Sunday 12 October 2014

መኢአድ ታላቅ የተቃዉሞ ሰልፍ በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች ሊያደርግ ነው

ለተቃውሞ ሰልፉ ህዝቡ እንዲዘጋጅ ጥሪውን አቅርቧል።
aeupበነገው ቀን ጋዜጣዊ መግለጫ በመስጠት የተቃውሞ ሰልፉን ቀን ይፋ ያደርጋል ተብሎ የሚጠበቀው መኢአድ በፋሽሽቱ ወያኔ በጋምቤላ በጉራፈርዳ እና በሱማሌ ክልል እየተካሄደ ያለዉን የዘር ማጥፋት ወንጀል በጋራ ለማስቆም መላዉ የኢትዮጵያ ህዝብ የሚሳተፍበት ተከታታይ የተቃዉሞ ሰልፍ በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች ይደረጋል ሲል የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት መኢአድ አስታወቀ።
“በዉጭም በሃገር ዉስጥም የምትገኙ ኢትዮጵያዊያን ከጎናችን በመቆም ይህን ዘረኛ ስርዓት ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ በዲሞክራሳዊ ስርዓት እንቀይረዉ” ያለው መኢአድ አስፈላጊዉን ዝግጅት ሁሉ ማጠናቀቁን ገልጾ ለተቃውሞ ሰልፉ ህዝቡ እንዲዘጋጅ ጥሪውን አቅርቧል።

No comments:

Post a Comment