Thursday 18 February 2016

ሰልፈኞች በቡልቡላ ከተማ የአላሙዲ ንብረት የሆነው የነዳጅ ታንከር አቃጠሉ


tankTrank 1
(ዘ-ሐበሻ) ንብረትነቱ የአላሙዲን የሆነው ናሽናል ኦይል ኢትዮጵያ ንብረት የሆነው የነዳጅ ታንከር በኦሮሚያ ክልል በቡልቡላ ከተማ ተቃጠለ::
እንደምንጮች ገለጻ በኦሮሚያ የወርቅ ማዕድኖችን እና የተለያዩ የሕዝብ ንብረቶችን ወደራሱ አስገብቷል ተብሎ ተቃውሞ የቀረበበት የአላሙዲን ንብረት በሆነው ሜድሮክ ኢትዮጱያና በሕወሓት አስተዳደር ሥር ያሉትን ንብረቶች ሁሉ ሕዝቡ እንዳይጠቀምና ከአካባቢውም ጠራርጎ እንዲያስወጣቸው በቀረበው ጥሪ መሠረት በተለያዩ ቦታዎች እርምጃ ሲወሰዱ ቆይተዋል::
በትናንትናው ዕለትም እንዲሁ ንብረትነቱ የትራንስ ኢትዮጵያ የሆነ ቦቴ የተቃጠለ ሲሆን በዚያው ምሽት በቡልቡላ ከተማ ሰልፈኞች የአላሙዲን የነዳጅ ታንከር መቃጠሉን የተሰራጩት ዜናዎች አስታወቀዋል::
በኦሮሚያ የሚገኙ የሕወሓት የንግድ ተቋማትና እንዲሁም የሼህ መሀመድ አላሙዲ ንብረት የሆኑ ድርጅቶች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ከስር ዓቱ የደህንነት ተቋማት ት ዕዛዝ እንደደረሳቸው የሚያስታውቁት የዘ-ሐበሻ ምንጮች በተለይም በአሁኑ ወቅት መንግስት ለአላሙዲ ድርጅቶች በኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ ጥበቃ እየተደረገላቸው እንደሚገኝ አስታውቀዋል::
Share1  1776  3 
 Share1

 English በአማርኛ ይፃፉ

No comments:

Post a Comment