Friday 19 December 2014

የባህር ዳር ህዝብ አደባባይ ወጣ፤ የባሕር ዳር ሕዝብም ተቃውሞውን እየተቀላቀለ ነው::

የባህዳር ነዋሪ በነቂስ በመውጣት በክልሉ ም/ቤት ፊት ለፊትና በአዲሱ ም/ቤት(ቀበሌ 10) መስቀል አደባባይ የቤተክርስያን የታቦት ማደሪያ ፣ ንብረትነቱም የቤተ-ክርስቲያን ነው ልትነጠቅ ወይም መንግስት እንደሚለው ለባለሀብት ሊሰጥ አይገባም በማለት ቁጣቸውን በማሰማት ላይ ናቸው፡፡ የባጃጅ ሾፌሮችም በየቦታው ትላክስና ጩኸት እያሰሙ ነው፡፡ የመስቀል አደባባይን መፍረስ በመቃወም በባህርዳር ከተማ የነበረው ሰልፍ ጥያቄውን አሰምቷል::
ነገረ ኢትዮጵያ እንደገለጸው ዘገባ
“• አምስት ሰዎች ሲቆስሉ ሁለት ሞተዋል
ዛሬ ጠዋት ባህርዳር ከተማ ላይ የተነሳውን የህዝብ ተቃውሞ ፖሊስ በኃይል ለመበተን ጥረት እያደረ ቢሆንም ህዝቡ በብዛት ተቃውሞውን እየተቀላቀለ መሆኑን ከቦታው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ ፖሊስ በተኮሰው ጥይት ሁለት ወጣቶች ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን ሌሎች አምስት ያህል ወጣቶች እንደቆሰሉ ተገልጾአል፡፡
በአሁኑ ወቅት ከቀበሌ 10 አባይ ማዶ ያለው መንገድ ተቃውሞውን በተቀላቀለው ህዝብ የተዘጋ ሲሆን ወደ ጎንደር የሚወስደው መንገድም መዘጋቱ ታውቋል፡፡ የቀበሌ 8፣ 10ና 11 ነዋሪዎች እንዲሁም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተቃውሞውን እየተቀላቀሉ ነው ተብሏል፡፡ የአፈ ጉባኤ ጽ/ቤት አካባቢም በርካታ ህዝብ የተገኘ ቢሆንም ርዕሰ መስተዳደሩን ጨምሮ ሌሎች ባለስልጣናት የሉም እንደተባሉ ገልጸውልናል፡፡” ነገረ ኢትዮጵያ
የሰልፉን ፎቶዎች ይመልከቱት:1937456_312016248996709_1054682142798199146_n
9783_596573470488802_1311708396556689267_n

No comments:

Post a Comment