Sunday 29 December 2013

ዛሬ አረና/መድረክ በሽሬ የሚያደርገው ስብሰባ ጉዳይ… (ከትግራይ)

(ኢ.ኤም.ኤፍ) በዛሬው እለት የአረና/መድረክ ፓርቲ በሽሬ እንዳስላሴ ከተማ ስብሰባ ለማድረግ ፈቃድ አግኝቶ፤ ይህንኑ ህዝባዊ ስብሰባ ያደርጋል ተብሎ እየተጠበቀ ነው። ሆኖም በስፍራው የሚገኘው የድርጅቱ ህዝብ ግንኙነት፤ አብርሃ ደስታ እንደዘገበው… ስብሰባው ከመጀመሩ በፊት የህወሃት አባላት መግቢያው በር ላይ ግርግር እየፈጠሩ ናቸው። እንዲህ በማለት ይቀጥላል። “ህዝባዊ ስብሰባውን ለመጀመር አዳራሹ ሲከፈት ህዝብ በስብሰባው ለመሳተፍ መግባት ሲጀምር አስተዳዳሪዎቹ ደንግጠው ‘በስብሰባው መሳተፍ የሚችለው የቀበሌ መታወቅያ ያለው ሰው’ ብቻ መሆን እንዳለበት አወጁ። ይህ ብቻም አይደለም፤ መታወቂያውን እየመዘገቡ ለማስገባት ወሰኑ። ህዝቡ ተቃወመ። የዓረና አመራር አባላትም ድርጊቱ ተቃወሙ። መታወቂያ የሌለው እንዳይገባ ስለተወሰነ ብዙ ሰው ተቃውሞ ስላነሳና መግባት ስለፈለገ የአዳራሹ መግብያ በር ተዘጋ። አሁን የተፈቀደልን አዳራሽ ዝግ ነው። ዓረና ስብሰባው በአዳራሹ በር ባለው ሜዳ ለማካሄድ ወስኗል። ባደራሹ በር አከባቢ ብዙ ህዝብ አለ። ካድሬዎቹ ህዝቡን ለመበተን እየፈተኑ ነው። (ኢ.ኤም.ኤፍ ሁኔታውን እየተከታተለ ማቅረቡን ይቀጥላል)

No comments:

Post a Comment