Tuesday 2 December 2014

በቅርቡ ከተለያዩ የሀገሪቱ አከባቢዎች በፅጥታ ሀይሎች ታፍነው ከተወሰዱት የአንድነት አባላት አራዳ ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ ታወቀ

ዛሬ ህዳር 23 በ8 ሰዓት የአንድነት ታሳሪዎች በአራዳ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ!
ethiopia-trial1-300x235በቅርቡ ከተለያዩ የሀገሪቱ አከባቢዎች በፅጥታ ሀይሎች ታፍነው ከተወሰዱት የአንድነት አባላት ውስጥ አንጋው ተገኝ፣ እንግዳው ዋኘው፣ በላይነህ ሲሳይ፣ አለባቸው ማሞ እና ሺሻይ አዘናው አራዳ በሚገኘው ፍርድ ቤት ይቀርባሉ፤ በቦታው ተገኝተን ያለንን አጋርነት እናሳይ።
በፀጥታ ሀይሎች ታፍነው ከተወሰዱ በኋላ እስካሁን ድረስ የት እንዳሉ ያልታወቁ ሌሎች ታሳሪዎች ደግሞ አባይ ዘውዱ፣ አለበል ዘለቀ፣ ጥላሁን አበበ እና ወጣት አወቀ ብርሃን ናቸው። መንግስት እነዚህን ዜጎች ያሉበትን እንዲያሳውቅና በፍርድ ቤት ቀርበው የዋስትና መብታቸውን እንዲጠበቅላቸው አሁንም ደግመን እንጠይቃለን።
የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ የህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ

No comments:

Post a Comment