Friday 21 March 2014

ለነፃነት የምናደርገው ትግል በህገ ወጥ እስርና ማስፈራሪያ አይደናቀፍም! (ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ)

‹ማርች-8›› የሴቶችን ነጻነትና እኩልነት እንዲሁም ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በዓለም አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ የሚከበር የሴቶች ቀን እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ይህን በዓል አስመልክቶ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ባለፈው ዕሁድ የካቲት 30/2006 ዓ.ም ሴቶች ብቻ የሚሳተፉበት የጎዳና ላይ ሩጫ ማዘጋጀቱ ይታወቃል፡፡ በዚህ የሐገራችንም ሆነ የዓለም ሴቶች የነጻነት ቀናቸውን በሚያከብሩበት ዕለት እንደሌሎች ሴቶች ሁሉ የሰማያዊ ፓርቲ አአባላትም አላማውን ደግፈው በዕለቱ ቀኑን አስመልክቶ በተዘጋጀው ሩጫ ላይ ተሳትፈዋል፡፡ በዚህ በሴቶች የነጻነት ቀን በስርዓቱ ላይ የሚነሱ ብሶቶችን ካሰሙት ተሳታፊዎች ውስጥ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት የሚገኙበት ሲሆን፣ በተለየ መልኩ በእነዚህ አባላቶቻችን ላይ ያነጣጠረ የአፈሳ እርምጃ ተወስዶባቸዋል፡፡
Semayawi wetatoch
ሰማያዊ ፓርቲ እንደዚህ አይነት ህዝባዊ መድረኮችን ላይ ብቻ ሳይሆን ሁሌም ህዝብ ላይ የሚደርሰው በደል በማጋለጥ መብት እና ለአገራችን ብሄራዊ ጥቅም በመቆም በገዥው ፓርቲ ተደጋጋሚ ህገ ወጥ እርምጃ ሲወሰድበት ቆይቷል፡፡ የተደረገው ህገ ወጥ ድርጊት ከዚሁ ፓርቲው ለህዝብና ለአገር መቆሙን ተከትሎ እየደረሰበት ያለው የከፋ የጭቆና አካል ነው፡፡
ህገ ወጥ ድርጊቱን የበለጠ አስገራሚ የሚያደርገውም አባላቶቻችን የታሰሩበት ምክንያት ‹‹የጣይቱ ልጅ ነን ፣ ህወሓት /ኢህአዴግን ምን ያህል ከታሪክ ጋር የተጣላ መሆኑን ከማሳየቱም በተጨማሪ አባላቶቻችን ለማስር እንግልት ወቅት በአባላቶቻችን ላይ የደህንነት አካላት ነን በሚሉ ግለሰቦች ማስፈራሪያና ዛቻ ተፈፅሞባቸው፡፡ አንዳንዶቹ አባላቶቻችን በሌሊት ጭምር ከእስር ክፍላቸው ወጥተው ቃል እንዲሰጡ ተከልክለዋል፡፡ ሙከራ ተደርጎባቸዋል፡፡ ከጠያቂ ቤተሰቦቻቸውና የትግል ጓደኞቻቸው ጋር እንዳይገናኙ ተከልክለዋል፡፡ የተጠረጠሩበት ክስ የማያስከስስና በነፃ የሚያስለቅቃቸው መሆኑ በየካ ክፍለ ከተማ ፍትህ ፅ/ቤት አቃቤ ህጎች ከተገለፀላቸው በኋላም በድጋሚ ፍርድ ቤት በማቅረብ እያንዳንዳቸው 1300 ብርና የመታወቂያ ዋስ በዋስትና እንዲቀርቡ ተጠይቀዋል፡፡
ፓርቲያችን ይህ እርምጃ በአባላቱ ላይ የተወሰደው ሰማያዊ ፓርቲ በመላው አገሪቱ መዋቅሩን እያደራጀና ህዝብን ከጎኑ እያሰለፈ ባለበት ወቅት መሆኑ፣ የህዝብ ድጋፍ የሌለው ገዥው ፓርቲ በስበብ አስባቡ ሰማያዊ ፓርቲን ከወዲሁ ለማዳከም የወሰደው ነው ብሎ ያምናል፡፡ በተለይ የምርጫ ወቅት እየቀረበ መሆኑን ተከትሎ ይህን ህገ ወጥ እርምጃ መውሰዱ አሁንም ቢሆን የአገራችን የፖለቲካ ምህዳር ምን ያህል እየጠበበ እንደሄደ ያሳያል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ መቼም ቢሆን ይህንና መሰል የአገዛዙን አፈናዎች አጥብቆ የሚያወግዛቸውና የሚታገላቸው መሆኑን እየገለጸ በሴቶች የነጻነት ቀን ያለአግባቡ ታስረው ህገወጥ እርምጃ በአባላቶቻችን ላይ የወሰዱትን የፖሊስ አካላት በህግ የምንጠይቅ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ በተጨማሪም ይህን መሰሉ የህገ ወጦች እርምጃ ሳይገታን ትግላችንን አጠናክረን የምንቀጥል መሆናችንን እናረጋግጣለን፡፡
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!!!
መጋቢት 12 ቀን 2006 ዓ.ም
አዲስ አበባ

No comments:

Post a Comment