Friday, 25 December 2015

መንግስት ታዋቂ የተቃዋሚ ድርጅት መሪዎችን እየያዘ በማስር ላይ ነው

ታኀሳስ ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ የተነሳውን ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ መንግስት ወጣቶችን በየአካባቢው እያፈሰ ከማሰሩም በላይ የተቃዋሚ መሪዎችን ሲያስፈራራ ከቆየ በሁዋላ መሪዎችን ይዞ ማሰር ጀምሯል።
በቅርቡ ከእስር የተፈቱት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ተቀዳሚ ም/ል ሊ/መንበር አቶ በቀለ ገርባ እንዲሁም የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ምክትል ዋና ጸሃፊ የሆኑት የህግ ባለሙያውና ከ10 አመት በፊት በተደረገው ምርጫ የፓርላማ አባል የነበሩት አቶ ደጀኔ ጣፋ ገለታ በጸጥታ ሃይሎች ተይዘው ታስረዋል።
ግለሰቡ ከዚህ ቀደም በመንግስት ላይ በሚያደርሱት ጠንካራ ትችት ይታወቃሉ። በተመሳሳይ ዜና በጅማ ሂምና ዩኒቨርስቲ የሚማሩ 13 የኦሮሞ ተወላጆች ተማሪዎችን ለተቃውሞ ቀስቅሰዋል በሚል እየተፈለጉ ነው። የዩኒቨርስቲው የጥበቃና ደህንነት የስራ ሂደት ቢሮ ባወጣው ማስታወቂያ ገመችስ ታከለ፣ አሸናፊ ሌንጂሳ፣ አለማየሁ ገመቹ፣ መብራቱ ጅሬኛ፣ መሃመድ ሸምሲዲን፣ አብዲሳ በንቲ፣ ፋጂ ሙላት፣ አብደላ ተስሳ፣ ዘነበች ጌታቸው ፣በሻቱ ቃናአ፣ ቢራ ነጋሽ ደመቀ እንዲሁም አሰፋ ፋና ታህሳስ 14 በዩኒቨርስቲው ተገኝተው የዲሲፒሊን ኮሚቴው የሚሰጠውን ውሳኔ እንደከታተሉ ተጠርተዋል። በኦሮምያ በተካሄደው ህዝባዊ ተቃውሞ 85 ዜጎች በአጋዚ ወታደሮች ሲገደሉ ከ1 ሺ በላይ የሚሆኑ ደግሞ ታስረዋል።

የአንዋር መስጊዱን የቦምብ ጥቃት አስመልክቶ በእስር ቤት ከሚገኙ የኮሚቴው አባላት የተሰጠ መግለጫ

ህዝበ ሙስሊሙ ለተንኮለኞች ሴራ ሳይበገር አንድነቱን አጠንክሮ፣ አመለካከቱን አቻችሎ ሰላማዊ የመብት ትግሉን መቀጠል ይኖርበታል!

በአንዋር መስጊድ ቅጥር ግቢ ታህሳስ 01/2008 የደረሰው የቦንብ ጥቃት የዓለም አቀፉ ሕብረተሰብ ትኩረት እንዲሰጠው፣ ድርጊቱም በገለልተኛ አካላት በአስቸኳይ ተጣርቶ ለህዝብ ይፋ ይደረግ ዘንድ እንጠይቃለን!

አርብ ታህሳስ 15/2008 /አዲስ አበባ/ኢትዮጵያ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ሕገመንግስታዊ የመብት ጥያቄያችንን ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ማቅረባችን ይታወቃል። ለጥያቄዎቻችን ተገቢውን እና ፍትሃዊ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ጥያቄውን በሀሰት በመፈረጅ ሰላማዊ ሂደቱን ለመቀልበስ ተደጋጋሚ ጥረት ተደርጓል። [ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]

Monday, 21 December 2015

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ባቀረቡት ጥሪ ኢትዮጵያውያን ቅድሚያ ሰጥተው ሊተገበራቸው የሚገቡ ስድስት ተግራት

አርበኞች ግንቦት 7 በሚከተሉት ስድስት ነጥቦች ዙርያ የተቀናጀ ትግል እንዲካሄድ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የትግል ጥሪ ያደርጋል።

1. በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች እየተካሄደ ያለው ትግል ከአሁኑ በተሻለ ተጠናክሮ እንዲቀጥል! ለዚህም በነኝህ አካባቢዎች ያለው የነኝህ ማህበረሰብ አባላት ብቻ ሳይሆን ባካባቢዎቹ የሚገኙ ሌሎች ኢትዮጵያውያን ትግሉን በስፋት እንዲቀላቀሉ እንጠይቃለን! በትግሉ ሂደትም በአሮሞና በአማራ ሕዝብ መካከል የትግል አጋርነትና የግብ ተመሳሳይነት መኖሩን ማጉላት ይገባናል። በአሁኑ ሰዓት ግፉና ስቃዩ እጅግ ለበረታበት የኦሮሞ ሕዝብ “አለንልህ፣ ከጎንህ ነን” ማለትና በርግጥም ከጎኑ ተሰልፎ መገኘት ይኖርብናል።
2. በሌሎች ክልሎች ያሉ ኢትዮጵያውያን ትግሉን በያሉበት ባስቸኳይ እንዲቀላቀሉ ጥሪ እናደርጋለን! ሌሎች ክልሎችና አካባቢዎች የሚያቀርቧቸው ጥያቄዎች በየአካባቢያቸው ባሉ የአስተዳደር በደሎችና የነጻነት ፍላጎት ላይ ያተኮሩ እንዲሆን ማድረግ ይገባል፤ ሆኖም ግን ለአካባቢያዊ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ ማግኘት የሚቻለው የአገራችን የፓለቲካ ሥርዓቱ ሲለወጥ ብቻ መሆኑ በትግሉ ሂደት ማሳየት ይጠበቅብናል!
3. የኢትዮጵያ መከላከያና ፖሊስ ሰራዊት እንዲሁም በያካባቢው ስርዓቱን እንዲያገለግሉ የተመለመሉ ሚሊሺያዎች ከኢትዮጵያ ህዝብ አብራክ የወጡ፤ ራሳቸውም የወያኔ አገዛዝ ሰላባ የሆኑ መሆኑን ሁሌም ማስታወስ ይገባል። አርበኞች ግንቦት 7 ይህ የኢትዮጵያ ሰራዊት በወንድሞቹ፣ እህቶቹና ወላጆቹ ላይ እንይተኩስ ይልቁንም አፈሙዙን በዚህ እኩይ ስርዓት ላይ እንዲያዞር በደተደጋጋሚ ጥሪ አድርጓል፤ አሁንም በዚህ ባስራ አንደኛው ሰዓት ይህንን ህዝባዊ ጥሪ በድጋሚ እናደርጋለን! በትግሉ ውስጥ የምትሳተፉ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ይህንን ጥሪ በየትግሉ አደባባይ ማስተጋባት፤ በጎናችን ለምናገኘው ጎረቤታችን፤ ዘመዳችን ወይንም ጓደኛችን ለሆነ የዚህ ያፈና መዋቅር አባል ሁሉ በተደጋጋሚ መንገር አንርሳ!
4. ለኦህዴድ፣ ብአዴን፣ ደህዴድና ህወሓት መካከለኛና አነስተኛ ካድሬዎች እንዲሁም ዝቅተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ለሆናችሁ ሁሉ! እናንተ ዛሬ ከሕዝብ ትግል ጎን ቆማችሁ ራሳቸሁንም ሆነ አገራችሁን መታደግ የምትችሉበት ወቅት መሆኑን እወቁ። ዛሬ የሕዝብን ጥሪ ሳትሰሙ ሥርዓቱን ለመታደግ ግፍ መፈፀማቸሁን ከቀጠላችሁ ነገ ዘራፊ አለቆቻቸሁ የዘረፉትን ለመብላት ሲሮጡ እናንተን የማያስጥሏችሁ መሆኑን መረዳት ለራሳችሁም ሆነ ለቤተሰባችሁ ዘለቄታዊ ጥቅም ይበጃል። አሁኑኑ ሰልፋችሁን አሳምሩ! ነገ አብሮአችሁ ከሚኖረው ህዝብ ጋር አትጣሉ! በትግሉ ውስጥ የምትሳተፉ ኢትዮጵያውያንም ከሕዝብ ትግል ጎን ለመቆም ለሚፈልጉ ለነኝህ ወገኖች መንገዱን አመቻቹላቸው!
5. ደም እየበዛ ሲሄድ ሀሞት እየመረረ እንደሚሄድ የኢህአዴግ ከፍተኛ ባለስልጣኖች ጊዜው ሳይመሽ ቢገነዘቡት ይበጃቸዋል! የኢህአዴግ ባለሥልጣናት አገራችን መመለሻ የሌለው ቀውስ ውስጥ ከመግባቷ በፊት እና የዘረፉትን ንብረት በሰላም ለመብላት በፍጹም የማይችሉበት ሁኔታ ከመፈጠሩ በፊት እየሄዱበት ያለውን የእውር ድንብር መንገዳቸውን ቆም ብለው እንዲያስቡ እንመክራቸዋለን! ለሀገራችን ችግሮች ፖለቲካዊ መፍትሄ ለመስጠት ወደ እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የሚያሻግር ሁሉንም ያሳተፈ ድርድር አሁኑኑ ቢጀምሩ ለራሳቸውም ላገሪቱም እንደሚበጅ ልናሳስባቸው እንወዳለን! ይህን ለማድረግ ደግሞ በቅድሚያ ሰላማዊ ሰዎች መግደልና ማፈንን በአስቸኳይ እንዲያቆሙ፤ የፓለቲካ እስረኞችን በሙሉ ባስቸኳይ እንዲፈቱና አፋኝ ህጎችን በመሰረዝ ለእንዲህ አይነት ሰላማዊ ሽግግር ዝግጁ መሆናቸውን በተግባር እንዲያሳዩ እንጠይቃቸዋለን!
6. በመጨረሻም በመሳሪያም ሆነ በሌላ መንገድ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የሚታገሉ ኃይሎች ሁሉ እንዲሰባሰቡና ይህን ስርዓት ለማንበርከክም ሆነ በይበልጥም ከዚህ ስርዓት ባሻገር የጋራ ቤታችን የሆነችውን ኢትዮጵያ አገራችንን በእውነተኛ እኩልነት፤ በፍትህና በዴሞክራሲያዊ ስርዓት እንደገና የምትታነጽበትን መንገድ በጋራ ለመተለም ባስቸኳይ ውይይት እንዲጀመር ጥሪ እናደርጋለን!

ሰማያዊ ፓርቲ እና መድረክ በጋራ ሰላማዊ ሰልፍ ጠሩ

ሰማያዊ ፓርቲ እና የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) አዲስ አበባ ላይ በጋራ ሰላማዊ ሰልፍ መጥራታቸውን የሰማያዊ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ነገሰ ተፋረደኝ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ እና መድረክ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት መስማማታቸው የሚታወስ ሲሆን እሁድ ታህሳስ 17/2008 ዓ.ም በጋራ ሰልፍ መጥራታቸውን አቶ ነገሰ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡Merera Gudina and Yilkal Getnet
ሰማያዊ ፓርቲና መድረክ የጠሩት ሰልፍ በዋነኛነት ከማስተር ፕላኑ ጋር በተያያዘ መንግስት እየወሰደው ያለውን እርምጃ፤ እንዲሁም መንግስት ለሱዳን አሳልፎ ለመስጠት ያቀደውን መሬቱ እንዳይሰጥ ለመቃወም ያለመ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ሰልፉ ላይ በሰብአዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ላይ መንግስት እየወሰደው ያለውን እፈና እና እርጃዎቸ እንደሚያወግዙ ምክትል ሊቀመንበሩ ተገልፆአል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ እና መድረክ በጋራ የሚያደርጉት ሰልፍ መነሻውን ፒያሳ ራስ መኮንን ድልድይ አድርጎ፣ በቸርቺል አደባባይ የሚያልፍ ሲሆን መዳረሻው ኢትዮ-ኩባ አደባባይ መሆኑን ታውቋል፡፡ መንግስት እየወሰዳቸው ባሉ የተሳሳቱ እርምጃዎች ሀገራችን አጣብቂኝ ውስጥ መሆኗን የገለፁት አቶ ነገሰ ተፋረደኝ ሀገራችን ካለችበት ችግር ለማውጣት ኢትዮጵያውያን በጋራ እንዲቆሙና በሰልፉም እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ሰልፉ እሁድ ታህሳስ 17/2008 ዓ.ም ከጠዋቱ 3 ሰዓት ፒያሳ ራስ መኮንን ድልድይ ላይ እንደሚጀምር ለማወቅ ተችሏል፡፡

At least 75 killed in Ethiopia protests: HRW

Nairobi (AFP) – At least 75 people have been killed during weeks of protests in Ethiopia which have seen soldiers and police firing on demonstrators, Human Rights Watch said on Saturday.
Oromo protesters leave Wolenkomi Photographer: William Davison/Bloomberg
Oromo protesters leave Wolenkomi Photographer: William Davison/Bloomberg
“Police and military forces have fired on demonstrations, killing at least 75 protesters and wounding many others, according to activists,” HRW said in a statement.
Rights groups have repeatedly criticised Ethiopia’s use of anti-terrorism legislation to stifle peaceful dissent, with Washington expressing concern over the crackdown and urging Addis Ababa to employ restraint.
There was no immediate response from Ethiopian government, which has previously put the toll at five dead.
Government spokesman Getachew Reda said the “peaceful demonstrations” that began last month had escalated into violence, accusing protesters of “terrorising the civilians.”
The protests began in November when students opposed government proposals to take over territory in several towns in the Oromia region, sparking fears that Addis Ababa was looking to grab land traditionally occupied by the Oromo people, the country’s largest ethnic group.
Demonstrations have taken place in the towns of Haramaya, Jarso, Walliso and Robe among others.
‘Dozens’ shot
“Human Rights Watch received credible reports that security forces shot dozens of protesters in Shewa and Wollega zones, west of Addis Ababa, in early December,” HRW added.
“Several people described seeing security forces in the town of Walliso, 100 kilometres (60 miles) southwest of Addis Ababa, shoot into crowds of protesters in December, leaving bodies lying in the street.”
HRW also said “numerous witnesses” described how “security forces beat and arrested protesters, often directly from their homes at night.”
Pictures have appeared on social media, apparently showing bloodied protestors and armed police firing tear gas at student demonstrators.
“The Ethiopian government’s response to the Oromia protests has resulted in scores dead and a rapidly rising risk of greater bloodshed,” HRW’s Leslie Lefkow said.
“The government’s labelling of largely peaceful protesters as ‘terrorists’ and deploying military forces is a very dangerous escalation of this volatile situation.”
With at least 27 million people, Oromia is the most populous of the country’s federal states and has its own language, Oromo, distinct from Ethiopia’s official Amharic language.
– US ‘deeply concerned’ –
In a statement issued on Saturday, which did not directly refer to the HRW figures, Washington expressed grave concern over the unrest.
“The United States is deeply concerned by the recent clashes in the Oromia region of Ethiopia that reportedly have resulted in the deaths of numerous protestors,” said the State Department.
“We urge the government of Ethiopia to permit peaceful protest and commit to a constructive dialogue to address legitimate grievances,” it said, also urging protesters “to refrain from violence and to be open to dialogue.”
Writing on Twitter on Friday, Washington’s UN envoy Samantha Power spoke of “concerning rhetoric” from Ethiopia’s prime minister, insisting the government “must use restraint” in its response to the Oromo protests.
Britain’s Foreign Office also expressed concern over the protests in a statement issued on Friday, noting that some had “turned violent, resulting in casualties.”
“There have been heavy clashes including gunfire between protesters and security forces” on December 17, it said, warning Britons against all but essential travel to western and southwestern parts of Oromia.
Some foreign-owned commercial farms have been “looted and destroyed” in the protests near Debre Zeit, some 50 kilometres (30 miles) southeast of Addis Ababa, HRW said.
HRW said the protests — and bloody crackdown — echoed protests in April and May 2014 when police were accused of opening fire and killing “dozens” of protestors. The government said eight people died in the 2014 unrest.

Thursday, 17 December 2015

Petition Letter to UN Secretary General: Ethiopia and Sudan border demarcation

December 14, 2015
H.E. Mr. Ban Ki-Moon
United Nations Secretary General
1st Avenue, 46th Street
New York, NY 10017
Your Excellency:
We the undersigned Ethiopian political parties and civic organizations have the honor to bring to your attention certain developments which do not augur well for the maintenance of peace and security between Ethiopia and the Sudan. Given that sovereignty lies with the Ethiopian people (and state) rather than with a regime, we feel compelled to put all responsible states and international organizations on notice that the long-term interests of the peoples of Ethiopia and the Sudan are being compromised to advance the interests of the elites who have forcibly usurped the power of the state.
Your Excellency will recall that, almost two years ago, several political parties and civic society organizations had the honor to register with your office a strong protest against a secret border deal that the dictatorial governments of both countries had concluded. Although the exact details of the deal are still shrouded in secrecy, the media in both countries have recently reported that the Ethiopian Prime Minister and the Sudanese President have made public their intention to demarcate the common boundary between the two countries on the basis of that deal.
We wish to recall that the respective territorial limits of both countries were defined by treaty at the turn of the 20th century. The 1902 Treaty provided that the line delimited therein must be demarcated by officers of the two governments. If and when the decisions and recommendations of the Joint Commission were accepted by the two governments, each side was then to undertake to explain the boundary line to their respective citizens.
This, however, did not occur. Instead, Major Gwynn alone, representing Great Britain as the colonial power then administering the Sudan, travelled the whole frontier ( about 950 miles) in the space of just a few months in 1903 and purported to demarcate the boundary. In this demarcation, the line Gwynn actually marked out departed from that marked on the map attached to the Treaty in several places for reasons which he alone deemed adequate. In the event, the reasons for the departure were all self-serving and unsurprisingly ended up favoring the Sudan to Ethiopia’s detriment.
It would be carrying coal to Newcastle to point out to Your Excellency that an arbitrary and unilateral demarcation line carried out by a colonial officer a century ago cannot bind the Ethiopian government. It is precisely for this reason that more than four successive Ethiopian governments prior to the current one have rightly and consistently rejected initially British and subsequently Sudanese entreaties to give the boundary line official legitimacy. As early as 1924, Emperor Haile Selassie, when he was still Regent of Ethiopia, declined to accept Gwynn’s unilateral acts, calling on the British government instead to demarcate the frontier by a joint Anglo-Ethiopian commission on the basis of the 1902 Treaty. In calling for such a commission, he minced no words in pointing out to the British Prime Minister of the time, Mr. Ramsey MacDonald, the fact that the frontier had not been demarcated in accordance with the 1902 Treaty. Successive Ethiopian administrations have uniformly maintained this position.
Recently, however, Sudan’s fortunes have improved dramatically with the apparent decision of the quisling government ruling Ethiopia today to accept Gwynn’s line as the basis for a fresh marking of the boundary on the ground. The decision to give legitimacy to the Gwynn line is widely interpreted by the Ethiopian public as a backroom deal intended as a quid pro quo for the Sudan to deny support for the opponents of the current Ethiopian regime. For the Sudan, the Gwynn line offers a vast expanse of territory that historically and under the 1902 Treaty legally belongs to Ethiopia. In return for acquiring Ethiopian territory, the Sudan has pledged that its territory shall not be used by Ethiopian political movements seeking to bring about democratic change in their country.
The rub, however, is that the decision to demarcate the boundary on the basis of a one-sided, outdated, unilateral and illegal arrangement is sure to be a continuing and prolific source of friction and conflict between the sisterly peoples of the two countries and their governments. An arrangement contrived by the extremely narrowly-based, illegitimate, and hated government of Ethiopia and the equally discredited government of the Sudan, led by a war criminal according to the International Criminal Court, will not and cannot stand the test of time.
We have it on good authority that the impending demarcation will deviate from boundary line as defined by the Treaty. Such a boundary will never be accepted by the vast majority of the Ethiopian people. That this is the position of the Ethiopian people has been made manifest by the numerous public demonstrations and press releases, at home and abroad, put out by virtually all political parties, civic organizations, and prominent intellectuals and elders. More importantly, the Ethiopian communities in the border areas who stand to lose their ancestral lands have already put up a stiff resistance in defense of Ethiopian territory and in rightful defiance of the current government’s actions.
As such, it defies common sense to believe that the demarcation line concocted by the two governments will stand the test of time as a final boundary. Quite to the contrary. The effort should be considered as laying a land mine with great potential to destroy relations between the two countries when the shelf life of the current rulers expires. And expire it will, sooner than the leaders are able to realize for they have been blindsided by greed and power.
Your Excellency knows the Horn of Africa is a region already plagued by extreme insecurity and instability, owing among other reasons, to its location astride the Red Sea, its proximity to the conflict- ridden Middle East, and the rivalries of great and aspiring powers alike arising from their desire to control the Nile basin and to exploit the natural resources of the region. Sadly, the Al-Bashir government has become the gateway and proxy for some of these powers and is intent on leveraging its friendly relations with Ethiopia’s historic enemies to obtain undue territorial concessions. The territories it seeks to acquire happen to be extremely fertile and close to Ethiopia’s major river systems, which it will then dole out to rich investors from the Middle East.
Recent developments along the Ethio-Sudanese border are harbingers of what we fear will come to define relations between the peoples of the two countries. Just a few months ago, thirty-three Ethiopians were taken prisoner by the Sudanese forces and a further eight Ethiopians were abducted from the border region by Sudanese militia and cruelly slaughtered like sheep near the Sudanese town of Gallabat. Following this massacre, the border has witnessed a rash of clashes between Ethiopian citizens and Sudanese militia as well as citizens. The Sudanese Ministry of the Interior has claimed that sixteen Sudanese civilian were killed and seven abducted in October by armed Ethiopian groups in reprisal raids. Needless to say, this cycle is likely to escalate with the implementation of the demarcation plan.
The feckless and illegitimate government of Ethiopia has chosen to sweep news of these clashes under the rug. Sudanese media, however, have carried several candid and strident interviews including, for example, with the Sudanese Ambassador to Ethiopia revealing the seriousness of the deteriorating situation on the border. The ambassador’s interview confirms our worst fears. Many innocent citizens of both countries have lost their lives and properties as a result of the rising tension on the border. Incredibly, however, the Ambassador seeks to blame the tension squarely on the shoulders of what he refers to as “the neighboring region’s government” – a thinly- veiled reference to the so-called Amhara Regional State- which he accuses of opposition to the demarcation on the basis of the Gwynn line. Yet, the planned demarcation is not confined to just the territory of the Amhara Regional State but extends to the entire frontier between Ethiopia and the Sudan. Therefore, since the boundary question concerns an issue of Ethiopian- not regional – territorial sovereignty, it is bound to involve the entire nation. Ethiopia’s history is replete with examples of its citizens coming together whenever the country’s territorial sovereignty is threatened.
We recognize that our legal standing to lodge complaints of this nature to Your Excellency is somewhat hampered by current international norms. Yet, in as much as festering border problems so often lead to conflicts between states and/or their citizens and since one of the principal purposes of the United Nations is to maintain international peace and security, we believe that it is entirely appropriate for the Secretariat of the United Nations to apprise itself of the current situation on the Ethio-Sudan border.
The border situation has all the elements and hallmarks of a brewing conflict which calls for Your Excellency’s attention. Some may indulge the hope that as long as the current governments of Ethiopia and Sudan are in agreement as to the basis on which the border is to be demarcated there would be little or no threat to the peace and security of the region. That view is in error. Because the current government is wholly unrepresentative of the views and interests of the Ethiopian people and is bereft of any semblance of legitimacy, its commitments and agreements do not carry weight with the people.
The Ethiopian people view the government’s decision to demarcate the boundary on Sudan’s terms as nothing less than a sellout. If the demarcation goes as planned, thousands of people all along the frontier will be uprooted from their homes, farms and investments, a result they will not take lying down. Ethiopians demand that the proposed demarcation of the boundary line be effectuated in compliance with the provisions of the 1902 Treaty. Anything short of that which is concocted as a political expedient for the ruling clique to prolong its power by ceding Ethiopian territory will never be honored by the Ethiopian people and is bound to provoke serious backlash.
In any case, we wish to go on record to affirm Ethiopia’s right to territorial sovereignty as defined by the 1902 Treaty – and not any other agreement that is reached behind the back of the Ethiopian people. We wish the UN Secretariat to know that the Ethio-Sudan border is pregnant with a situation calling for Your Excellency’s attention. We would appreciate registration of our petition with the UN offices and its circulation among member states.
Please accept the assurances of our highest consideration.
Sincerely,
1. Ethiopian Democratic Hibrehizb Unity Movement
2. Ethiopian Peoples Revolutionary Party
3. Ethiopian Borders Forum
4. Ethiopiawinnet: Council for the Defense of Citizen Rights
5. Gasha LeEthiopia
6. Gonder Hebret
7. International Women’s Organization
cc. Dr Nkosazuma-Dlamini Zuma
Chairperson of the Africa Commission
P.O.Box 3243
Addis Abeba, Ethiopia
The Government of the Republic of Sudan
C/O The Embassy of the Republic of Sudan
2210 Massachussetts Avenue
Washington, DC, 20008
The Federal Democratic Republic of Ethiopia
C/O The Embassy of Ethiopia
3506 International Drive, N.W.
Washington, DC, 20008

ትግላችንን ተጠናክሮ በአንድነት ይቀጥል! (አርበኞች ግንቦት7)

የኢትዮጵያ ህዝብ ለመብቱ በያቅጣጫው መነሳቱ የሚያኮራ ነው። ባለፉት 3 ዓመታት ብቻ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ያደረጉትን የመብት ትግል ጨምሮ በደቡብ፣ አማራ፣ አፋር፣ ጋምቤላና በሌሎችም አካባቢዎች በርካታ የነጻነት ትግሎች ተካሂደዋል። አሁን በኦሮምያ እና በአማራ በተለይም በሰሜን ጎንደር አካባቢዎች እየተካሄዱ ያሉት የነጻነት ትግሎች የአጠቃላዩ የነጻነት ትግል አካሎች ናቸው። በእነዚህ የነጻነት ትግሎች ገዢው ፓርቲ ከህዝብ ጋር ለምንጊዜውም መለያየቱን ለማየት ችለናል። ስልጣኑን ለማስጠበቅ ሲልም፣ አቅሙ ቢፈቅድለትና ማግኘት ቢችል በምድር ላይ ያሉትን ጅምላ ጨራሽ መሳሪያዎችን ሁሉ በገዛ ህዝቡ ላይ ለመጠቀም ወደ ሁዋላ የማይል የአረመኔዎች ስብስብ መሆኑን አረጋግጠናል። በጭካኔውና በፍርሃቱ ብዛት የተነሳ በርካታ ሙስሊሞች፣ ክርስቲያኖች፣ መብታቸውን በሰላም ለመጠየቅ ወደ አደባባይ የወጡ ወጣቶች ተገድለዋል፤ የፖለቲካ ድርጅት መሪዎችና ጋዜጠኞች በእስር ተንገላተዋል፤ በእስር ቤትም ማንነታቸውን ከማዋረድ ጀምሮ የተለያዩ አካላዊ ጥቃቶች ተፈጽሞባቸዋል።
የኦሮሞ ህዝብ መብቴ ይከበርልኝ ብሎ መነሳቱን ተከትሎ ኢትዮጵያውያን ከያቅጣጫው ድጋፋቸውን እየገለጹ ነው። ይህ ለነጻነት ሃይሎች ብስራት ሲሆን ዘርን ከዘር በማጋጨት የስልጣን እድሜውን ለማራዘም ለሚፈልገው የሽፍታ አገዛዝ ደግሞ ትልቅ መርዶ ነው። ባለፉት 25 ዓመታት ወያኔ አንዱን ዘር ከሌላው ዘር እያጋጨ፣ በወንድማማቾችና እህትማማቾች መካከል መተማመን እንዳይፈጥር መርዙን ሲረጭ ቆይቷል፤ ያሰበው አልሰምርለት ሲል ደግሞ በአገሪቱ አንጡራ ሃብት በሸመተው ጠመንጃ ለመብቱ የተነሳውን ህዝብ ደረት ደረቱን እየመታ ፈጅቶታል። በተለይም የአማራው ህዝብ ከሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር በአንድነት ተሰልፎ በህወሃት አገዛዝ ላይ የነጻነት ክንዱን ለማሳረፍ እንዳይችል ሌት ተቀን የጥላቻ መርዙን በመርጨት ከሌላው ህዝብ ጋር እንዲጋጭ ለማድረግ በእጅጉ ደክሟል። ወያኔ የረጨውን የጥላቻ መርዝ የኦሮሞ እና የአማራ ልጆች በጋራ እያረከሱት መገኘታቸው፣ የሌሎች ብሄሮችና ብሄረሰቦች ህዝቦችም እንዲሁ ” አንለያይም” በማለት በጋራ ለመሰለፍና ትግሉን ለማቀጣጠል ዝግጁነታቸውን መግለጻቸውና በተግባር እያሳዩ መምጣታቸው የ25 አመታት የወያኔ የአፈናና የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ እያከተመ መምጣቱን የሚያመላክት ነው። ወያኔ የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲው በመላው ኢትዮጵያውያን ትብብር እንደረከሰበት ሲያውቅ ደግሞ የግድያ አዋጅ አውጥቶ በ-ኢትዮጵያውያኑ ላይ ጥይት አርከፍክፎ ጸጥ ሊያሰኛው መዘጋጀቱን በአዋጅ አስነግሯል። ከታሪክ መማር የማይችለው ጠባቡ ወያኔ፣ ህዝባቸውን አዋጅ አስነግረው የገደሉ ጨቋኝ መንግስታት መጨረሻቸው ምን እንደነበረ እንኳን ቆም ብሎ ማሰብ አልቻለም። ዛሬ የእሳት ላንቃ በሚተፋ ጠመንጃቸው ሊጨፈልቀው የሚያስበው ህዝብ ነገ መልሶ ራሱን እንደሚጨፈልቀው ለአፍታም ቢሆን ለማሰላሰል አልቻለም። የዘረፈው ሃብትና የታጠቀው መሳሪያ አእምሮውን ደፍኖት፣ እየመጣ ያለውን ህዝባዊ ሱናሚ ለማየት ተስኖታል። በጦር መሳሪያ ጋጋታና ድንፋታ ቢሆን ኖሮ ወራሪዋ ጣሊያን እስከዛሬ ድረስ ከአገራችን ለቃ ባልወጣች ነበር፣ በጦር መሳሪያ ጋጋታ ቢሆን ኖሮ እነ ጋዳፊን ዛሬ ቤተመንግስት እንጅ መቃብር ውስጥ አናገኛቸውም ነበር።
የአገራችን ህዝብ ከመቼውም ጊዜ በላይ ለነጻነቱ የሚያደርገውን ትግል በጥንቃቄ የሚመራበት ጊዜ ላይ ነን ። የገጠመን ጠላት በታሪካችን አይተነው የማናውቅ፣ የገዛ ህዝቡን በጠላትነት ፈርጆ ሊያጠፋው የተነሳ በመሆኑ፣ አገዛዙ እስከዛሬ ካደረሰው ጥፋት ሌላ ተጨማሪ ጥፋት ሳያጠፋ፣ ከአገራችን መሬት ለመንቀል እንድንችል እርምጃችን ሁሉ ጥንቃቄ የተሞላበት ሊሆን ይገባል። ጠላታችን ህዝብን ከህዝብ ለማፋጀት ያለ የሌለ ሃይሉን የሚጠቀም መሆኑ ብቻ ሳይሆን፣ አቅሙ በፈቀደለት መጠን ሁሉ ህዝቡን በጅምላ ለመፍጀት ወደ ሁዋላ የማይል ነው። ህዝቡ የጠላቱን አውሬነት ተገንዝቦ እሱ በሚከፍተው ቀዳዳ ዘው ብሎ ላለመግባት መጠንቀቅ አለበት። ሊገድሉን ሲመጡ ዘወር ብሎ በማሳለፍ፣ እንደገና ደግሞ ወደ አደባባይ በመውጣት፣ እንዲሁም የተቃውሞውን አድማስ በማስፋትና የሃይል መከፋፈል እንዲፈጠር በማድረግ ወያኔን አዳክሞና ተስፋ አስቆርጦ ካለሙት ግብ መድረስ ይቻላል። አሁን እየታየ ያለው አንድነት ይበልጥ እየተጠናከረ፣ ከኦሮሞው ጎን አማራው፣ ከአማራው ጎን ጉራጌው፣ ከጉራጌው ጎን ትግሬው፣ ከትግሬው ጎን አፋሩ፣ ከአፋሩ ጎን ጋምቤላው፣ ከጋምቤላው ጎን ሀረሪው፣ ከሃረሪው ጎን ጉሙዙ፣ ከጉሙዙ ጎን አዲስ አበቤው፣ ከአዲስ አበቤው ጎን ጋሞው በአጠቃላይ መላው ህዝብ እጅ ለእጅ እየተያያዘ የነጻነት ባበሩ ወደፊት እንዲሮጥ ማድረግ አለበት። ወጣቱ ራሱን ባለበት ቦታ እያደራጀና አመራር እየሰጠ በያቅጣጫው የጀመረውን የነጻነት ትግል አጠናክሮ ይቀጥል።
አርበኞች ግንቦት7 ትግሉን በተለያዩ አቅጣጫዎች አጠናክሮ ቀጥሎአል፤ የአርበኛው ሰራዊት የወያኔን ጀሌዎች በቀኝና በግራ መውጫና መግቢያ እያሳጣቸው ነው። የንቅናቄው አባላት በዳር አገር በአፈሙዝ፣ በመሃል አገር ደግሞ ወጣቱን እያደራጁ ለትግል እንዲሰልፍ እያደረጉት ነው። የንቅናቄያችን መሪ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ፣ “ከነጻነት ትግሎች ጎን አለን” እንዳሉት የአርበኛው ልጆች ፊት ለፊት ተሰልፈው አመራር በመስጠት የነጻነት ትግሉን ለማቀጣጠል እና መከፈል ያለበትን የህይወት መስዋትነት ለመክፈል ተዘጋጅተው በያቅጣጫው እየተንቀሳቀሱ ነው።
ተደጋግሞ እንደተነገረው የአርበኞች ግንቦት7 አላማ በአገራችን የዲሞክራሲያዊ የሽግግር ስርዓት ማስጀመር ነው። ሁሉም ኢትዮጵያዊ በዚህ አላማ ዙሪያ ተሰልፎ ትግሉን ይቀጥል። ይህን አላማ የሚደግፉ የፖለቲካ ድርጅቶችም ዛሬውኑ ከጎናችን ተሰልፈው ወያኔን ለማስወገድ በሚደረገው የሞት ሽረት ትግል ይሰለፉ!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!
አገራችን በልጆቿ ነጻ ትወጣለች!
አርበኞች ግንቦት7