Tuesday 5 May 2015

ጠ/ሚኒስትር ናታኒያሁ የተቃውሞው መነሻ የሆነውን ወታደር ደማስ ፈቃደማስ ፈቃደን አነጋገሩ





  • 692
     
    Share

natanyahu 2
netanyahu
ኢሳት ዜና :-በሺዎች የሚቆጠሩ ቤተእስራኤላውያን ዘረኝነትን በመቃወም ካለፈው ሃሙስ ጀምሮ የጀመሩት የተቃውሞ ሰልፍ እሁድ ተጠናክሮ ከቀጠለ በሁዋላ፣ የአገሪቱ ጠ/ሚኒስትር ቤንጃሚን ናታኒያሁ ፣ የተቃውሞው መነሻ የሆነውን ወታደር ደማስ ፈቃደን አነጋግረውታል።
ወታደር ደማስ በእስራኤል ፖሊሶች መደብደቡ በአገሪቱ የሚኖሩትን በተእስረኤላውያንን በእጅጉ አበሳጭቶ ለተቃውሞ አደባባይ አስወጥቶአቸዋል። ቤተእስረኤላውያኑ በአገሪቱ ውስጥ ያለውን ዘረኝነት እጥብቀው የተቃወሙ ሲሆን፣ ቁጣቸውንም የተለያዩ ጠርሙሶችና ፕላስቲኮችን በፖሊሶች ላይ በመወርወር ገልጸዋል። በፖሊሶችም በቤተእስረኤላውያን ላይ ጉዳት መደርሱን መገናኛ ብዙሃን ገልጸዋል።
እሁድ የተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ በቅርብ የእስራኤል ታሪክ ያልታየ ነው ተብሎአል። ተቃውሞውን ተከትሎ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ኢትዮጵያውያኑ በአግባቡ አለመያዛቸውን፣ ቁጣውም ለአመታት የተጠራቀመ መሆኑን በመግልጽ ይቀርታ ጠይቀዋል።
ጠ/ሚኒስትሩም ችግሩን እንደሚፈቱ ቃል በመግባት ሁኔታውን ለማረጋጋት እየሞከሩ ነው።
ኢሳት ያነጋገራቸው ቤተእስራኤላውያን እንደሚሉት የአሁኑ ተቃውሞ የ30 አመታት የዘር መድሎ የወለደው ነው። ቤተእስረኤላውያኑ ተቃውሟቸውን የሚቀጥሉ ከሆነ፣ ሁኔታው ሊቀየር እንደሚችል ተስፋቸውን እየገለጹ ነው።
የአለም የመገናኛ ብዙሃን ቤተእስረኤላውያኑ ያደረጉትን ተቃውሞ ሰፊ የዜና ሽፋን ሰጥተውታል።

No comments:

Post a Comment