Friday 25 December 2015

መንግስት ታዋቂ የተቃዋሚ ድርጅት መሪዎችን እየያዘ በማስር ላይ ነው

ታኀሳስ ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ የተነሳውን ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ መንግስት ወጣቶችን በየአካባቢው እያፈሰ ከማሰሩም በላይ የተቃዋሚ መሪዎችን ሲያስፈራራ ከቆየ በሁዋላ መሪዎችን ይዞ ማሰር ጀምሯል።
በቅርቡ ከእስር የተፈቱት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ተቀዳሚ ም/ል ሊ/መንበር አቶ በቀለ ገርባ እንዲሁም የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ምክትል ዋና ጸሃፊ የሆኑት የህግ ባለሙያውና ከ10 አመት በፊት በተደረገው ምርጫ የፓርላማ አባል የነበሩት አቶ ደጀኔ ጣፋ ገለታ በጸጥታ ሃይሎች ተይዘው ታስረዋል።
ግለሰቡ ከዚህ ቀደም በመንግስት ላይ በሚያደርሱት ጠንካራ ትችት ይታወቃሉ። በተመሳሳይ ዜና በጅማ ሂምና ዩኒቨርስቲ የሚማሩ 13 የኦሮሞ ተወላጆች ተማሪዎችን ለተቃውሞ ቀስቅሰዋል በሚል እየተፈለጉ ነው። የዩኒቨርስቲው የጥበቃና ደህንነት የስራ ሂደት ቢሮ ባወጣው ማስታወቂያ ገመችስ ታከለ፣ አሸናፊ ሌንጂሳ፣ አለማየሁ ገመቹ፣ መብራቱ ጅሬኛ፣ መሃመድ ሸምሲዲን፣ አብዲሳ በንቲ፣ ፋጂ ሙላት፣ አብደላ ተስሳ፣ ዘነበች ጌታቸው ፣በሻቱ ቃናአ፣ ቢራ ነጋሽ ደመቀ እንዲሁም አሰፋ ፋና ታህሳስ 14 በዩኒቨርስቲው ተገኝተው የዲሲፒሊን ኮሚቴው የሚሰጠውን ውሳኔ እንደከታተሉ ተጠርተዋል። በኦሮምያ በተካሄደው ህዝባዊ ተቃውሞ 85 ዜጎች በአጋዚ ወታደሮች ሲገደሉ ከ1 ሺ በላይ የሚሆኑ ደግሞ ታስረዋል።

የአንዋር መስጊዱን የቦምብ ጥቃት አስመልክቶ በእስር ቤት ከሚገኙ የኮሚቴው አባላት የተሰጠ መግለጫ

ህዝበ ሙስሊሙ ለተንኮለኞች ሴራ ሳይበገር አንድነቱን አጠንክሮ፣ አመለካከቱን አቻችሎ ሰላማዊ የመብት ትግሉን መቀጠል ይኖርበታል!

በአንዋር መስጊድ ቅጥር ግቢ ታህሳስ 01/2008 የደረሰው የቦንብ ጥቃት የዓለም አቀፉ ሕብረተሰብ ትኩረት እንዲሰጠው፣ ድርጊቱም በገለልተኛ አካላት በአስቸኳይ ተጣርቶ ለህዝብ ይፋ ይደረግ ዘንድ እንጠይቃለን!

አርብ ታህሳስ 15/2008 /አዲስ አበባ/ኢትዮጵያ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ሕገመንግስታዊ የመብት ጥያቄያችንን ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ማቅረባችን ይታወቃል። ለጥያቄዎቻችን ተገቢውን እና ፍትሃዊ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ጥያቄውን በሀሰት በመፈረጅ ሰላማዊ ሂደቱን ለመቀልበስ ተደጋጋሚ ጥረት ተደርጓል። [ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]

Monday 21 December 2015

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ባቀረቡት ጥሪ ኢትዮጵያውያን ቅድሚያ ሰጥተው ሊተገበራቸው የሚገቡ ስድስት ተግራት

አርበኞች ግንቦት 7 በሚከተሉት ስድስት ነጥቦች ዙርያ የተቀናጀ ትግል እንዲካሄድ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የትግል ጥሪ ያደርጋል።

1. በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች እየተካሄደ ያለው ትግል ከአሁኑ በተሻለ ተጠናክሮ እንዲቀጥል! ለዚህም በነኝህ አካባቢዎች ያለው የነኝህ ማህበረሰብ አባላት ብቻ ሳይሆን ባካባቢዎቹ የሚገኙ ሌሎች ኢትዮጵያውያን ትግሉን በስፋት እንዲቀላቀሉ እንጠይቃለን! በትግሉ ሂደትም በአሮሞና በአማራ ሕዝብ መካከል የትግል አጋርነትና የግብ ተመሳሳይነት መኖሩን ማጉላት ይገባናል። በአሁኑ ሰዓት ግፉና ስቃዩ እጅግ ለበረታበት የኦሮሞ ሕዝብ “አለንልህ፣ ከጎንህ ነን” ማለትና በርግጥም ከጎኑ ተሰልፎ መገኘት ይኖርብናል።
2. በሌሎች ክልሎች ያሉ ኢትዮጵያውያን ትግሉን በያሉበት ባስቸኳይ እንዲቀላቀሉ ጥሪ እናደርጋለን! ሌሎች ክልሎችና አካባቢዎች የሚያቀርቧቸው ጥያቄዎች በየአካባቢያቸው ባሉ የአስተዳደር በደሎችና የነጻነት ፍላጎት ላይ ያተኮሩ እንዲሆን ማድረግ ይገባል፤ ሆኖም ግን ለአካባቢያዊ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ ማግኘት የሚቻለው የአገራችን የፓለቲካ ሥርዓቱ ሲለወጥ ብቻ መሆኑ በትግሉ ሂደት ማሳየት ይጠበቅብናል!
3. የኢትዮጵያ መከላከያና ፖሊስ ሰራዊት እንዲሁም በያካባቢው ስርዓቱን እንዲያገለግሉ የተመለመሉ ሚሊሺያዎች ከኢትዮጵያ ህዝብ አብራክ የወጡ፤ ራሳቸውም የወያኔ አገዛዝ ሰላባ የሆኑ መሆኑን ሁሌም ማስታወስ ይገባል። አርበኞች ግንቦት 7 ይህ የኢትዮጵያ ሰራዊት በወንድሞቹ፣ እህቶቹና ወላጆቹ ላይ እንይተኩስ ይልቁንም አፈሙዙን በዚህ እኩይ ስርዓት ላይ እንዲያዞር በደተደጋጋሚ ጥሪ አድርጓል፤ አሁንም በዚህ ባስራ አንደኛው ሰዓት ይህንን ህዝባዊ ጥሪ በድጋሚ እናደርጋለን! በትግሉ ውስጥ የምትሳተፉ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ይህንን ጥሪ በየትግሉ አደባባይ ማስተጋባት፤ በጎናችን ለምናገኘው ጎረቤታችን፤ ዘመዳችን ወይንም ጓደኛችን ለሆነ የዚህ ያፈና መዋቅር አባል ሁሉ በተደጋጋሚ መንገር አንርሳ!
4. ለኦህዴድ፣ ብአዴን፣ ደህዴድና ህወሓት መካከለኛና አነስተኛ ካድሬዎች እንዲሁም ዝቅተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ለሆናችሁ ሁሉ! እናንተ ዛሬ ከሕዝብ ትግል ጎን ቆማችሁ ራሳቸሁንም ሆነ አገራችሁን መታደግ የምትችሉበት ወቅት መሆኑን እወቁ። ዛሬ የሕዝብን ጥሪ ሳትሰሙ ሥርዓቱን ለመታደግ ግፍ መፈፀማቸሁን ከቀጠላችሁ ነገ ዘራፊ አለቆቻቸሁ የዘረፉትን ለመብላት ሲሮጡ እናንተን የማያስጥሏችሁ መሆኑን መረዳት ለራሳችሁም ሆነ ለቤተሰባችሁ ዘለቄታዊ ጥቅም ይበጃል። አሁኑኑ ሰልፋችሁን አሳምሩ! ነገ አብሮአችሁ ከሚኖረው ህዝብ ጋር አትጣሉ! በትግሉ ውስጥ የምትሳተፉ ኢትዮጵያውያንም ከሕዝብ ትግል ጎን ለመቆም ለሚፈልጉ ለነኝህ ወገኖች መንገዱን አመቻቹላቸው!
5. ደም እየበዛ ሲሄድ ሀሞት እየመረረ እንደሚሄድ የኢህአዴግ ከፍተኛ ባለስልጣኖች ጊዜው ሳይመሽ ቢገነዘቡት ይበጃቸዋል! የኢህአዴግ ባለሥልጣናት አገራችን መመለሻ የሌለው ቀውስ ውስጥ ከመግባቷ በፊት እና የዘረፉትን ንብረት በሰላም ለመብላት በፍጹም የማይችሉበት ሁኔታ ከመፈጠሩ በፊት እየሄዱበት ያለውን የእውር ድንብር መንገዳቸውን ቆም ብለው እንዲያስቡ እንመክራቸዋለን! ለሀገራችን ችግሮች ፖለቲካዊ መፍትሄ ለመስጠት ወደ እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የሚያሻግር ሁሉንም ያሳተፈ ድርድር አሁኑኑ ቢጀምሩ ለራሳቸውም ላገሪቱም እንደሚበጅ ልናሳስባቸው እንወዳለን! ይህን ለማድረግ ደግሞ በቅድሚያ ሰላማዊ ሰዎች መግደልና ማፈንን በአስቸኳይ እንዲያቆሙ፤ የፓለቲካ እስረኞችን በሙሉ ባስቸኳይ እንዲፈቱና አፋኝ ህጎችን በመሰረዝ ለእንዲህ አይነት ሰላማዊ ሽግግር ዝግጁ መሆናቸውን በተግባር እንዲያሳዩ እንጠይቃቸዋለን!
6. በመጨረሻም በመሳሪያም ሆነ በሌላ መንገድ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የሚታገሉ ኃይሎች ሁሉ እንዲሰባሰቡና ይህን ስርዓት ለማንበርከክም ሆነ በይበልጥም ከዚህ ስርዓት ባሻገር የጋራ ቤታችን የሆነችውን ኢትዮጵያ አገራችንን በእውነተኛ እኩልነት፤ በፍትህና በዴሞክራሲያዊ ስርዓት እንደገና የምትታነጽበትን መንገድ በጋራ ለመተለም ባስቸኳይ ውይይት እንዲጀመር ጥሪ እናደርጋለን!

ሰማያዊ ፓርቲ እና መድረክ በጋራ ሰላማዊ ሰልፍ ጠሩ

ሰማያዊ ፓርቲ እና የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) አዲስ አበባ ላይ በጋራ ሰላማዊ ሰልፍ መጥራታቸውን የሰማያዊ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ነገሰ ተፋረደኝ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ እና መድረክ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት መስማማታቸው የሚታወስ ሲሆን እሁድ ታህሳስ 17/2008 ዓ.ም በጋራ ሰልፍ መጥራታቸውን አቶ ነገሰ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡Merera Gudina and Yilkal Getnet
ሰማያዊ ፓርቲና መድረክ የጠሩት ሰልፍ በዋነኛነት ከማስተር ፕላኑ ጋር በተያያዘ መንግስት እየወሰደው ያለውን እርምጃ፤ እንዲሁም መንግስት ለሱዳን አሳልፎ ለመስጠት ያቀደውን መሬቱ እንዳይሰጥ ለመቃወም ያለመ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ሰልፉ ላይ በሰብአዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ላይ መንግስት እየወሰደው ያለውን እፈና እና እርጃዎቸ እንደሚያወግዙ ምክትል ሊቀመንበሩ ተገልፆአል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ እና መድረክ በጋራ የሚያደርጉት ሰልፍ መነሻውን ፒያሳ ራስ መኮንን ድልድይ አድርጎ፣ በቸርቺል አደባባይ የሚያልፍ ሲሆን መዳረሻው ኢትዮ-ኩባ አደባባይ መሆኑን ታውቋል፡፡ መንግስት እየወሰዳቸው ባሉ የተሳሳቱ እርምጃዎች ሀገራችን አጣብቂኝ ውስጥ መሆኗን የገለፁት አቶ ነገሰ ተፋረደኝ ሀገራችን ካለችበት ችግር ለማውጣት ኢትዮጵያውያን በጋራ እንዲቆሙና በሰልፉም እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ሰልፉ እሁድ ታህሳስ 17/2008 ዓ.ም ከጠዋቱ 3 ሰዓት ፒያሳ ራስ መኮንን ድልድይ ላይ እንደሚጀምር ለማወቅ ተችሏል፡፡

At least 75 killed in Ethiopia protests: HRW

Nairobi (AFP) – At least 75 people have been killed during weeks of protests in Ethiopia which have seen soldiers and police firing on demonstrators, Human Rights Watch said on Saturday.
Oromo protesters leave Wolenkomi Photographer: William Davison/Bloomberg
Oromo protesters leave Wolenkomi Photographer: William Davison/Bloomberg
“Police and military forces have fired on demonstrations, killing at least 75 protesters and wounding many others, according to activists,” HRW said in a statement.
Rights groups have repeatedly criticised Ethiopia’s use of anti-terrorism legislation to stifle peaceful dissent, with Washington expressing concern over the crackdown and urging Addis Ababa to employ restraint.
There was no immediate response from Ethiopian government, which has previously put the toll at five dead.
Government spokesman Getachew Reda said the “peaceful demonstrations” that began last month had escalated into violence, accusing protesters of “terrorising the civilians.”
The protests began in November when students opposed government proposals to take over territory in several towns in the Oromia region, sparking fears that Addis Ababa was looking to grab land traditionally occupied by the Oromo people, the country’s largest ethnic group.
Demonstrations have taken place in the towns of Haramaya, Jarso, Walliso and Robe among others.
‘Dozens’ shot
“Human Rights Watch received credible reports that security forces shot dozens of protesters in Shewa and Wollega zones, west of Addis Ababa, in early December,” HRW added.
“Several people described seeing security forces in the town of Walliso, 100 kilometres (60 miles) southwest of Addis Ababa, shoot into crowds of protesters in December, leaving bodies lying in the street.”
HRW also said “numerous witnesses” described how “security forces beat and arrested protesters, often directly from their homes at night.”
Pictures have appeared on social media, apparently showing bloodied protestors and armed police firing tear gas at student demonstrators.
“The Ethiopian government’s response to the Oromia protests has resulted in scores dead and a rapidly rising risk of greater bloodshed,” HRW’s Leslie Lefkow said.
“The government’s labelling of largely peaceful protesters as ‘terrorists’ and deploying military forces is a very dangerous escalation of this volatile situation.”
With at least 27 million people, Oromia is the most populous of the country’s federal states and has its own language, Oromo, distinct from Ethiopia’s official Amharic language.
– US ‘deeply concerned’ –
In a statement issued on Saturday, which did not directly refer to the HRW figures, Washington expressed grave concern over the unrest.
“The United States is deeply concerned by the recent clashes in the Oromia region of Ethiopia that reportedly have resulted in the deaths of numerous protestors,” said the State Department.
“We urge the government of Ethiopia to permit peaceful protest and commit to a constructive dialogue to address legitimate grievances,” it said, also urging protesters “to refrain from violence and to be open to dialogue.”
Writing on Twitter on Friday, Washington’s UN envoy Samantha Power spoke of “concerning rhetoric” from Ethiopia’s prime minister, insisting the government “must use restraint” in its response to the Oromo protests.
Britain’s Foreign Office also expressed concern over the protests in a statement issued on Friday, noting that some had “turned violent, resulting in casualties.”
“There have been heavy clashes including gunfire between protesters and security forces” on December 17, it said, warning Britons against all but essential travel to western and southwestern parts of Oromia.
Some foreign-owned commercial farms have been “looted and destroyed” in the protests near Debre Zeit, some 50 kilometres (30 miles) southeast of Addis Ababa, HRW said.
HRW said the protests — and bloody crackdown — echoed protests in April and May 2014 when police were accused of opening fire and killing “dozens” of protestors. The government said eight people died in the 2014 unrest.