Wednesday 5 November 2014

ሚሊዮኖች ድምጽ – የአንድነት የአዲስ አበባ ምክር ቤትን ይተዋወቁ

የአንድነት ፓርቲ በተለያዩ የአገሪቷ ክፍሎች መዋቅሩን የዘረጋ ድርጅት ነው። ወደ አምስት ሚሊዮን የሚጠጋ ሕዝብ በሚኖርባት አዲስ አበባ ፣ ፓርቲው እስከታች በመዝለቅ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ድርጅታዊ መዋቅሩን ዘርግቶ የሚንቀሳቀስ ነው።
- የአዲስ አበባ ምክር ቤት የተቋቋመው በአዲስ አበባ ከሚገኙ 23 የምርጫ ወረዳዎች በተወከሉ ስድስት ስድስት አባላት ነው። በአጠቃላይ 138 አባላት አሉት።
- በ23ቱም የምርጫ ወረዳዎች ፣ ዘጠኝ የወረዳው የስራ አስፈፃሚ አባላት ያሉት ሲሆን፣ በ116 መንግስታዊ መዋቅር ወረዳዎች 5 የመሰረታዊ ድርጅት አመራር አባላት አሉት
- ከወረዳ መዋቅር በተጨማሪ፣ ከአሥሩም ክፍለ ከተማ ተመርጠው የመጡ፣ በአጠቃላይ 70 የክፍለ ከተማ አስተባባሪዎች አሉት።
በአጠቃላይ በአዲስ አበባ አንድነት ዉስጥ ያሉ አመራሮች፣ በድምሩ 895 ሲሆኑ፣ አንድነት በሺዎች የሚቆጠሩ አባላትና ደጋፊዎች በአዲስ አበባ ያሉት፣ በትልቅ ህዝባዊ መሰረት ላይ የታነጸ ድርጅት ነው።
አንድ ድርጅት ለዉጥ ሊያመጣ የሚችለው ሕዝቡን ከላይ እስከ ታች ማደራጀት ሲችል ነው። አገዛዙ ኢሕአዴግ ስማቸው በምርጫ ቦርድ ሰነድ ላይ ብቻ የሚታወቁ፣ ወደ ሕዝብ የማይሄዱና ሕዝቡን የማያደራጁ፣ ገለባ ድርጅቶችን ብቻ ነው ማየት የሚፈልገው። በየወረዳው ህዝቡ ለመብቱና ለመጻነቱ እንዲነሳ ድርጅታዊ ሥራ የሚሰራን ፣ እንደ አንድነት ፓርቲ ያለ ድርጅት፣ ለገዢው ፓርቲ ኢሕአዴግ አይመቸዉም። ስለዚህም ነው አንድነት ፓርቲ በየጊዜው፣ ሕገ-ውጥ በሆነ መንገድ የአገዛዙ ዱላ እያረፈበት ያለው።
ሆኖም አንድነት፣ የሕዝብ ድጋፍ ያለው እንደመሆኑ፣ የሚነሳበትን ዱላ ተቋቁሞ ትግሉን እየመራ ነው። የአዲስ አበባ አንድነት አሁን ከተደረገው በላይ የአባላትን ቁጥር ለማስደግ፣ ለሕዝቡ የጠራና የተሻለ አማራጭ ሆኖ ለመቅረብ፣ በአዲስ አበባ ሃያ ሶስቱም ወረዳዎች ጠንካራ ተወዳዳሪ ለማሰለፍ፣ የቀረቡ ተወዳዳሪዎች በሕዝቡ እንዲመረጡ ከፍተኛ ቅስቀሳ በማድረግና ህዝቡ የሰጠዉም ድምጽ እንዳይሰረቅ ነቅቶ ለመቆጣጣር የሚቻልበትን ሁኔት ከወዲሁ ለማመቻቸት በመንቀሳቀስ ላይ ያለ፣ ከኢሕአዴግ ቀጠሎ መረቡን በስፋት የዘረጋ ብቸኛ ድርጅት ነው።
የአዲስ አበባ ምክር ቤት ይህን ሲመስል፣ የአንድነት ፓርቲ በተመሳሳይ ሁኔታ በአዳማ፣ በባህር ዳር፣ በጂንካ፣ በአርባ ምንጭ፣ በሶዶ፣ በአሰላ ፣ በመቀሌ ..እንዲሁም በርካታ ከተሞችና ዞኖች ሰፊ መዋቅር ያለው ድርጅት እንደሆነም ይታወቃል።
ለዉጥ ስለተመኘነው አይመጣም። ለዉጥ ሥራ ይጠይቃል። ነጻነት ዋጋ ያስከፍላል። ህዝቡን ለመብቱና ለነፃነቱ እንዲነሳ፣ ሕዝቡን እስከታች ድረስ ማደራጀት ያስፈልጋል። የአንድነት ፓርቲ በአዲስ አበባ በ23 ወረዳዎች እያደረገ ያለውም ይሄንኑ ነው።
እንግዲህ በዚህ ወሳኝ ወቅት፣ በአገር ዉስጥም ሆነ ከአገር ዉጭ የምንኖር ኢትዮጵያዉያን ትግሉን በመቀላቀል የአንድነት አባል እንሁን። በአገራችን ያለው መጠነ ሰፊ ችግሮችን የኑሮ ዉድነቱን፣ የፍትህ መጓደሉን፣ ዘረኝነቱን እየተነጋገርን ከምናወራ ብሶትና ምሬት ጎን ለጎን፣ መፍትሄ ልናመጣ እንደምንችል በማሰብ “እስከ መቼ ? ብለን በመጠየቅ በግልና በቡድን ምን ማድረግ እንዳለብን እንደ ዜጋ መነጋገር መጀመር አለብን። በግላችን “ የለውጥ አካል እሆናለሁ” ብለን ልንነሳ ያስፈልጋል። ሁሉም በግሉ ዉሳኔ ከወሰነ፣ አንድ ተብሎ አሥር ሚሊዮኖች እንሆናለን።UDJ-SEAL

በምእራብ አርማጭሆና በመተማ የአንድነት ፓርቲ አደራጆች ጭካኔ በተሞላበት መንገድ ታፍነው ተወሰዱ

ጥቅምት ፳፬(ሃያ አራትቀን ፳፻፯ / ኢሳት ዜና :-ከአዲስ አበባ የተላኩ የፌደራል ፖሊስ አባላትና ደህንነቶች፣ ወደ ፓርቲው መሪዎች ቤት ከንጋቱ አስራ አንድ ሰአት ላይ በመሄድ፣ መኖሪያ ቤቶቻቸውን ሰብረው በመግባትና አንዳንዶችንም ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ በመደብደብ አፍነው ወዳልታወቀ ቦታ ወስደዋቸዋል።
የመተማ ወረዳ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ በላይነህ ሲሳይ፣ የምእራብ አርማጭሆ ወረዳ ሰብሳቢ አቶ አንጋው ተገኝ እንዲሁም የስራ አስፈጻሚ አባላት የሆኑት አባይ ዘውዱና እንግዳው ዋኘው ከተያዙት መካከል ይገኙበታል። የአቶ በላይነህ ቤት ከሌሊቱ 9 ሰአት የተከበበ ሲሆን፣ አቶ በላይ ሳይነጋ ቤቴን አልከፍትም በማለት፣ ከንጋቱ 11 ሰአት ላይ ቤቱን ሰብረው ገብተው ወስደውታል። ቤተሰቡ በፌደራል ወታደሮች ድርጊት በእጅጉ ተዳንገጠዋል።
ከንጋቱ 11 ሰአት ሲሆን በአብራጅራ የአንድነት ፓርቲ አመራር በሀነው በአቶ አንጋው ተገኝ ቤት የተገኙት የፌደራል ፖሊሶች፣ ቤቱን እንዲከፍት ሲጠይቁ፣ እስኪነጋ እንዲታገሱት ቢጠይቅም፣ ወታደሮቹ በሩን ሰብረው በመግባት ክፉኛ ደብድበው ወስደውታል። አቶ አንጋው ክፉኛ በመደብደቡ ወታደሮች አንስተው መኪና ላይ እንደጫኑት የአይን እማኞች ገልጸዋል።
ወጣት አባይ ዘውዱን ሊይዙ የሄዱት ፖሊሶች ከቤተሰቦቻቸው በደረሰባቸው ተቃውሞ ውዝግብ ፈጥረው የቆዩ ቢሆንም፣ በመጨረሻ ግን በሃይል መውሰዳቸውን ቤተሰቦች ተናግረዋል።
ለቤተሰቡ ብቸኛ የሆነውንና ከዚህ ቀደም ስራ በመከልከልና በእስራት ከፍተኛ እንግልት ሲደርስበት የነበረውን ወጣት አባይን ላለማስወሰድ ሲማጓቱ የነበሩ ሁለት እህቶቹ በሰደፍ በመመታታቸው በአሁኑ ጊዜ ጤና ጣቢያ ውስጥ መተኛታቸውን ቤተሰቦች ገልጸዋል። አንደኛዋ ጡቷ ስር በሰደፍ ስትመታ ሌላኛዋም ተመሳሳይ ጉዳት ደርሶባት ፈሳሽ ምግብ ወይም ግሉኮስ ተተክሎላት ህክምና እየተደረገላት ነው።  በአካባቢው ህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት ያላቸው ሶስቱ የፓርቲው አመራሮች በተያዙበት ወቅት ነዋሪው ተቃውሞ በማሰማት ውሳኔውን ለማስቀልበስ ጥረት ቢያደርግም ሳይሳካ ቀርቷል። ይሁን እንጅ ድርጊቱ የህዝብ ቁጣ መቀስቀሱን ነዋሪዎች ይናገራሉ።
አቶ አንጋው ተገኝ ከዚህ በፊት በከፍተኛ ሁኔታ  ተደብድቦ ታስሮ መፈታቱ ይታወቃል። አባይ ዘውዱም ኤርትራ ካሉ ተቃዋሚዎች ጋር ትገናኛለህ በሚል ከወር በፊት በመከላከያ አባላት ተይዞ በህዝብ ተቃውሞ እንዲፈታ መደረጉ ይታወቃል።  ሁለቱም መሪዎች ስለሚደርስባቸው እንግልት በቅርቡ ለኢሳት ቃለምልልስ መስጠታቸው ይታወቃል።
ገዢው ፓርቲ የሃይል አፈናውን  አጠናክሮ መቀጠሉን የሰሜን ጎንደር አንድነት ፓርቲ የአመራር አካል የሆኑት አቶ ሙላት ፍሰሃ ተናግረዋል በደቡብ ጎንደር ደግሞ የፎገራ ወረዳ የአንድነት ሰብሳቢ የሆኑት አቶ አለበል ዘለቀ ከሚሰሩበት የእርሻ ቦታቸው ላይ በፌዴራል በፖሊስ ተይዘው ወዳልታወቀ ቦታ ሲወሰዱ፣ በምዕ/ጎጃም ደጋ ዳሞት ወረዳ የወረዳው ሰብሳቢ አቶ ጥላሁን አበበና 3 የአንድነት አባላት ከቤታቸው በፌዴራል ፖሊስ ተይዘው ወዳልታወቀ ቦታ ተወስደዋል።
ከትናንት በስቲያ ደግሞ የምእራብ ጎጃም የመኢአድ ዋና ጸሃፊ አቶ ጌታቸው መኮንንና የፓርቲው ዋና ጸሃፊ የነበሩት አቶ ተስፋየ ታሪኩ  ተይዘው መታሰራቸው መዘገቡ ይታወቃል።  የወላይታ ዞን የአንድነት ፓርቲ ሰብሳቢ አቶ ማሞ ገሞ እና የዞኑ ድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ወኖ በዳሳ ጥቅምት 22 ቀን 2007 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ በአንድ ሆቴል ውስጥ እያሉ በከተማው የፖሊስ አዛዥ መመሪያ በመንግስት ሀይሎች ከባድ ድብደባ እንደተፈፀመባቸው የፓርቲው የድርጅት ጉዳይ ለፍኖተ ነፃነት መናገራቸው መዘገቡ ይታወሳል።

Moral Hazards of the Aid Industry in Ethiopia: justice is overdue November 4, 2014

November 4, 2014
Commentary by Aklog Birara (Dr.)
Click here for PDF
“Africa is treated as the dustbin of the world…To donate untested food and seed to Africa is not an act of kindness but an attempt to lure Africa into further dependency on foreign aid.”
Michel Chossudovsky “The Globalization of Poverty and the New World Order”
Ethnic-federalism (the kilil system) is an instrument of disenfranchisement
Aklog Birara, PhD
In October each year the Bretton Woods Institutions, the World Bank and the International Monetary Fund created in 1944 to reconstruct worn-torn Europe and the rest hold their meetings alternating between Washington and other countries. These meetings discuss and define global monetary and development policies that affect and often bind the global community regardless of economic and political status. I had the privilege of attending these meetings representing Ethiopia and as a Senior Member of the World Bank Group. My observation is that wealthy and powerful countries decide policies that help their own societies first. As the only independent country in Africa, Ethiopia served as a founding member of numerous multilateral and UN and regional agencies and is recognized as a founding member of the Bretton Woods Institutions. Committed to multilateralism, Ethiopia served the world community (Korea, the Congo, for example) much longer than the vast majority of countries that were colonized at the time. It played a leading role in the formation of the Organization of African Unity and its successor the African Union that it continues to host. Nevertheless, largely because of its poverty and technological backwardness, its influence in the Bretton Woods institutions is minimal; as is the influence of the rest of Sub-Saharan Africa. Poor and underdeveloped nations are by definition at a disadvantage in globalization. They are receivers rather than policy makers. So, why is Ethiopia preferred as the largest aid recipient in Africa today?
When did aid to Ethiopia begin?
Today, Ethiopia is the largest aid recipient in Sub-Saharan Africa and among the top in the world for a strategic reason. It is important to note though that aid to Ethiopia did not start under the current governing party, the Tigray People’s Liberation Front (TPLF) and the ethnic coalition, the Ethiopian Peoples’ Revolutionary Party (EPRDF) that this minority ethnic elite dominates. Ethiopia received its first loan from the World Bank in 1950 in the amount of $5 million for a road rehabilitation project following the devastating Fascist invasion that had destroyed the country’s modest social and physical infrastructure. The World Bank’s participation in alleviating Ethiopia’s poverty continued for more than 64 years. Prominent in the Bank’s development effort and contributions is significant investment in the social sectors—education, health, nutrition, sanitation, safe drinking water, HIV/AIDs, agriculture and food security and rural roads; and in institution capacity building. The Bank’s economic and sector analytical work and policy directions in Ethiopia are equally notable. These contributions have been especially pronounced over the past 24 years. Total Official Development Assistance (ODA) to the TPLF-led government has exceeded $30 billion. Why?
My thesis is Ethiopian Western allies and the donor community especially multilaterals such as the World Bank, the European Commission and the African Development Bank and bilateral agencies such as USAID and DFID (UK) transferred enormous financial resources since the current government took political power in 1991 for strategic reasons. The Governments of the United States and United Kingdom identified Meles and his party as indispensable friends not only in the Horn but also in the rest of Africa. On October 22 214, David Smith of the Guardian wrote an outstanding piece, “Ethiopia, 30 Years after the Famine,” in which he underpins direct correlations between the American War against Terrorism and massive aid to the Ethiopian government under Meles and beyond. “Ethiopia is seen as a reliable police officer (client state) in the region, hosting a U.S. Military base and sending troops to fight the Islamist militant group al-Shaabab in neighboring Somalia.” The War on Terrorism is now a pretext used by the TPLF to terrorize Ethiopians. Being a powerful country’s “police officer” pays for those in power; but has practically wiped out the semblance of civil liberty or human rights or a sense of human worth in Ethiopia today.
The aid narrative articulated by the donor and diplomatic community differs from my thesis. Instead, the narrative is that Ethiopia deserves more aid because of its intractable poverty and the destitution of the vast majority of the population; and especially the intractable dilemma of feeding its growing population that has reached 96 million. Even if we accept this definition, the aid industry has not made a headway to make the vast majority of Ethiopians self-sufficient and secure and the middle class prosperous. Ironically, one of the fastest growing economies in the world has impoverished the tiny middle class instead of enriching it. Most members of this class rely heavily on relatives in the Diaspora to make ends meet. Forget the poorest of the poor who barely survive. Ethiopia is a country of extremes: a tiny minority, mostly Tigrean that is filthy rich; and the vast majority who are unable to eat three meals a day. The filthy rich does not alleviate poverty in its home base, Tigray either.
Ethiopia is one of the hungriest and unhealthiest nations on the planet. It is also one of the most repressed and oppressed. Per capita income is still a miniscule $470 per annum. It is not just the poor and the unemployed or underemployed who leave the county in droves. It also the most educated. Between 1991 and 2006, 3,000 of 3,700 Ethiopia- educated and trained medical doctors left the country. Hundreds of thousands of Ethiopian youth take enormous risks seeking employment alternatives in North Africa, the Middle East, the rest of Africa and the West. Many of the 160,000 day laborers expelled by Saudi Arabia and shipped to Ethiopia last year trekked back to the country that expelled them. They are being re-expelled. Young Ethiopians immigrate to the Ukraine, an economic basket case with at least 10 percent unemployment. They are being expelled. This does not suggest the growing Ethiopian economy that is enriching the few and creating new millionaires, including TPLF generals each year has the absorptive capacity to create the required 2.5 million jobs each year. The Ethiopian government does not care for citizens. It only cares for the preservation of the Orwellian state that is backed by Western Governments, especially the U.S. and the U.K and financed by multilaterals such as the World Bank and the E.U. Ethiopia’s security, intelligence and defense forces have links to their backers in the West. No one knows what percentage of Ethiopia’s GDP subsidizes spies, security, defense, wealthy defense, federal police and other officers. I reckon it is high.

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የመጀመሪያ ዙር ህዝባዊ ትግል ፕሮግራሙን ይፋ አደረገ • የ24 ሰዓት (የአዳር) የተቃውሞ ሰልፍ ተጠርቷል – በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም 9 ተቃዋሚ ፓርቲዎች የመሰረቱት ትብብር ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል ለአንድ ወር የሚቆይ የመጀመሪያ ዙር የህዝባዊ ትግል ፕሮግራሙን ዛሬ ጥቅምት 25/2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ይፋ አደረገ፡፡
‹‹ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ የማይታሰብ በመሆኑ የተዘጋውን በር ለመክፈት የ‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ› በሚል የፕሮግራም መርሃ ግብር ለመክፈት ወስኖ የመጀመሪያው ዙር እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ከተማ ለማድረግ›› እንዳዘጋጀ ያሳወቀው ትብብሩ የትግሉ ዓላማ ፍትሃዊ ምርጫ እንዲኖር የሚያስችል መሆኑን ገልጾአል፡፡
‹‹ምርጫ ቦርድ ለገዥው ፓርቲ ያለውን ወገናዊነትና ጉዳይ አስፈጻሚነት ፍንትው አድርጎ አሳይቷል›› ያለው መግለጫው በመጀመሪያ ዙር የአንድ ወር ፕሮግራሙ 6 ዋና ዋና ተግባራትን ለመፈጸም ዝርዝር እቅዶችን አውጥቶ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል፡፡ በህዳር ወር የሚያከናውናቸው ተግባራትም፡-
1. በቤተ እምነት ጸሎት እንዲደረግና ጥሪ ማቅረብና አማኞች እንደየ እምነታቸው ተሳትፎ እንዲያደርጉ ማድረግ
2. የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባዎችን ማድረግ
3. የተቃውሞ ድምጽ ማሰማት (ሰላማዊ ሰልፍ)
4. ለመንግስት ተቋማት ደብዳቤ ማስገባት
5. በምርጫ ዙሪያ የፓናል ውይይቶችን ማድረግና
6. የህዝብን ተሳትፎ ማበረታታትና ድጋፍ ማሰባሰብ እንደሆኑ በመግለጫው አሳውቋል፡፡
ከእቅዶቹ መካከልም በሶስት ተከታታይ እሁዶች በተለያዩ የአዲስ አበባ ክፍሎች 3 የአደባባይ ስብሰባዎች እንደሚኖሩ፣ በመጨረሻው መርሃ ግብርም ህዳር 27ና 28 በፕሮግራሙ ማጠቃለያነት የ24 ሰዓት (የውሎና የአዳር) የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚደረግ የትብብሩ ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ገልጸዋል፡፡
በገዥው ፓርቲና በምርጫ ቦርድ ጥምረት ይፈጸማል ያለውን ህገ ወጥ ተግባር በመታገል ለሰላማዊ ትግሉ አወንታዊ አስተዋጽኦ ለማበርከት እስከመጨረሻው በፅናት ለመቆም መዘጋጀቱን የገለጸው ትብብሩ በአገር ቤትና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን፣ በትብብሩ ሂደት ቆይተው እስካሁን ያልፈረሙና ሌሎች ፓርቲዎች እና የዓለም አቀፉ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ከጎኑ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርቧል፡፡10359898_1498367410433215_3013403061198377504_n

የሰማያዊ ፓርቲ የጎንደር አስተባባሪ ታሰረ

 ‹‹ጎንደር ውስጥ ያለውን የህዝብ ጥያቄ ለማፈን የተደረገ ነው፡፡›› አቶ ዮናታን ተስፋዬ
• ‹‹የፀረ ሽብር ህጉ የገዥው ፓርቲን ስልጣን ለመጠበቅ እየዋለ ነው፡፡›› አቶ ይድነቃቸው ከበደ
የሰማያዊ ፓርቲ የብሔራዊ ምክር ቤት አባል እና የሰሜን ጎንደር የዞን ሰብሰቢ አቶ አግባው ሰጠኝ ጎንደር ከተማ ውስጥ ጥቅምት 25/2007 ዓ.ም በገዥው ፓርቲ ደህንነቶች መታሰሩን የሰማያዊ ፓርቲ የህግ ጉዳይ ኃላፊ አቶ ይድነቃቸው ከበደ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
agebaw setegn
ፖሊስና የደህንነት ኃይሎች አቶ አግባው ሰጠኝን ወደ መኖሪያ ቤታቸው በመውሰድ ከ1 ሰዓት ተኩል በላይ ፍተሻ እና ብርበራ በማካሄድ ስፍራው ወደልታወቅ ቦታ እንደወሰዷቸው ጎንደር ውስጥ የሚገኙ የፓርቲ አመራርና አባላት ገልጸዋል፡፡
አቶ አግባው ከተያዘ በኋላ ጎንደር ከተማ የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት እንዲሁም ዘመዶቹ ፖሊስ ጣቢያዎችን እየዞሩ ቢያጠያቁም ‹‹ነገ ጠዋት ጠይቁ!›› ከሚል ትዕዛዝ ውጭ የታሰረበትን ማወቅ እንዳልቻሉ ገልጸዋል፡፡
አቶ አግባው ሰጠኝ ከመታሰሩ በፊት የማያውቃቸው ሰዎች ለእሱ ተቆርቋሪ መምሰል ‹‹አርፈህ ስራህ ስራ፣ ከሰማያዊ ጋር የምታደርገውን እንቅስቃሴ አቁም፣ አዲስ አበባ ያሉት የፓርቲው አመራሮች ግንኙነታቸው ከሌላ ሰው ጋር ነው፡፡ ስለማታውቅ ነው፡፡›› ይሉት እንደነበር እንዲሁም ከመታሰሩ በሁለት ቀናት በፊት ከደህንነት የተላኩ ነኝ የሚል ግለሰብ ‹‹ከዚህ የማትወጣ ከሆነ በህይወት ላይ እርምጃ እንወስዳለን፣ መጀመሪያም መክረንሃል›› ብለው ይዝቱበት እንደነበር የሰማያዊ ፓርቲ የህግ ጉዳይ ኃላፊ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡
ፖሊሶች የያዙት የፍርድ ቤት ማዘዣ ‹‹በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩ በመሆናቸው አስፈላጊውን ፍተሻ ማካሄድ እንዲችሉ›› እንደሚል መረጃው የደረሳቸው የህግ ጉዳይ ኃላፊው ‹‹በመጀመሪያ የፀረ ሽብር አዋጁም ተቀባይነት የሌለውና የተለየ ሀሳብ ያላቸውን ሰዎች ለማሰቃየትና ገዥውን ፓርቲ ለመጠበቅ የወጣ ህግ ነው፡፡ አሁንም የምናየው በሰላማዊ መንገድ የሚንቀሳቀሱ አባላት በመጠናከራቸው ለመገደብ እየተጠቀመበት ነው፡፡›› ሲል ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡
በተመሳሳይ የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት አቶ ዮናታን ተስፋዬ ‹‹ጎንደር አካባቢ በማህበራዊና ሌሎች ችግሮች ምክንያት በገዥው ፓርቲ ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ አለ፡፡ አቶ አግባውን ጨምሮ ሌሎችም አመራሮችና አባላት ህዝቡን ስለሚያስተባብሩ ነው የታሰሩት፡፡ ጎንደር ውስጥ ያለውን የህዝብ ጥያቄ ለማፈን የተደረገ ነው፡፡ ከአሁን ቀደም አርባ ምንጭ ላይ ህዝቡ ተቀባይነት ያላቸውና ጠንካራ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ አመራሮችና አባላት ላይ ተመሳሳይ እስር ተፈጽሞባቸዋል፡፡ ሌሎች አባላትና አመራሮችም አሁንም ድረስ እያዋከቧቸው ነው፡፡›› ብሏል፡፡
ኃላፊው አክሎም ‹‹በተለይ በአሁኑ ወቅት ፓርቲዎች በጋራ እየሰሩ በመሆኑ ስጋት ውስጥ የወደቀው ገዥው ፓርቲ እንቅፋት ለመፍጠር ነው እስራቱን የሚፈጽመው፡፡›› ሲል ገዥው ፓርቲ ጠንካራ እንቅስቃሴ የሚያደርጉትን የፓርቲ አመራሮችና አባላት በማሰር ፓርቲውን ለማዳከም የሚያደርገው የተለመደ ስልት መሆኑን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡ በተመሳሳይ ሰሞኑን በመኢአድ፣ አንድነትና አረና አመራሮችና አባላት ላይም ተመሳሳይ እስር እንደተፈጸመ ተዘግቧል፡፡

Tuesday 4 November 2014

ጎተራው ወዴት ነው?¡

(ጌታቸው አበራ)
gettera
ሀገር በብረት ሲታጠር — ‘ግንቦት ሃያህ’ ሲከበር፤
አዲስ ዓመት በመጣ ቁጥር — ዘመን በዘመን ሲቀየር፤
የስራ-ፈቶች ስብስብ መንጋ — ‘ፓርላማህ‘ሲከፈት ሲዘጋ..፤
ሱፍህን ገጥግጠህ — ከረባትህን ጠፍረህ፣
ወዝህን አሳምረህ — ካሜራ ፊት ቀርበህ፣
ጉሮሮህን..ጠርገህ — ፊትህ የከመርከውን ‘ሃያ ገጽ’ ገልብጠህ፣
ቁጥር እየቆጠርክ፣ አሃዝ እየጠራህ…፣
“ምናምን..ሺ.ቶን፣ ሚሊዮን ስልቻ፣
አምርተን አስገባን በዚህ ዓመት ብቻ…”፣
እያልክ ስትደሰኩር — ትንፋሽህ እስኪያጥር፣
ሰምቼህ ሳበቃ፣ የግርምት ጥያቄ እስኪማ ልሰንዝር፤
በልበ-ሙሉነት “ጠግብን በላን” ያልከው፣
ሕዝቡን ቆጥረህ ይሆን? ወይስ የቤትህን ያንተኑ ግሳት ነው?!
ስርህ ተግተርትሮ፣ ላብ እያሰመጠህ፣
ያቀረብከው ‘ሪፖርት‘ እንዲያ ተውረግርገህ፣
የራስህን በጀት፣ የጓዳህን ወሬ፣
ወይስ የምስኪኗን ኢትዮጵያ ሀገሬ?
እኮ ታዲያ የታል? የተትረፈረፈው፣
የእህል ዘር፣ የእህል ምርት..የት የተከተተው?
እባክህ ንገረን ጎተራው ወዴት ነው?!
እንደልቡ አፍሶ ሕዝብ የሚጠግብበት፣
የተትረፈረፈው…የተከማቸበት፣
ንጉስ አብዱላህ አገር ከሳዑዲ አረቢያ?
ከ’ካራቱሪ’ አገር ወይስ ከኢንዲያ?
ወይስ ከ’ሸራተን’ ከ’ሚድሮክ’ መጋዘን?
የት ይሆን ጎተራው? በነካካ አፍህ ጨክነህ ብትነግረን¡
አገር ያለውማ ሕዝቡን እሚያከብር፣
የራሱ አልበቃው ሲል ለመጥገብ ሲቸገር፣
ከሞኝ ደጃፍ ወርዶ፣ ሸጋ ሞፈር ቆርጦ፣
ባላድ፣ በስሙኒ..ጋሻ መሬት ገዝቶ፣
ያገር ደን መንጥሮ — የሰው-ሰው አባሮ፣
መሬት አለስልሶ፣ ውሃ ቦዩን ጠልፎ፣
ቀለቡን ይሰፍራል፤ ምርቱን አትረፍርፎ፤
እሱ ነው እሚያምርበት!
አደባባይ ቆሞ ለሕዝብ ቢያቀርብ ‘ሪፖርት’።
እንጂማ አንተማ፣ ክፋት-ምቀኝነት…
መቅኔህ ድረስ ዘልቆ፣ አጥንትህን ቦርቡሮ፣
መላ ሰውነትህ በጥላቻ-በእልህ..በቅንቅን ተወሮ፣
በዚያቹ በምስኪን ባዶ ጎጆው ቀንተህ፣
ያያት-ቅድማያቱን ርስት ቀዬ ነጥቀህ፣
በባዶ አንጀቱ በጥይት ቀጥቅጠህ፣
አገርህን ንቀህ፣ ወገንህን ጠልተህ፣
በ’ፌደራል ፖሊስ‘ ለባዕድ ዘብ ቆመህ..፣
ካሜራ ፊት ቀርበህ አረፋ እየደፈቅህ፣ “ጠግበን በላን” ያልከው፣
ምጸት ነው! ምጸት ነው! ለምስኪን ያገር ልጅ ሁለተኛ ሞት ነው!!
ጌታቸው አበራ
ጥቅምት 2007 ዓ/ም (ኦክቶበር 2014)

“ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ” የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ፕሮግራሙን ይፋ አደረገ

የ24 ሰዓት (የአዳር) የተቃውሞ ሰልፍ ተጠርቷል
9 parties
ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም 9 ተቃዋሚ ፓርቲዎች የመሰረቱት ትብብር “ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ” በሚል ለአንድ ወር የሚቆይ የመጀመሪያ ዙር የህዝባዊ ትግል ፕሮግራሙን ዛሬ ጥቅምት 25/2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ይፋ አደረገ፡፡
“ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ የማይታሰብ በመሆኑ የተዘጋውን በር ለመክፈት የ‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ› በሚል የፕሮግራም መርሃ ግብር ለመክፈት ወስኖ የመጀመሪያው ዙር እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ከተማ ለማድረግ” እንዳዘጋጀ ያሳወቀው ትብብሩ የትግሉ ዓላማ ፍትሃዊ ምርጫ እንዲኖር የሚያስችል መሆኑን ገልጾአል፡፡
“ምርጫ ቦርድ ለገዥው ፓርቲ ያለውን ወገናዊነትና ጉዳይ አስፈጻሚነት ፍንትው አድርጎ አሳይቷል” ያለው መግለጫው በመጀመሪያ ዙር የአንድ ወር ፕሮግራሙ 6 ዋና ዋና ተግባራትን ለመፈጸም ዝርዝር እቅዶችን አውጥቶ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል፡፡ በህዳር ወር የሚያከናውናቸው ተግባራትም፡-
1. በቤተ እምነት ጸሎት እንዲደረግና ጥሪ ማቅረብና አማኞች እንደየ እምነታቸው ተሳትፎ እንዲያደርጉ ማድረግ
2. የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባዎችን ማድረግ
3. የተቃውሞ ድምጽ ማሰማት (ሰላማዊ ሰልፍ)
4. ለመንግስት ተቋማት ደብዳቤ ማስገባት
5. በምርጫ ዙሪያ የፓናል ውይይቶችን ማድረግና
6. የህዝብን ተሳትፎ ማበረታታትና ድጋፍ ማሰባሰብ እንደሆኑ በመግለጫው አሳውቋል፡፡
ከእቅዶቹ መካከልም በሶስት ተከታታይ እሁዶች በተለያዩ የአዲስ አበባ ክፍሎች 3 የአደባባይ ስብሰባዎች እንደሚኖሩ፣ በመጨረሻው መርሃ ግብርም ህዳር 27ና 28 በፕሮግራሙ ማጠቃለያነት የ24 ሰዓት (የውሎና የአዳር) የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚደረግ የትብብሩ ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ገልጸዋል፡፡
በገዥው ፓርቲና በምርጫ ቦርድ ጥምረት ይፈጸማል ያለውን ህገ ወጥ ተግባር በመታገል ለሰላማዊ ትግሉ አወንታዊ አስተዋጽኦ ለማበርከት እስከመጨረሻው በፅናት ለመቆም መዘጋጀቱን የገለጸው ትብብሩ በአገር ቤትና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን፣ በትብብሩ ሂደት ቆይተው እስካሁን ያልፈረሙና ሌሎች ፓርቲዎች እና የዓለም አቀፉ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ከጎኑ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርቧል፡፡ (በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር)

ፕሮፌሰር መስፍንን ለቀቅ

ፕሮፌሰር መስፍንን ለቀቅ
አንተነህ መርዕድ
ህዳር 2014
በዙህ ጉዳይ ላይ ለመጻፍ በሁለት ምክንያቶች ከራሴ ጋር ብዙ ታግያለሁ። መጀመርያ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም አይደለም ለራሳቸው፤ ለሌላም የሚተርፍ አንደበት አላቸውና ራሳቸው መልስ  ይስጡ በማለት ሲሆን ሁለተኛው ምክንያቴ ደግሞ ትልልቅ አገራዊ ጉዳይ እያለ በዚህ ጠባብ ነገር መጠመድ ለማን ይበጃል በሚል ነበር።በሁለቱም ትክክል አልነበርሁም። ፕሮፌሰር መስፍን በግል ደረጃ የወረደ እንቶ ፈንቶ መግባት ስብዕናቸው ስላልፈቀደ ንቀው መተዋቸው ትክክል ነበር። በሌላ በኩል ደግሞ አንዳንድ ግለሰቦች ሆነ ቡድኖች ትልልቅ የአገር አድባሮችን ሲያዋርዱ በዝምታ መመልከቱም ተገቢ አለመሆኑን ተገንዝቤአለሁ።
Prof. Mesfin
አንድ ህብረተሰብ ከመካከሉ የሚወጡ ፋና ወጊ መሪዎችን በመንከባከብ፤ ሲሳሳቱ በማረም  ቢያሳደግ ለበለጠ ሰላምና ብልጽግና ያበቃዋል። ይህንን እውነት በበርካታ አገሮች አይተናል።በህይወት ሳሉ ተሞግሰውና ተከብረው፤ እውቀታቸውንና ጉልበታቸውን የበለጠ ለአገራቸው ጥቅም ላይ እንዲያውሉ ሲበረታቱ፣ ከሞቱም በኋላ ሃውልትና መታሰብያ ተሰርቶላቸው ትውልዱ አርዐያቸውን እንዲከተል ይደረጋል። እንዳለመታደል ባለፉት አርባ አመታት በአገራችን በአምባገነን መሪዎችና አንዳንድ ወገኖች የተያዘው አደገኛ መንገድ የአገሪቱን ትልልቅ ሰዎች ማዋረድ፣ መሪና ምሳሌ የሚሆነን ማሳጣት ነው። በተለይም በአብዮቱ ዘመን የምስራቁን ርዕዮት በአገራችን ለመትከል ታጥቀው የተነሱ ወገኖች ትልልቅ ኢትዮጵያውያንን ኢላማ አድርገው እንደነበር የምንዘነጋው አይደለም። ብዙ ለአገራቸው አስተዋፅዖ ያደረጉ አዛውንትና ትልልቅ ዜጎች ራሳቸውን ትልቅ አድርገው በሚመለከቱና ትንንሽ ጭንቅላት ባላቸው ከንቱዎች ተሰድበዋል፣ ተዋርደዋልም። እነዚህ ብርቅ ኢትዮጵያውያን  ከትውልድ ትውልድ ሊተላለፍ የሚችል ስራቸው በሁሉም ልቦና ያለ ሲሆን ሰዳቢዎቻቸውና አዋራጆቻቸው ግን ያሰቡት ሳይሳካ መክነው ቀርተዋል።
ዛሬ በህይወት የሚገኙትና በአዛውንት እድሜአቸው ደከመኝ ሳይሉ በተባ አንደበታቸው ጥልቅ የሆነ እውቀታቸውንና ተመክሮአቸውን ለወገን እያበረከቱ ያሉት ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም  ብዙዎች የምንሳሳላቸውና የምናከብራቸው ቢሆንም ሁሉም ይወዳቸዋል ብለን አንጠብቅም። ሶስቱንም የአገራችንን   የአምባገነን ስርዓቶች አጥብቀው የታገሉ፣ ድፍረትና እውቀታቸው የመጠቀ፣ ለሃብት፣ ለስልጣን ሆነ ለግል ድሎት ቦታ የማይሰጡ፣ ትክክል ነው ብለው ያመኑትን ከመናገርና ከማስተማር ግንባራቸውን የማያጥፉ መሆናቸው ለብዙው ኢትዮጵያዊ እንደ አርአያ (ሮል ሞዴል) ሆነው እንዲታዩ ያደረጋቸውን ያህል በአንዳንዶች የአገርና የህዝብ ጠላት ሆነው እንዲታዩ ጥረት ይደረጋል። ይህ ትችቴ የፕሮፌሰር መስፍንን አንዳንድ ሃሳቦች በሃሳብነት የሚሞግቱትን ጨዋ ሰዎች አይመለከታቸውም። መስፍን ወልደማርያምን ፍጹም ናቸው የሚል ሃሳብ አይወጣኝም፣ እሳቸውም ይህንን እንደማይቀበሉ አምናለሁ። ትችቴ ፈረንጆች “ህፃኑን ከእጣቢው ጋር መወርወር” እንደሚሉት ሁሉ የፕሮፌሰሩን የተወሰነ ሃሳብ በስህተትነት ይዘው ጨዋነት በጎደለው ሰብዕናቸውን ለማጥፋት የዘመቱ ወገኖች ዓላማቸው አደገኛና አጥፊ መሆኑን ለማስገንዘብ ነው።
የፕሮፌሰሩን አንዳንድ ሃሳብ የማይቀበሉ የተወሰኑ ግለሰቦች ጽሁፎቻቸውንና ንግግሮቻቸውን እየነቀሱ ጨዋነትና እውቀት ላይ የተመሰረተ ትችቶችን ማድረጋቸው ለብዙዎቻችን እውቀት መዳበርና የሃሳብ ጥራት ገንቢ ሚና ተጫውተዋል። ፕሮፌሰር  መስፍን ወልደማርያምም የምርምርና የእውቀት  ሰው በመሆናቸው ይህንን ዓይነት ትችት እንዲዳብር የሚስማሙበት ይመስለኛል። የብዙዎችን ላቆየውና በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ካንድ ወገን የሚሰነዘረው ከባህላችን ውጭ የሆነ ዓላማው ግልጽ ያልሆነ ስድ በሚያሰኝ የመንገድ አዳሪ ቋንቋ የስድብ ውርጅብኝ  በኒህ አዛውንት አባት ላይ ሲወርድባቸው ዝም ብሎ መመልከቱ ለህሊና ይከብዳል።
ነሃሴ 25 ቀን 2006 ዓ ም  “ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት”  በራሱና በሌሎችም ማህበራዊ ድረገፆች “ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም በዐማራው ቁስል ላይ ጨው ነሰነሱ! የ<<ዐማራ የለም>> አቋም የክህደት ወይስ የመሳት?” በሚል ርዕስ የበተነው መግለጫ ተልዕኮው ምን እንደሆነ ያልለየና አሳዛኝ ነበር። በዚህ አምስት ገጽ በሞላ አማራው ላይ ስለደረሰ ግፍ በሚዘረዝር እውነትን ባዘለ ይዘቱ ላይ ተቃውሞ የለኝም። በመሬት ላይ ያለው ተጨባጭ እውነት ከዚያም የከፋ በመሆኑ ማንም ሊያደበዝዘው አይቻለውም። ነገር ግን በፕሮፌሰሩ ላይ የተሰነዘረው ቃል ተገቢ አልነበረም።
መለስ ዜናዊ ኢትዮጵያዊ የሆኑ ትልልቅ ሃሳቦችንና ሰዎችን አኮስምኖና ገድሎ የራሱን ትልቅነት ለመገንባት ሲጥር ለመጀመርያ ጊዜ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያምን ነው በቴሌቪዥን ሊሞግት የሞከረው። ሁሉም እንደተከታተለው በክርክሩ ወቅት የመለስ ትንሽነት ነበር ጎልቶ የወጣው። በዚያ ውይይት ኢትዮጵያውያንን በጎሳ ከፋፍሎ ሊበትን ያሰበውን ዓላማ በመስፍን ወልደማርያም አፍ ላይ ሊያስቀምጥ ሲል “አማራ የሚባል ጎሳ የለም” ብለው በስሙ እንዳይነገድበት ያቀረቡት መከራከርያ እስከዛሬ ድረስ ወያኔ በሰፋላቸው የጎሳ እጀጠባብ ማጌጥ የሚፈልጉ ሁሉ የሚያመነዥኩት ሃሳብ ሆኗል። በቅርቡ ፕሮፌሰሩ በሸገር ሬድዮ በሰጡት ቃለ መጠይቅ ይሄው ሃሳብ መደገሙ ካስቆጣቸው ወገኖች ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት አንዱ በመሆኑ ይመስላል ይህንን መግለጫ አይሉት ስድብ አሰራጭቷል። ባከታታይም የሞረሽ ደጋፊዎች ነን የሚሉትም ትኩረታቸው ቆምንለት የሚሉት አማራ ነፃ የሚወጣበትን መንገድ ከመሻት ፕሮፌሰሩን በመተቸት ተጠምደዋል።
ተደጋጋሚ የሆነ ከሃሳብ ይልቅ በግል ሰብዕና ላይ ያተኮረ ትችት አስነዋሪ ከመሆኑም በላይ ፕሮፌሰሩን በመሳሰሉ ታላላቅ ኢትዮጵያውያን ላይ የሚሰነዘረው ስድብ በአገር ላይ እንደሚሰነዘር ይቆጠራልና በዚህ መግለጫ ያነበብሁት ስድብ አሳዝኖኝ ከበርካታ ጓደኞቼም ጋር ተነጋግረንበት አልፈነው ነበር። እንዳጋጣሚ በፈረንጆች አቆጣጠር መስከረም 7 ቀን 2014 በቶሮንቶ ካናዳ የኢትዮጵያውያንን አዲስ ዓመት በክሪስቲ አደባባይ እናከብር ነበርና ብዙ ህዝብ በሚርመሰመስበት የደመቀ በአል መሃል የሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት መሪ የሆኑትን አቶ ተክሌ የሻውን አገኘኋቸው። ደስ ብሎኝ ራሴን ካስተዋወቅሁ በኋላ በወጋችን መሃል በቅርቡ ከወጣው መግለጫቸው አምስት ገጽ እውነት ውስጥ ጨዋነት የጎደለው ስድብ ተገቢ እንዳልነበር ነገርኳቸው። የሰማሁት መልስና ለፕሮፌሰሩ ያላቸው ጥላቻ አስደነገጠኝ። ለአማራው ህዝብ መብት ቆሜያለሁ ብለው አደባባይ የወጡ  እኒህ ሰው አንዱን ታላቅ ወገናቸውን በሰብዕናቸው ገብተው ሲዘልፉ መመልከት ዓላማቸውን ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ ሆኖ አገኘሁት። ስልሳዎቹ ውስጥ የሚሆኑ እኒህ አዛውንት ሌላው በእድሜ፣ በእውቀትና በተመክሮ ለሚበልጧቸው ክቡር ሰው የሚሰጠውን የጨዋ አማራ ባህል ከውስጣቸው አላየሁም። ስለሆነም ውይይቴን ብቀጥል የበለጠ ህሊና የሚያቆስል ነገር እንደምሰማ በመገመት ተሰናበትኋቸው። የመግለጫውን ስድቦች ነቅሼ ላቅርብላችሁ። (ሙሉውን ጽሁፍ ከሞረሽ ወይንም ከሌሎች ድረገጾች ፈልጋችሁ አንብቡ)
“…የፕሮፌሰር መስፍንም ክርክር ጭፍን ክህደት ወይም መሳት (መጃጀት) አልያም ቀቢፀ-ተስፋ የተሞላው ቁጭት ከመሆን አያልፍም።……ከመሳት (መጃጀት) የመነጨ ከሆነ ግን አያድርስ! እንዲህ እስኪሆንስ ፈጣሪን “አታቆዬን” ከማለት ሌላ ምን ይባላል።
“…ፕሮፌሰር መስፍን ክህደት የመታወቂያ ባህሪያቸው ስለሆነ…..”
“….ከክህደት ባህሪ በተጨማሪ በዕድሜ መግፋት ምክንያት የመጣ፣ የኋላን ያለማየት እና የመሳት አባዜ የገጠባቸው መሆኑን የሚያመለክት ነው።….”
(ስርዞቹ ለአፅንዖት የተጠቀምሁባቸው የእኔ ናቸው)
ስድቦቹ ሲጠቃለሉ ሁለት ፀያፍ ጽንሰ ሃሳብ ይዘዋል፤ ክህደትና መሳት(መጃጀት)
ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያምን በክህደት መክሰስ በጣም የሚያሳዝን ነው። መስፍን ወልደማርያም ሁሉንም ኢትዮጵያዊ አማራ፣ ትግሬ፣ ኦሮሞ፣ ወላይታ፣ አገው፣ ጃንጂሮ፣ ጉሙዝ ሳይሉ ርሃቡን፣ ጥማትቱን፣ ስቃዩን፣ እስሩን፣ ግድያውን፣ ግርፋቱን፣ እንግልቱን በጠረጴዛ ዙርያ ውይይትና መግለጫ በማውጣት ሳይሆን ውስጡ ሆነው የታገሉትና የሚታገሉትም። ስቃዩን በአካልም በመንፈስም የሚጋሩት ጀግና ናቸው። ያውም እንደ እኔ የወያኔ ጫና ወላፈኑ ሲዋጀው ነፍሱን በጨርቁ ቋጥሮ፣ ጅራቱን ቆልፎ ከአገሩ የሸሸ ይቅርና፤ አገር ውስጥ ዳፋውን እየተጋቱ ያሉትም መስፍን ወልደማርያምን በክህደት አይወነጅሉም። እዚህ ሆኖ ማቅራራትና እዚያ ሆኖ ህዝብ መሃል እየኖሩ፣ እየተለበለቡ፣ እየታሰሩ  መታገል የብርሃን ዓመት ያህል ይራራቃልና። ርቆም ቢሆን ትግልያስፈልጋል ብሎ ላመነ ትግሉን በእውነትና በጨዋነትየተመራ ቢያደርገው የተመረተ ያደርገዋል።
የትግራይና የወሎ ህዝብ በርሃብ ሲረግፍ ሁሉም ጭንቅላቱን አሸዋ ውስጥ እንደከተተ ሰጎን አንገቱን በደፋበት በዚያ ፈታኝ ወቅት ህይወታቸውን አዳጋ ላይ ጥለው የደረሱላቸውና ዓለም እንዲያውቀው ያቀናበሩት ፕሮፌሰር መስፍን መሆናቸውን መካድ ነው ከሃዲነትሊሆን የሚችለው። የዐማራ ነገድ አለ የለም የሚል እንቶ ፈንቶ ለፖለቲካ ነጋዴዎች እንጂ ለመስፍን ወልደማርያም ሆነ ለዐማራው አንዲት ነገር አይፈይድም።
ለነገሩማ ታምራት ላይኔ፣ ተፈራ ዋልዋ፣ አዲሱ ለገሰ፣ በረከት ሲሞን፣ ደመቀ መኮንን፣ አለምነው መኮንን….አማራው አለ ይላሉ እኮ! የሚያዋርዱት፣የሚገድሉትና የሚያስገድሉት ደግሞ እነሱ ናቸው። ተግባር እንጂ መናገር ማንነትን የማያሳይ ለመሆኑ እነዚህ ሰዎች ጥሩ ምሳሌዎች በመሆናቸው፤ የሚለፈልፉትን ሁሉ ማመን ከባድ የሚሆነው ለዚህ ነው። ዲያቪሎስም ከወንጌል ይተቅሳል ይላሉ በመኖር ተመክሮ የበሰሉ ዘመዶቻችን።
በደኖ፣ አርባ ጉጉ፣ ጋምቤላ፣ አሶሳ፣ ጎንደር አደባባይ ኢየሱስ ወዘተ…አማራው ሲጨፈጨፍ በእውቀታቸው፣ በገንዘባቸው፣ በጉልበታቸው የደረሱለት፤ በአገርም በዓለምም የሞገቱት፣ ባቋቋሙት የኢትዮጵያ ሰብዐዊ መብት ጉባኤ (ኢሰመጉ)ና በግላቸው የደከሙትን ብርቅዬ ታጋይ ሲደክሙ ከጎናቸው ያልነበሩ በከሃዲነት ሊወነጅሏቸው የሚያስችል የሞራል ብቃት ያለ አይመስለኝም። ሙሾ ማውረድ ለእንደኔ አይነት ደካሞች ቀላል ነው። በተለያየ መንገድ ደም መላሽ የሆኑትን ጀግኖችና ትልልቆችን በመጥለፍ ጀግናና ትልቅ መሆን የሚገኝ የሚመስላቸው አይጠፉም። ከዚህ በፊትም ነበሩ። የኋላ ኋላ መጋለጡ ግን የማይቀር እውነት ነው።
ወያኔ ኢትዮጵያን ለመበተን በመድረክ ሲያውጅ፤ ይህንን ዘረኛና ከፋፋይ ዓላማ በብቸኝነት የተቃወሙት ታላቁ ኢትዮጵያዊ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ነበሩ። በዚያም አልቆም ብሎ በአማራው ላይ እልቂት ሲታወጅና ሲታረድ ያ ትልቅና ኩሩ ህዝብ መገደል የለበትም ብለው ከፊት የቆሙትና ለመስዋዕት የቀረቡት የቁርጥ ቀን ልጅ አስራት ወልደየስ ናቸው። ወያኔ ደመኛ ጠላት አድርጎ ሊያጠፋቸው ሲነሳ እንዲወግራቸው ደንጋይ ሲያቀብሉ የነበሩት “ለአማራ ቆሜአለሁ” ብለው ብቅ ሲሉ ደግሞ ታሪክና ህዝብ በትዝብት እየመዘገበ መሆኑን ሊዘነጉት አይገባም። ፕሮፌሰር አስራትን ወያኔና ደጋፊዎቻቸው በአካል እንዲጠፉ አድርገው ይሆናል፤ በስራቸው በህዝብ ልብ ላይ መሆናቸውንና ባለታሪክነታቸውን የሚያጠፋ የምድር ሃይል አይኖርም። በተመሳሳይ ሁኔታ የመስፍን ወልደማርያምን ስራና ትልቅነት ደካሞች የሚያጠፉ መስሏቸው ከሆነ ከታሪክ ሊማሩ ይገባል።
 2
( ሰዳቢዎቻቸው ይህን እስኪመስሉ በእስር ካንገላታቸው ወያኔ የሚለዩት በምን ይሆን?አክባሪዎቻቸውም ይሸልሟቸዋል)
መስፍን ወልደማርያም ትናንት ለነበረው አምባገነን መንግስት ካድሬ ሆነው አገልግለው ዛሬ ታጋይ ሆነው ብቅ ያሉ ሳይሆን አሁን ከእንቅልፋቸው ባንነው “አማራ ተበደለ” ብለው ከሚጮሁ ወገኖች በፊት በተደጋጋሚ አምባገነን ስርዓቶችን ተጋፍጠው ህዝቡ መራቡን ያጋለጡ፣ ለእርዳታ ማንም ሳይደርስ የደረሱ፤ ታሰረ፣ ተገረፈ፣ ተገደለ የተባለውን ቀድመው በመገኘት የታደጉ የተግባር ሰው ስለሆኑ በጠረጴዛ ዙርያ ለሚታኘክ የብሄር ብሄረሰብ ቲዎሪ ጊዜ የላቸውም። ስብዕናቸውና ትልቅነታቸው ወደዚህ ትንንሽ ነገር አይመራቸውም። አማራው ኢትዮጵያዊ ነኝ ብሎ ራሱን በመስዋዕትነት ካስቀመጠበት ልዕልና አውርዶ በጠባቡ የብሄር ስልቻ ውስጥ ለመክተት የሚታገሉ ወገኖች አላማቸውን በጨዋነት ማስረዳት እንጂ በተራ ብልግና ትልልቆችን ማዋረድ “የቆሙለት” የአማራው ባህልም አይደለም።
ሌላው ፀያፍ የሆነው ሁለትኛው ስድባቸው መስፍን ወልደማሪያምን የሳተ (የጃጀ) በሚል ለማዋረድ የሰነዘሩት ስድባቸው ነው። ምን ዐይነት ጤነኛ አዕምሮ ያለው ነው በጎንደር፣ በጎጃም፣ በወሎ፣ በሸዋ የሚገኝ አማራ ብቻ ሳይሆን ሌላውም ኢትዮጵያዊ ፊት እድሜ የጠገበን የአገር አዛውንት የጃጀ ብሎ ደፍሮ የሚሳደብ? ጃጅተውስ ቢገኙ ምን ነውር አለው? በአባቱ ገበና የሚስቅ ምን ዓይነት እርጉም ነው? እንደ አገሬ ደንጋይ ምንም ሳይሰሩ ተጎልተው የሸበቱ ሠርቶና ደክሞ ያረጀን፣ የጃጀን ይንከባከቧል እንጂ አደባባይ ለስድብ ያቀርቧል?
የሚገርመው መስፍን ወልደማርያም ለመጀመርያ ጊዜ መለስ ዜናዊን ስለ አማራው የተከራከሩት የዛሬ ሃያ ሶስት ዓመት በግምት በአሁኑ ሰዓት አቶ ተክሌ የሻው ባሉበት እድሜ ላይ ሆነው ነው። የዛን ጊዜ መስፍን ወልደማርያም ይህንን ሃሳብ የተናገሩት አርጅተውና ጃጅተው ነው ከተባለ አቶ ተክሌ የሻው ሆኑ ጓደኞቻቸው ተስፋ የላቸውም ማለት ነው። ይህንን ስድብ የጻፉት ሆነ መግላጫ ሆኖ እንዲወጣ ያደረጉት ጃጅተዋል ማለት ነው። በእነሱ አባባል ከሆነ ማለቴ እንጂ እኔ ማንንም በእግዚአብሄር አምሳል የተፈጠረ ሰው በእድሜውና በጤናው የመሳለቅ ብልግና ነውርነቱን እየሰማሁ ነው ያደግሁት። ነገር ግን መስፍን ወልደማርያም  በአሁኑ እድሜአቸው እንኳ ከነአቶ ተክሌ ሺህ ጊዜ የሰላ አዕምሮ እንዳላቸው አውስትራልያ ሰሞኑን ያወያዩአቸውን ኢትዮጵያውያንን በመጠየቅ መረዳት ይችላሉ። ወይንም ፕሮፌሰሩ በየቀኑ በብሎጋቸው የሚያሰፍሩትን ማንበብ አለባቸው። አንድ ኢሜል መመለስ ባህል ማድረግ አቅቶን በምንደፋደፈው ደካሞች መካከል ቀን በቀን የዓለምን ሁኔታ እየተከታተሉ ብዙዎቻችንን እያስተማሩ ያሉ አዛውንት ጃጅተዋል ማለት ምን ተፈልጎ ነው? በነፃው ዓለም ትልልቅ ከተሞች ሃያ ሰው አሳምኖ መሰብሰብ የማይችሉ ሰዎች የመስፍን ወልደማርያምን አዕምሮ ለመመዘን ሲሞክሩ ያሳዝናል። ባዶ በርሜል ብዙ ይጮሃል ብለው ይሆናል መስፍን ወልደማርያም መልስ ያልሰጧቸው። እውቀት በተግባር ይፈተኗል። ለአማራው አለህ የለህም የሚለው ቀረርቶ ጀሮው ጫፍ አይደርስም። የመንዝ አማራ ከቀዳማዊ ኃይለስላሴ ሃረጉን ቢስብ እንደማይጠቅመው አሳምሮ ያውቃል። እንዳይገደል፣ እንዳይታሰር፣ እንዳይዘረፍ በተጨባጭ የሚከላከልለት እንጂ በስሙ የንግድ ፈቃድ አውጥቶ የሚነግድበት አይደለም የሚፈልገው። ስለፕሮፌሰር መስፍን ገድል ብዙ የሚያውቁ፣ አብረው የሰሩ፣ ሃዘናቸውንና ድካማቸውን የተካፈሉ ዝም ብለው በተቀመጡበት ሰዓት አላስችለኝ ብሎ ለፈለፍሁ እንጂ ታሪክና በርካታ አዋቂዎች እየታዘቡ እንደሆነ አውቃለሁ።
ለፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም በእግዜብሄር አምሳል የተፈጠረ ሰው ክቡርነቱ እንጂ አማራ፣ ኦሮሞ፣ ትግሬ፣ ወላይታ… የሚለው የታፔላ ስም መቀነስ መጨመሩ ፋይዳ አይሰጣቸውም። ለከፋፋዮች፣ ለፖለቲካ ነጋዴዎች፣ የማንነት ቀውስ ውስጥ ለተዘፈቁ ከንቱዎች ይጠቅም ይሆናል። እየጠቀመም ነው።
አፄ ቴዎድሮስን፣ አፄ ዮሃንስን፣ አፄ ምንይልክን፣ ንጉሥ ተክለሃይማኖትን፣ ቀዳማዊ ኃይለስላሴን፣ ንጉሥ ጦናን፣ አሉላ አባ ነጋን፣ በላይ ዘለቀን፣ ሱልጣን አሊሚራህን፣ አባ ጅፋርን፣ ጄኔራል ጀጋማ ኬሎን፣ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስን፣ ባሮ ቱምሳን፣ ተስፋዬ ደበሳይን፣ አብርሃም ደቦጭን፣ አበበ አረጋይን፣ ሌንጮ ለታን፣ ጄኔራል ከማል ገልቹን፣ አንዳርጋቸው ጽጌን፣ እስክንድር ነጋን…ወዘተ እነዚህን ሁሉ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰዎች በሰብዕናቸውና በኢትዮጵያዊነታቸው እንጂ በጎሳቸው፣ በቋንቋቸው  እየከፋፈለ  የሚያይ ሳያረጅ የጃጀ፣ እውቀት ሳይገበይ የሳተ፣ ያለዚያም የፖለቲካ ንግድ ፈቃድ አውጥቶ የሚሮጥ ሸፋጭ ነው።
ትችቴን አንድ የውጭ አገር ፀሃፊ የኢትዮጵያውያንን  ጨዋነት በገለጸበት ታሪክ ልደመድመው ወደድሁ። የጎደለን እውነተኝነትና ጨዋነት ስለሆነ። ጸሃፊው ኢትዮጵያ ከጣልያን ጋር ስትዋጋ ከጎኗ ተሰልፎ ብዙ መስዋዕት የከፈለውና ያየውንም እውነት የመሰከረው አዶልፍ ፓርለሳክ ነው። “የሃበሻ ጀብዱ” በሚለውና ተጫነ ጆብሬ መኮንን  በተረጎሙት ገጽ 111 ላይ እንዲህ ይቀርባል።
በአድዋ ጦርነት ጊዜ አምባላጌን ይዟት ለነበረው የጣልያን ሻለቃ ቶለሲን ራስ መኮንን እንዲህ ብለው ነበር።
“ውድ ወዳጄ ሻለቃ ቶለሲ፤ ጀግንነትህንና ቆራጥነትህን አውቃለሁና አከብርሃለሁ። አደንቅሃለሁ።ይሁን እንጂ በዚህ ጦርነት ትሸነፋለህ። ስለዚህ አምባላጌን ለቅቀህ ወደ መቀሌ ሽሽ። እንዲህ በሰላም አምባላጌን ለቅቀህ ከወጣህ ጦርህ እንደታጠቀ ወደ መቀሌ ሸሽቶ ያለችግር እንደሚገባ ቃሌን እሰጥሃለሁ። ወዳጄ ቶለሲ ያለህን ጦር አውቃለሁ። እኔ አስር እጥፍ ጦር አለኝ። እና ኋላ በወታደሮቼ ብትገደል ልቤ ያዝናልና እባክህ አምባላጌን ለቅቀህ ውጣ።” ብለው መልዕክት ቢልኩበትም፣ ሻለቃ ቶለሲ “ከአለቆቼ ተጨማሪ ትዕዛዝ ካላገኘሁ አምባላጌን መልቀቅ አልችልም” ብሎ የራስ መኮንን ልመና ባለመቀበሉ ራስ መኮንን ሁለተኛ ጊዜ ለሻለቃ ቶለሲ መልዕክት ሲልኩ እንዲህ ብለው ነበር።
“ነገ ማለዳ ጦሬ ይዘምትብሃል።አሁንም ደግሜ ላሳውቅህ። ጦርህን ይዘህ ሂድ። ልቤን አታሳዝነው።” ሻለቃ ቶለሲ በድጋሚ የራስ መኮንንን ደግነት ባለመቀበሉ የራስ መኮንን ጦር የሻለቃ ቶለሲን ጦር ለወሬ ነጋሪ ሳያስቀር አጨደው።
በኋላ ራስ መኮንን የሻለቃ ቶለሲን ሬሳ አስፈልገው ወታደሮቻቸውን ለአንድ ጀግና በሚገባው ክብር እንዲቀበር አዘው ዐይናቸው ያዘለውን እንባ ለመዋጥ ሺጣጣሩ ታይተዋል። እንግዲህ እንዲህ ዓይነት የጦር መሪ ያፈራችውን ሃገር ነበር ጣልያኖች ዛሬም ያልሰለጠነች አረመኔ ሃገር አድርገው በመላው ዓለም ጉራቸውን የሚነፉት።”  ብሏል።
ከመቶ ዓመት በፊት በአድዋው ጦርነት አገርን ለወረረና ለተዋጋ ጠላት አባቶቻችን የሰጡትን ክብር እንኳ ለመሰል ዜጋችን መስጠት ሲሳነን የሚያሳዝን ነው። ለዚህ ፈረንጅ የኢትዮጵያውያንን ጨዋነት ለማወቅና ለመመስከር ኢትዮጵያዊ ሆኖ መወለድ ሆነ ማደግ አላስፈለገውም። ንፁህ ህሊናና ብሩህ አዕምሮ ብቻ ነው የሚጠይቀው። ህሊናችን በአድርባይነት፣ በምቀኝነት፣ በንዋይና በስልጣን ስስት ከጨቀየ የምንናገረውና የምናደርገው ሁሉ አገርና ህዝብን መጉዳቱ አይቀርም። መልካም ዛፍ በፍሬው ይታወቃልና ከምንናገረው የበለጠ የምናደርገው በማንነታችን ላይ ምስክር ሆኖ የኖራል።
አገራችን መስቀለኛ መንገድ ላይ ናት። አደገኛ አጥፊዋም በስልጣን ላይ ያለው ዘረኛ አምባገነን ስርዓት ነው። የትግሉ አቅጣጫ ሁሉ ስርዓቱን ለመቀየር  ተባብሮ በመታገል የሁሉም የሆነች ኢትዮጵያን መገምባት ሊሆን ይገባል። በጎንዮሽ ጦር እየሰበቁ ወገንን ለመውጋት ጊዜና ጉልበት ማባከኑ ቢያበቃ መልካም ነው። ድክመቶችም ካሉ በጨዋነት እየተመካከሩ ማረም ከኪሳራው ትርፉ ያመዝናል። ፕሮፌሰር መስፍንን ጭቃ ላይ ለመጎተት ህሊና ያልዳኛቸውን ዛሬ ስለሚሉትና ነገ ስለሚያደርጉት እንዴት እንመናቸ? በመተሳሰብና በመመካከር ወደጋራ የአገር ጥላት ማተኮር ይሻላል በማለት ቁጭቴን ለመግለጽ በመሆኑ ሃሳቤ የሚያስቀይማችሁ ካላችሁ አስቀድሜ ይቅርታ እጠይቃለሁ። ከተሳሳትሁም ለመታረም ዝግጁ ነኝ።
ቸር እንሰንብት
ኢትዮጵያን ተባብረንና ተከባብረን ካጥፊዎቿ እናድናት
ጸሃፊውን በ amerid2000@gmail.com ማግኘት ይቻላል

Crackdown on dissent intensified as journalists convicted – Joint Statement

31 October 2014. Ethiopia’s already limited space for civil society and human rights defenders is undergoing further contraction, warns CIVICUS, The East and Horn of Africa Human Rights Defenders Project, and the Ethiopia Human Rights Project (EHRP). Throughout 2014, Ethiopian authorities have orchestrated an unprecedented legislative assault on journalists, and independent voices within civil society, undermining fundamental human rights and restricting the operating environment for civil society and human rights defenders.
On 27 October 2014, prominent newspaper editor Temesgen Desalegn was sentenced to three years imprisonment on politically motivated charges of provoking incitement against the state. Temesgen and his now defunct newspaper, Feteh, were targeted under Ethiopian Criminal Code provisions.  The charges, which are widely viewed as an attempt to silence independent reporting on sensitive issues, stem from articles published byFeteh on demonstrations organised by Muslim groups and youth activists in 2012.
Earlier this month, three magazine owners were sentenced to sentences ranging from three years and three months to three years and eleven months in absentia. They are Endalkachew Tesfaye of the Addis Gudaymagazine, Fatuma Nuriya of Fact, and Gizaw Taye of Lomi. The charges levelled against them included “inciting violent revolts, printing and distributing unfounded rumours and conspiring to unlawfully abolish the constitutional system of the country.” In August 2014, the Ministry of Justice accused six weekly papers of committing unsubstantiated crimes against the state. There are concerns that the three other newspapers listed in the communique, including Afro-Times, Enqu and Jano, will also be targeted.
“The recent convictions are indicative of the intolerance of the Ethiopian state towards any kind of dissent. It is a widely held view that the current government is becoming particularly sensitive to public scrutiny as it readies for national elections in May 2015,” said Mandeep Tiwana, Head of Policy and Research at CIVICUS. “With at least 17 journalists and bloggers currently imprisoned in Ethiopia, the country is believed to be the second largest imprisoner of journalists in Sub -Saharan Africa after Eritrea.”
In addition to the wilful misapplication of the Criminal Code, sweeping provisions of Ethiopia’s 2009 Anti-Terrorism Proclamation continue to be invoked to silence journalists and human rights defenders. On 17 July 2014, six members of the blogger’s collective, Zone 9, and three independent journalists, were charged with planning terrorist acts and committing outrages against the Constitution under the Anti-Terrorism proclamation and Ethiopian Criminal Code.
In addition, a seventh member of Zone 9, Soliyana Gebremicheal, who also coordinates the Ethiopian Human Rights Project, was charged in absentia with leading the group. As justification for the charges, the public prosecutor pointed to Soliyana’s recent involvement in a digital security training organised by international human rights groups.
“In the run up to national elections, the increasing trend of arbitrary arrest and detention, politically motivated prosecutions, and intimidation of independent voices within civil society is deeply concerning,” said Soleyana Gebremichael, of the Ethiopia Human Rights Project. “Similar trends were notable in the run-up to the 2010 national election, in which the ruling EPRDF party won 99.6% of parliamentary seats.”
The escalating crackdown in the country comes at a time of growing concern among the international community over Ethiopia’s disregard for its national and international human rights obligations. In September this year, six independent UN experts urged the government to cease misusing the Anti-Terrorism proclamation to curb the rights to freedom of expression and association. In May 2014, the UN High Commissioner for Human Rights alsoraised concern about the climate of intimidation of human rights defenders in Ethiopia.
“In Ethiopia over the last five years, we have seen the wholesale disappearance of the human rights community, with countless human rights defenders forced into exile due to heavy-handed and manifestly unlawful state tactics aimed at undermining their work,” said Hassan Shire, Executive Director of the East and Horn of African Human Rights Defenders Project. “Throughout 2014, the risks facing journalists and independent human rights voices have reached unprecedented new heights.”
The Ethiopian government continues to ignore calls from the international community to institute substantive reforms to rectify the human rights situation in the country. In September 2014, during the adoption of its UN Universal Period Review Report, Ethiopian authorities refused to accept a number of recommendations to release imprisoned journalists and activists in the country or revise the Anti-Terrorism proclamation, despite calls from civil society organisations and a number of governments.
CIVICUS, the East and Horn of Africa Human Rights Defenders Project, and the Ethiopia Human Rights Project urge Ethiopia’s trade and development partners to engage with the Ethiopian government with a view to ending the on-going crackdown on human rights defenders and civil society.
Source: CIVICUS