Thursday 26 May 2016

በሐረርጌ የተቀሰቀሰው የተማሪዎች አመጽ ወደ ሌሎች ቦታዎች ተዳረሰ (የፍኖተ ዴሞክራሲ ራድዮ አጫጭር ዜናዎች)

 በተመድ ስር የሚሰሩ ወታደሮች ደሞዛቸው በወያኔ ባለስልጣናት እንደሚበዘበዝ ተጋለጠ
 ስደተኞች ለመቆጣጠር የተቋቋመው የአውሮፓ ህብረት ግብረኃይል የሊቢያን ጠረፍ ጠባቂዎች
እንዲያሰለጥን መመሪያ ተሰጥተው
 በኬኒያ ኩሱሙ በምትባለው ከተማ የተቃውሞ ኃይሎች ያካሄዱትን ሰላማዊ ሰልፍ ለማፈን
ፖሊሶች በወሰዱት እርምጃ ቢያንስ አንድ ሰው ተገደለ
 በዳርፉር መስጊድ ውስጥ የነበሩ ስምንት ሰዎች በአረብ ሚሊሺያዎች ተገደሉ
13254093_10102296231320823_8172214177964234618_n
ዝርዝር ዜናዎች
 ለሳምንታት ጋብ ብሎ የነበረው የተማሪዎች ተቃውሞና የሕዝብ እንድቅስቃሴ እንደገና መቀስቀስ
መጀመሩ ታወቀ። በሐረጌ በዓለማያ ዩኒቨርስቲ ውስጥ ያገረሽው የተማሪዎች ተቃውሞ እንቅስቃሴ
ለማፈን የወያኔ አግአዚ ጦርና የፌዴራል ፖሊስ ወደ ዩነቨርስቲው ግቢ ውስጥ በመግባት
የተማሪዎችን የመኝታ ክፍሎች ከቀላል መፈንከት እስከ አጥንት ስብራት የደረሰ ድብደባ
መፈጸማችው የሚታወቅ ሲሆን በዚህ የጭካኔ ድብደባ ምክንያት ተቃውሞና ሕዝባዊ ንቅናቄው
በሌሎች የኒቨርሲቲዎናች ከተሞች የተዛመተ መሆኑ ይነገራል። በወለጋ በነቅምት ዩኒቨርሲት
ተማሪዎች ተቃውሟቸውን እንደገና ማሰማት የጀመሩ ሲሆን ወያኔም እንደተለመደው ነፍሰ ገዳይ
አግአዚ ወታደሮችን አሰማርቷል። የሆሩ ጉድሩና የከምቦልቻ ከተማ ነዋሪዎችም ዳግም የመብት
ጥያቄን አንግበው አደባባይ መውጣት ጀምረዋል።
 የወያኔ አገዛዝ ዓለም አቀፍ አስዳሪዎቹን ለማስደሰትና እግረ መንገዱንም ጠቀም ያለ ገንዘብ
ለመሰብሰብ በማሰብ በተመድ ስር በሺህ የሚቆጠሩ ወታድሮች ያሰማራ መሆኑ ይታወቃል። ተመድ
ከፍተኛ የሆነ ደምዝ ለወታደሮቹ በየጊዜው ቢከፈልም የወያኔ የጦር አለቆች ገንዘቡን በመረከብ
ወታደሮችን እየበዘበዙ መሆናቸው ታውቋል። ወታደሮቹ የሞት አደጋ ሲደርስባቸው በግልጽና በይፋ
የማይነገር ሲሆን የተመድ የህይወት ካሳ ክፍያንም ባለስልጣኖቹ እንደሚቀራመቱት ይታወቃል።
ተመድ ባለፈው ሳምንት የተመድ የሰላም አስከባሪዎች ቀንን ምክንያት በማድረግ በተመድ ተልእኮ
ስር ሆነ የተገደሉ ስምንት የወያኔ ወታደሮችን የሸለመ ሲሆን የተለያዩ አገሮች ዜጎች የሆነ 128
ወታደሮቹን ተልእኮውን በመፈጸም ህይወታቸው በማለፉ ክብርና ሚዳሊያ ሰጥቷል።
 በኬኒያ ምዕራባዊ ግዛት በምትገኘው ኩሱሙ በምትባለው ከተማ የተቃዋሚ ኃይሎች ደጋፊዎች
ትዕንተ ሕዝብ ያካሄዱ ሲሆን ከፖሊሶች ጋር በተካሄደው ግጭት ቢያንስ አንድ ሰው የሞተ መሆኑን
የዜና ምንጮች ዘግበዋል። ሟቹ የተገደለው ከፖሊሶች በተተኮሰ ጥይት ነው የሚለውን ዜና የፖሊሱ
ክፍል አስተባብሎ ግለሰቡ ወድቆ መሞቱን ገልጿል። ባለፈው ሳምንት በኬኒያ ዋና ከተማ
በተደረገው የተቃውሞ ስልፍ ፖሊሶች ሰልፉን ለመበተን የኃይል እርምጃ መውሰዳቸው ይታወሳል።
በኩሱሙ የተደረገው ስልፍ የተቃዋሚ ፓርቲዎች የምርጫ ኮሚሽኑን የአድልዎና ብልሹ አሰራር
በመቃወም በተከታታይ ካደረጓቸው ስለፎች ውስጥ አራተኛ መሆኑ ነው።
 የአውሮፓው ኅብረት ሰኞ ግንቦት 15 ቀን ባደረገው ስብሰባ ስደተኞች የሚዲትራኒያን ባህር
አቋርጠው ወደ አውሮፓ እንዳይዘለቁ ለመከላከል የተቋቋመው የባህር ኃይል ግብረ ኃይል የሊቢያ
ጠረፍ ጠባቂዎችን በማሰልጠን ተግባር ላይ እንዲሰማራ ተጨማሪ ኃይላፊነት የሰጠው መሆኑ
ተገልጿል። አፕሬሽን ሶፊያ በመባል የሚታወቀው ይኸው ግብረኃይል በሚቀጥለው ሐምሌ ወር
ውስጥ ኃይላፊነቱ የሚያበቃ መሆኑ የታወቀ ሲሆን በብራስል የተሰበቡት 28 የአውሮፓ አገሮች
የግብረኃይሉን እድሜ ለአንድ ዓመት እንዲራዘም አድርገዋል። ግብረኃይሉ ከተቋቋመ ጀምሮ
ያስገኘው ውጤት አነስተኛ ነው በሚል በተደጋጋሚ ወቀሳ የቀረበበት ሲሆን ኃይሉ እንዲጠናከርና
በማሰልጠን ተግባር ላይ እንዲሰማራ የተወሰነው ድክመቱን አርሞ ውጤት እንዲያስገኝ ነው
ተብሏል።
 በዳርፉር የአረብ ሚሊሺያ አባሎች በአንድ መስጊድ ውስጥ በተሰበሰቡ ሰዎች ላይ በወሰዱት ጥቃት
ቢያንስ ስምንት ሰዎች መገደላቸው ታውቋል። ቀደም ብሎ በአንድ የገበያ ቦታ አንድ የአረብ
ብሔረሰብ አባል የሆነና አንድ የመሳሊት ማህብረሰብ አባል የግል አለመግባባት ፈጥረው በተደጋጋሚ
በዱላ የተመታው መሳሊት አረቡን በስለት ገድሎት እንደነበር ከቦታው የተገኘው ዜና ይገልጻል።
የአረቡ ሚሊሺያ አባሎች ለአረቡ መገደል በወሰዱት የበቀል እርምጃና በአካሄዱት የእሩምታ ተኩስ
በመስጊድ ውስጥ የተሰበሰቡ ስምንት ነዋሪዎችን መግደላቸውንና ከእነዚህ ውስጥ ሁለቱ ልጆች
መሆናቸውን የዜና ምንጮች ገልጸዋል።
 በደቡብ አፍሪካ በፕሬቶሪያ ከተማ ሰሜናዊ ክፍል በህገ ወጥ መንገድ የተሰሩ ቤቶችን ለማፍረስ
የጸጥታ ኃይሎች የወሰዱትን እርምጃ በመቃወም ነዋሪዎቹ የተቃውሞ እንቅስቅስቃሴ
ማድረጋቸውን ከስፍራው የተገኘ ዜና ያስረዳል። ሰኞ ግንቦት 15 ቀን በነበረው ግጭት ቤቶች
ለማፍረስ ከተላከው የአፍራሽ ግብረኃይል አባላት ውስጥ ቢያንስ ሁለቱ መገደላችውን የደቡብ
አፍሪካ ባለስልጣኖች ገልጸዋል። ባለስልጣኖቹ ሃማንስክራል በሚባለው የከተማው አካባቢ በሺ
የሚቆጠሩ ሰዎች በህገ ወጥ መንገድ የሚኖሩ መሆናቸውን ጠቁመው ቦታውን ለማጽዳት ከፍርድ
ቤት ፈቃድ የተሰጣቸው መሆኑን ገልጸዋል።

No comments:

Post a Comment