long ago, and now the U.N. supply is thinning too. They were given food rations 10 days ago… These people get a monthly handout; July’s [2013] was cut by a third. The rising price of grain worldwide means an extra one hundred million pounds need to be raised just to keep this up… 400 miles north near the Somali border, we found a changed landscape but the same crises and the rains are late here too and half the population needs food aid… They have been given a stark option [by regime representative Omar Abdi] ‘I have two options for them: to die or do the land.’ But across this country just now outside help is keeping millions alive. Malnutrition figures continue to rise and show no signs of slowing. This global food crises may be raising food bills in the West but the people here [in Ethiopia] are paying a far higher price.
Rang the famine alarm bell on the looming famine
In October 2012, I rang the alarm bell in my commentary “Ethiopia: An Early Warning of a Famine in 2013”. I claim no special knowledge or expertise in the economics of famine. However, by carefully piecing data, analyses and findings  from various sources including the Famine Early Warning Systems Network (FEWS NET), Oxfam, the U.N. World Food Programme, the U.N. Food and Agricultural Organization and reports of the New England Complex Systems Institute, [NECSI] (a group of academics from Harvard and MIT who specialize in predicting how changes in environment can lead to political instability and upheavals), it became clear to me that 2013 was likely to be the threshold year for the onset of famine or “catastrophic food crises”, as they euphemistically call it, in Ethiopia.
By late 2012, there was general consensus that reductions in the exports of grains from producing countries could trigger increased prices on the global commodities markets in 2013. I demanded to know how the “government of PM Hailemariam Desalegn expected to deal with the effects of the inevitable global food crises in light of its depleted foreign reserves and how his government will avert potentially catastrophic famine in the country.” I warned, “Planning to panhandle more emergency food aid simply won’t cut it. Relying on ‘Productive Safety Nets Programmes’ simply won’t do it. If the government of PM Hailemariam Desalegn cannot come up with a better answer or alternative to the looming famine over the horizon, it should be prepared to face not only a hungry population but also an angry one!”
For the past year, neither Hailemariam nor his puppet masters have done anything demonstrably constructive to deal with the “looming famine”. As usual, they are sitting around twiddling their thumbs and swatting flies waiting for American taxpayers to bail them out for the umpteenth time. There is a joke going around about the time Hailemariam was asked if he was worried about the poor rains and looming famine in Ethiopia. “We are not worried about the rains in Ethiopia; we are worried about the rains in America and Canada.” In February 2014, Hailemariam and Co. are polishing off their begging bowls to make a beeline to the U.S. and Canadian embassies to do their annual panhandling rounds.
In 2011, when Hailemariam was a “foreign and deputy prime minster” he was cocksure that his regime could lick famine and take a big bite out of poverty in no time. In an interview with  Africa Confidential, Hailemariam boasted, “For the last seven years, Ethiopia has witnessed double digit growth and this is a sign that our economic policy is working very well. If we continue this pace of development, we can double our economy in the next five years. This means that we will double our income for our community and so we will reduce poverty by 50%.” Hailemariam’s predecessor, the late imperious Meles Zenawi, “in his first press conference in Addis Ababa [over two decades ago], in reply to a question about his goals, declared that he would consider his government a success if Ethiopians were able to eat three meals a day.” (See video here.) In 2011, Meles pompously declared, “We have devised a plan which will enable us to produce surplus and be able to feed ourselves by 2015 without the need for food aid.”
“Three meals a day” in 2014 is pie in the sky for the vast majority of Ethiopians; and there is no chance that Ethiopia will feed itself “without the need for food aid” by 2015 as Meles “devised”. In fact, Ethiopia today is 123 out of 125 worst fed countries in the world. According to a new Oxfam food database “while the Netherlands ranks number one in the world for having the most plentiful, nutritious, healthy and affordable diet, Chad is last on 125th behind Ethiopia and Angola.”
The tragic irony is that as millions of Ethiopians starve, Saudi Arabian, Indian agribusinesses commercially farm Ethiopia’s most fertile lands to export food to their countries and China stealthily implements its plans for the penetration of Ethiopia’s agricultural sector. What a doggone crying shame! So much for “double digit growth”, “doubling the economy”, “surplus production” and “three meals a day”!
Uncovering the hidden famine in Ethiopia
Over the past few years, I have written over a dozen commentaries specifically on famine in Ethiopia or other related matters (see footnote in link). I have railed time and again against official secrecy in keeping famine stricken areas off limits to international and local journalists as tens of thousands die or suffer excruciating physical pain from food deprivation. The Meles/Hailemariam regimes have followed their predecessors lockstep in keeping famines secret. H.I.M. Haile Selassie in 1974 pretended there was no famine until the documentary the “Hidden Hunger” by Jonathan Dimbleby was aired provoking  shock and anger among Ethiopians. Former junta leader Mengistu Hailemariam was arrogantly dismissive during the 1984-85 famine. He casually asked, “What famine?” Meles, Hailemariam and those behind Hailemariam’s wooden throne today are far more cunning. Their solution is 1) to clampdown on the local press and shut the country down to all foreign journalists and media representatives who are interested in reporting on the impending humanitarian disaster, and 2) stand outside Western embassies with their shiny begging bowls.
It is interesting to note that the imperial government, the Derg junta and the current regime, like Nero who played his violin as Rome burned, continued their extravagant lifestyles as millions of Ethiopians starved. In 1974, before the overthrow of H.I.M. Haile Selassie, the Derg televised documentaries showing the excesses of the royal family as they fed their pets expensive morsels of meat and enjoying supposedly fancy imported cakes from Europe while tens of thousands died from famine in the northern part of the country. In 1984, on the tenth anniversary of the Derg’s seizure of power, the haughty soldiers let the champagne and whiskey flow like a river stream. Tens of thousands also died in the great famine of 1984.
In 2014, the situation is far worse. Those in power, their relatives, cronies, partners and cadres are spending tens of thousands of dollars on exclusive designer clothes, shoes, handbags and perfumes, hundreds of thousands of dollars on fancy cars and sports utility vehicles and living in multi-million dollar mansions furnished with the most expensive European furniture and kitchen appliances. They are stashing billions of dollars in foreign banks and secret investment schemes as documented in a report of Global Financial Integrity. In 2014, millions of Ethiopians are doomed to famine. Such is the sad but true story of Ethiopia today. By intimidating the press, the regime in power in Ethiopia has managed to maintain a complete news blackout on Ethiopia’s hidden famine. Thanks to the courageous Martin Geissler, ITN and NBC, we now have a glimpse of the human catastrophe that is taking shape.
The international conspiracy to keep Ethiopia’s hidden famines hidden
For over two decades, there has been a well-orchestrated conspiracy of silence between the regime in Ethiopia and the international donors, aid experts, international bureaucrats and NGOs not to use the dreaded “F” word in Ethiopia. They have gone to great lengths to hide the human face of famine by masking the truth with bureaucratic doublespeak and media newspeak. They talk about stages of “food insecurity”. Hungry and starving people are said to experience “acute food insecurity”, face “stressed” food situations, go into “crises” mode, graduate to “emergency” status and in the last stage undergo “catastrophic” food shortages. Nowhere  will they mention the word “famine” or “starvation”.
There is a reason why the word “famine” is banned among the hordes of international poverty pimps and the regime in Ethiopia. Famine conjures  up images of hordes of skeletal Ethiopians walking across the parched landscape, curled up corpses of famine victims under acacia trees and fly-infested children with distended bellies clutching their mothers at feeding camps. Geissler’s report last week does not show curled up corpses, but his video shows children with distended bellies clutching their mothers who are woefully resigned to the fact that their children will be dead in a day or two.
Talking about famine in Ethiopia openly is dangerous to the donor/NGO communities and the ruling regime because it portends political upheavals. In their analysis of recurrent famines in Ethiopia, Professors Angela Raven-Roberts and Sue Lautze noted, “Declaring a famine was also a complicated question for the Ethiopian government. Famines have contributed to the downfall of Ethiopian regimes… Some humanitarian practitioners gauge their successes, in part, according to ‘famines averted’.”
The conspiracy of silence serves the interest of all involved in dealing with the problem of famine in Ethiopia. To acknowledge the existence of famine by the regime, donors, NGOs and aid bureaucrats is tantamount to pointing an accusatory finger at oneself. If there is famine, it is proof positive that the donors who dumped millions of dollars in food aid, the NGOs involved in the distribution line and the highly overpaid international aid bureaucrats have failed. They have failed to produce a workable plan for food self-sufficiency in Ethiopia despite billions in aid. They have also failed to use their leverage against the regime in Ethiopia to deal with the famine bull by the horn.
The ruling regime in Ethiopia would rather have its tongue cut out than utter the word “famine”. For instance, in January 2010, Mitiku Kassa, Meles Zenawi’s agriculture minister declared, “In the Ethiopian context, there is no hunger, no famine… It is baseless [to claim hunger or famine], it is contrary to the situation on the ground. It is not evidence-based. The government is taking action to mitigate the problems.” Meles was equally dismissive: “Famine has wreaked havoc in Ethiopia for so long, it would be stupid not to be sensitive to the risk of such things occurring. But there has not been a famine on our watch — emergencies, but no famines.” No famines. No political prisoners. No human rights violations. No dictatorship. No problems!
But the conspiracy to deny the existence of famine in Ethiopia implicates the U.S. itself. In 2004, President George W. Bush “challenged his administration to ensure that famines were avoided during his tenure, a policy known as ‘No Famine on My Watch’; declaring the existence of a famine could be seen as a political shortcoming and, therefore, a political vulnerability.” The one exception to the official embargo on the use of the word “famine” is Wolfgang Fengler, a lead economist for the World Bank, who on August 17, 2011, definitively declared, “This [famine] crisis [in Ethiopia] is manmade. Droughts have occurred over and again, but you need bad policymaking for that to lead to a famine.” In other words, the fundamental problem with famine in Ethiopia is poor governance, not drought; incompetent and indifferent governance, not environmental factors. The recurrent famines in Ethiopia are manmade; that is, they are “made” by corrupt, indifferent,  incompetent and clueless regimes that lack political will to deal with the recurrent problem. Those in positions of power in Ethiopia have a petrified “bush mentality” impervious to rational planning and policymaking.
The ruling regime in Ethiopia blames “drought” for the deaths and suffering of millions of Ethiopians year after year. Yet that ne’er-do-well regime has done next to nothing to deal with the underlying problems aggravating the conditions leading to endlessly recurrent famines (see my July 2010 commentary “Apocalypse Now or in 40 Years?”). They have done nothing meaningful to control the country’s high population growth and food prices, improve environmental degradation and low agricultural productivity caused by state ownership of land and subsistence farming on fragmented small plots and have yet to undertake comprehensive agricultural planning. The regime’s solution has been to give away the most arable land in the country to so-called international investors who “lease” the land for commercial agriculture and exports to their home countries or for sale on the international market while Ethiopians starve. Hailemariam believes Saudi and Indian land grabs will transform Ethiopian agriculture. He recently told the New African, “We have subsistence agriculture and that’s now changing into commercial agriculture.”
The moral hazard of U.S. food aid to Ethiopia
There is a mindboggling irony and disconnect in U.S. food aid to Ethiopia. Every year for decades, the U.S. has provided food aid to Ethiopia with certain knowledge that it will be providing food aid again to the very same people year after year.  Except for feel-good-we-are-doing-something show and tell projects like “productive safety nets programmes” (which the ruling regime uses to extort political support from rural farmers and residents), the U.S. has imposed few conditions on the regime to deal with the famine problem. Yet millions of Ethiopians are in dire straits year after year; and millions of American tax dollars targeted for famine relief are lost to fraud, abuse and waste.
The fact of the problem is that U.S. food aid policy itself must be scrutinized to determine the extent to which it has contributed to keeping starving Ethiopians teetering on the edge of catastrophe. As Paul Hebert, the head of the UN Office for the Coordination of Humanitarian Affairs in Ethiopia recently observed, “The problem we face [in Ethiopia] is that more and more people are living on the edge… It doesn’t take very much to push them over that edge. The fear is that if we do have another large drought in this country and we haven’t made significant progress in addressing the chronic food security that could set things back significantly. Because of the precariousness of many people, you can easily slip into a very serious famine situation.”
Is the U.S. a silent accomplice watching on the sidelines as millions of Ethiopians living on the edge slide off the edge? As the recent NBC report documented, several millions of Ethiopians in the southern Ethiopia’s Somali and Oromiya regions are today facing “catastrophic severe food shortages”, commonly known as famine. Other areas expected to experience famine-like conditions in 2014  include northeastern Amhara and eastern and southern Tigray regions and the lowlands of East Hararghe Zone in Oromia. Between 12-20 million Ethiopians are estimated to be “living on the edge”; it will not take much to push them over the edge into full-fledged famine. Is the U.S. a silent accomplice?
The regime’s old panhandling tricks to hustle hundreds of millions of dollars in annual American taxpayer handouts may have already come to an end. U.S. Food for Peace contributions have been on steep decline for the past several years: 451.7million (2010); $313.3million (2011); $306.6million (2012); $235.5million (2013) and $86.9million for 2014. If Hailemariam and Co., believe they can wing the current “food crises” or solve Ethiopia’s “chronic food shortages” by panhandling the U.S. as usual, they had better think again. It seems even Obama now wants to see a change in the fraud, waste and abuse of U.S. food aid in countries like Ethiopia. Donor fatigue is spreading and setting hard throughout America, particularly outside the Washington beltway. Hailemariam and his puppet master should take note of that.
Annual harvest of famine: The fierce urgency for official transparency and accountability
The problem of “food shortages”, “food insecurity”, or whatever euphemism one chooses to use, in Ethiopia cannot be solved by food handouts. After corruption, panhandling is the lifeline of the regime in Ethiopia today. For over two decades, the regime in power in Ethiopia has been harvesting famine and shame. The regime is so accustomed to food handouts, it is now hopelessly addicted to food aid. The poor Ethiopian famine victims have no confidence in the ability or capacity of those in power to care of them. They cast their gazes upon the U.S. and other Western donors. How long must American taxpayers dole out their hard earned dollars to a regime that could not care less for its population? How long will American taxpayers tolerate their tax dollars being wasted, abused and defrauded in the name of humanitarian aid by corrupt regimes?
As I have often said, talking about the rule of law, accountability and transparency to those in power in Ethiopia today is like preaching Scripture to a gathering of deaf-mute heathen or pouring water over a slab of granite.  It is an exercise in total futility. After twenty-three years in power, they still cling to the politics of secrecy they practiced in the bush. They suffer from arrested development unable to transition from bushcraft to statecraft. That said, we must never stop insisting on transparency and accountability.
The role of press freedom in attaining transparency and accountability cannot be overstated. Investigative journalists in the past have saved the lives of millions in Ethiopia. They are the unsung heroes who exposed callous official indifference and saved millions from starvation and famine in the 1970s and 80s. When junta leader Mengistu Hailemariam denied the devastating famines, investigative journalists stepped in and let the world know what was happening leading to a massive global grassroots response. The same held true for the imperial regime in the early 1970s. It is no different now. Hailemariam and his puppet masters must come clean and let the world know the extent of famine and starvation in Ethiopia. Donor countries should insist on strict accountability by making sure that the truth about the looming famine is laid bare to the world, and insist on effective remedial measures. The alternative is that the U.S and other Western donors must accept co-responsibility as silent accomplices of the regime for the deaths of hundreds of thousands of Ethiopians in the looming famine. In the end, Ethiopians will remember not only the depraved indifference and criminal neglect of those claiming to be their leaders but also the inaction and silence of the bleeding heart do-gooders who give them lip service but are morally indifferent to their suffering. Perhaps they should all heed Bob Marley’s message in a song: “A hungry man is an angry man.”

Them belly full, but we hungry;
A hungry mob is a angry mob.

Cost of livin’ gets so high,
Rich and poor they start to cry:
Now the weak must get strong;

Now the weak must get strong.
Who will now save Ethiopians from the rider of the Black Horse holding a scale?
Professor Alemayehu G. Mariam teaches political science at California State University, San Bernardino and is a practicing defense lawyer.