Thursday 26 May 2016

ግንቦት 20 ለኢትዮጵያ ህዝብ ምኑ ነው?

(በኤልሳቤጥ ግርማ ከኖርዌይ)
በዚህ በያዝነው ወር በየዓመቱ ስለግንቦት 20 በተለያየ መልኩ ይሰበካል፣ ይገለጻል። ለሀገራችን ኢትዮጵያ ታምራዊ ለውጥ እንዳስመሰገበ ሁሉ ወሩን ሙሉ ሲተረክ መስማት እንደ ሀገራዊ መዝሙር የተለመደ ሆኗል:: በተለይ የሥርዓቱ ባለቤቶችና ደጋፊዎች ምስኪኑን ሕብረትሰብ ሳይቀር በማስገደድ ቀኗን “ልዩ ቀን” “የድል ቀን” “የስኬት ቀን” በማለት ሰይመው በአስረሽ ምችው ሲከበር ማየት ድፍን 25 ዓመታትን አስቆጠረ።
eprdf-tplf
ጀግናው የኢህአዲግ ሰራዊት ደርግ ኢሰፓ ሲጠቀምበት የነበረውን የሬዲዮ ጣቢያ ተቆጣጥሮታል ሺ ዘጠኝ መቶ ሰማኒያ ሦስት ብለው እንዳበሰሩን በእርግጥ ለጥቂቶች ግንቦት 20 የድል ቀን ነው:: ምክንያቱም ሀገሪቱን በአንባገነናዊ አገዛዝ ለማስተዳደርና የስልጣን ጥማታቸውን ለማርካት መሰረት የጣሉባት እና የአስራ ሰባት ዓመት የልፋት ዋጋቸውን ያገኙባት ልዩ ቀን ናትና:: በዚች ቀን ህብረተሰቡን በምስጢራዊ የአገዛዝ ስልት ለማስተዳደርና ስልጣናቸውን ዘላለማዊ ለማድረግ የነበራቸው ሕልም እውን የሆነባት ቀን ናትና በልዩ አከባበር ቢያከብሯት ሲያንሳት እንጂ አይበዛባትም::
የተወሰኑ የስራዓቱ አቀንቃኞችም ስለቀኗ መልካምነትና ከዚያች ቀን በኃላ አገራችን ኢትዮጵያ በልማት ጎዳና የገስገሰች፣ የዜጎች አኩልነት የተረጋገጠባት፣ ፍትህና ዲሞክራሲ የሰፈነባት፣ ሰባዊ መብቶች የተከበሩባት፣ ፍትሃዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ የታየባት፣ ህብረተሰቡን በእኩል የሚያስተዳድር መንግስትና ሕግ መንግስት የተመሰረተባት አገር እንድትሆን ግንቦት 20 ታሪካዊ የድል አሻራ እንደጣለች በኩራት አፋቸውን መልተው ይናገራሉ:: ይባስ ብለው ከውጭ ወራሪ ወይም ቅኝ ግዛት ኢትዮጵያን ነፃ ያወጧት ይመስል ግንቦት 20ን የነፃነት/ሀገራዊ ቀን ለማድርግ የሚሞክሩ ብልጣብልጥ የስራዓቱ ደንገጡሮችም አሉ::
በእርግጥ የደርግ አንባገነን መንግስት የአጼ ኃይለ ስላሴ መንግስትን ገርስሦ በምትኩ ወታደራዊ ጁንታ በመመስረት ስሙን በመቀያየር አገዛዙ ለ17 ዓመታት ኢትዮጵያን በብዙ ዘርፈ ብዙ ችግሮች በተለይ ሀገሪቱን መለወጥ ይችላሉ ተብለው የሚታሰቡትን 60 ሚኒስተሮች በመረሸን፣ ነጭና ቀይ ሽብር በማለት ሀገር ተረካቢ ትውልድን በማስጨፍጨፉ የኢትዮጵያ ህዝብ የደርግን ስርዓት አንቅሮ ተፍቶት ነበር። የለውጥ ያለሽ ብሎ በመጮህ ከደርግ አረመኔያዊ የጭካኔ አገዛዝ ነጻ ሊያወጣው የሚችል መለኮታዊ ኃይል እስኪፈልግ ድረስ የኢትዮጵያ ህዝብ በሙሉ ለውጥ ፈላጊ ሆነ።
ህወሓት የህዝቡን ብሶትና እሮሮ ተጠቅሞ 17 ዓመት ጫካ ውስጥ ያረገዘውን መርዝ ለመርጨት ግንቦት 20 ደርግን ገርስሦ በትረ ስልጣኑን ጨበጠ። እዚህ ላይ ወያኔ የደርግን ስርዓት ሳያይና በትንሹም ቢሆን ለውጥ እንዲመጣ ጥረት ሳያደርግ ለትግል ወደ ጫካ መግባቱ ሀገራዊ ለውጥ አሳስቦት ሳይሆን የብሄር ፖለቲካ ጥማት እንደሆነ በትክክል መገንዘብ ይቻላል፤እያየነውም ነው። የብሄር ፖለቲካ ደግሞ እንደ ኢትዮጵያ በርካታ ብሄር ብሄረሰቦችን ለምታስተናግድ ሀገር ቀርቶ ለየትኛውም የአለም ሀገራት የማይበጅ መሆኑ የታወቀ ነው። ኢትዮጵያም የከፋፍለህ ግዛውና የጎሳ ፖለቲካ እንደማይጠቅማት ከዘመነ መሣፍንት ትምህርት ቀስማ ነበር። ዳሩ ግን የኢትዮጵያ ህዝብ የደርግን ሥርዓት ጥላቻና ሽሽት ዘረኛው ወያኔን ግንቦት 20 በሩን ከፍቶ እጁን ዘርግቶ ተቀበለ።
ወያኔዎች የደርግን ሥርዓት ገርስሰው መንግስቱ ኃይለ ማርያምን ወደ ዝምባብዌ ካስኮበለሉ በኋላ ሥልጣናቸውን ለማጽናት የይስሙላ ህገ መንግሥት አርቅቀው አጸደቁ። ለተወሰኑ ዓመታትም የነጻነት በርን ለመከፈትና ስላምና መረጋጋትን ለማስፈን የመጡ እስኪመስል ድረስ ሰላምን ሰበኩ። ከደርግ ጋር ንክኪ አላቸው ተብሎ የሚጠረጠሩ ግለሰቦችን በሙሉ እስር ቤት ወረወሯቸው። ከገጠር እስከ ከተማ ህብረተሰቡ ለራሱ መጠበቂያ ብሎ የገዛዉን ትጥቅ ሳይቀር በሙሉ አስፈቱ። የኢትዮጵያ ህዝብ ግንቦት 20 በየዓመቱ “የድል ቀን” እያለ እንዲዘምር ተደረገ።
በእውኑ ግንቦት 20 ለኢትዮጵያ ህዝብ ምኑ ነው? ይህ ጥያቄ በተለያየ መልኩ በሁላችንም አይዕምሮ ውስጥ እንደሚመላለስ እርግጠኛ ነኝ። መልሳችን ግን በራሳችን ምዕናባዊ እይታ ስለምንመለከተው የተለያየ ሊሆን ይችላል፤ ሆኖም ግን ከሁለት አማራጮች ሊዘል አይችልም። ግንቦት 20 ለኢትዮጵያ ህዝብ ወያኔዎች እንደሚሉት “የድል ቀን” ወይም ብዙዎች እንደሚስማሙበት “የውድቀት ቀን” መሆን አለበት። ወያኔዎችና ደጋፊዎቻቸው ግንቦት 20ን “የድል ቀን” ማለታቸው በእርግጥም ትክክል ናቸው። ምክንያቱም በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የአንባገነን ስልጣናቸውን ያፀኑበት እና በሦስቱም ዘርፍ ማለትም ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮችን ሙሉ በሙሉ የተቆጣጠሩበት ቀን ነውና።
እውነታው ሲገለጥ ግን ግንቦት 20 ለኢትዮጵያ ህዝብ የውድቀት እና የውርደት ቀን እንጂ በምንም መመዘኛ የድል ቀን ሊሆን አይችልም። ምክንያቱም ለአንድ ሀገር የድል ቀን ሲባል ዜጎቿ እኩል ተጠቃሚ ሊያደርግ የሚችል በጎ አጋጣሚ ወይም የኩራት ምንጪ ሲፈጠር ብቻ ነው። ግንቦት 20 ግን ከዚህ በተቃራኒው መሆኑን ግልጽ ሊያደርግ የሚችል ብዙ ማሳያዎች ከመኖሩም ባሻገር በኢትዮጵያና በህዝቦቿ ላይ የደረሰውንና እየደረሰ ያለውን ችግር ዘርዝሮ መናገር ይቻላል።
“የድል ቀን ሆይ የት ነሽ?ምንጭሽስ ከቶ ከወደየት ይገኛል?”
የኢትዮጵያ ህዝብ ከግንቦት 20 የተቀበላቸውን ገጸ እርግማኖች ለማሳያ ያክል እንደሚከተለው እናያለን፤
የብሄር ፖለቲካ የተፀነሰበት
የህወሓት ማፍያ ቡድን ገና ከጅምሩ ሃገራዊ ፍቅር ሰንቆ እንዳልመጣ ከስሙ መረዳት ይቻላል። የትግራይ ነጻ አውጪ ቡድን ብሎ መሰየሙ ለኢትዮጵያና ለህዝቧ እንዳልቆመ ለመረዳት ነብይነት አያሻውም ነበር። የከፋፍለህ ግዛው መርህን በማንፌስቶው ይፋ አድርጎ ይንቀሳቀስ እንደነበር ሰነዶች ህያው ማስረጃ ናቸው። ለስልጣን ማራዘሚያ በዋናነት የተጠቀመበት ዋናና ትልቁ አጀንዳ የብሄር ፖለቲካን ነው። ምክንያቱም የኢትዮጵያ ህዝብ አንድ ካልሆነ በስተቀር ከስልጣን ሊወርድ የሚችልበት ምንም አይነት አጋጣሚ እንደሌለ በሚገባ ያውቃልና። የብሄር ፖለቲካ እያራመደ እርስበርሳችን እንዳንተማመን በብሄር ለያይቶናል። ይሄ የናንተ መሬት ነው፣ ይህ ደግሞ የነሱ ነው ወዘተ እያለ በቡድን ከፋፍሎናል። በብሄሮች መካከል መግባባት እንዳይኖር እነእገሌ እንዲህ አደረጓቹህ፣ ታሪካችሁ እንዲህ ነው በማለት መጀመርያ መምጣት ያለበት ብሄር ነው ወዘተ እያለ የብሄር ጥላቻ እንዲሰፍን ሀውልት ሰርቶልናል። አንድ ዜጋ ኢትዮጵያዊ ነኝ ከማለት ይልቅ በውሸት የብሄር እኩልነት ስም ኦሮሞ፣አማራ፣ ጉራጌ፣ አፋር፣ ሶማሌ፣ ጋምቤላ እያለ በየቦታው እራሱን እያዋረደ እርስ በእርሳችን በጥላቻ እንድንናቆር ማድረጉ የወያኔ የብሄር ፖለቲካ ውጤት ነው። ስለዚህም ግንቦት 20 ለኢትዮጵያ ህዝብ የድል ቀን ሳይሆን የብሄር ፖለቲካ የተፀነሰበት የውርደት ቀን ነው። “የድል ቀን ሆይ የት ነሽ?ምንጭሽስ ከቶ ከወደየት ይገኛል?”
ትውልድ ገዳይ ሥርዓተ ትምህርት የተቀረጸበት
ትምህርት ቤቶች ለአንድ ሀገር ተተኪ ዜጋ ፈጣሪ ተቋም እንደመሆናቸው መጠን የሃገሪቱን ነባራዊ ሁኔታ ያገናዘበ፣ ታሪክንና ባህልን ከማሳወቅ ባለፈም በማንነት ላይ የተመሰረተ ጥራት ያለው ዜጋ ለማፍራት የሚቀረጸው ሥራተ ትምህርት ትልቁን ድርሻ ይወስዳል። ነገር ግን ወያኔ የቀረጸው ሥርዓተ ትምህርት ግን ትውልድን ገዳይና የተማሪዎችን አይዕምሮ ለምርምርና ጥናት የማይጋብዝ ዘላቂና አስተማማኝ ያልሆነ ጥራት የጎደለው ሥርዓተ ትምህርት ነው። ትምህርት ቤቶችም ተማሪዎችን በጥሩ ሥነ ምግባርና ባህልን ከማሳዎቅ አንጻር አስተምሯቸው ዝቅተኛና ከዚህ ግባ የማይባል መሆኑ ለትውልዱ መጥፋት ሌላው የወያኔ የስርዓቱ ውጤት ነው። ትምህርት ቤቶችን ስንመለከት ከተቀረጸላቸው ሥርዓተ ት/ት ጀምሮ ትውልድን ለመቅረጽ ቀርቶ በዜግነት ደረጃም እኔ ኢትዮጵያዊ ነኝ ብሎ የሚናገር ትውልድ እንዲጠፋ በማድረግ ረገድ ግንቦት 20 የራሷን ጥቁር ጠባሳ ጥላለች። አንዳንድ የዘመነ ወያኔ ተማሪዎች የሀገረን ታሪክ በሚገባ ካለማዎቅ የተነሳ ቅኝ ግዛት በተገዛን ኑሮ ሲሉ መስማት የሥርዓተ ትምህርት ውድቀቱን ማሳያ አንዱ መንገድ ነው።
የሃገር ዳር ድንበር የተደፈረበት
አንድ ሀገር የድል ቀን የምታከብር ከሆነ ለሀገርና ለህዝብ የሚቆረቆር መንግሥት አላት ማለት ነው። መንግሥት ካለ ደግሞ የሃገር ሉዓላዊነት ተጠብቆ፣ ታሪኳ ሳይበረዝና ሳይፋለስ ለትውልድ መተላለፍ ይችላል ማለት ነው። ወያኔ ስልጣን ከያዘ ጀምሮ ግን የኢትዮጵያ እጣ ፈንታ ዳር ድንበሯ የተደፈረባት፣ ወደቧን ያጣችበትና ታሪኳ የተበረዘበት ዘመን ነው። ድሮ አባቶቻችን ቅኝ አንገዛም በማለት ታሪካችንና ባህላችን ሊበረዝ ከቶ አይችልም ብለው አጥንታቸውን ከስክሰው፣ ደማቸውን አፍስሰው፣ ውድ ህይወታቸውን ሰውተው ዳር ድንበሯን ከነሙሉ ክብሯ ያቆዩልንን ሀገር ወያኔ ለአረብና ህንድ ባለሃብቶች ማቀራመቱ ሳያንሰው ሱዳን የድርሻሽን ውሰጅ ብለው በመማጸን ላይ እንደሆኑ ስንሰማ በእውነትም ግንቦት 20 ለኢትዮጵያ ህዝብ የውርደትና የውድቀት ቀን ነው። ዜጎቿ በሄዱበት ሞትና እንግልቱ ሳያንሳቸው በእራሳቸው ሀገር በሌላ ዜጋ እንደ እንስሳ ደማቸው ሲፈስና ህጻናት በገፍ ተግዘው ሲሄዱ ከማየት በላይ ምን የተለየ ውርደትና ውድቀት ይኖራል። “የድል ቀን ሆይ የት ነሽ?ምንጭሽስ ከቶ ከወደየት ይገኛል?”
ህዝቦቿ ለሞት፣ለስርና በስደት ለውርደት የተዳረጉበት
በወያኔ አገዛዝ ከ1983 እንደ ኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ከግንቦት ወር ጀምረን በግፍ ውድ ህይወታቸውን በስውርና በአደባባይ የተቀሰፉ፣ ለስር፣ ለእንግልትና ለስደት የተዳረጉ ዜጎችን የሰማይ አምላክ ይቁጠራቸው እንጂ በአኃዝ ማስቀመጥ እጅጉን ይዘገንናል። ተፈጥሯዊና ሰባዊ መብቶች በይፋ ተገርስሰዋል። የስርዓቱ አባል፣ ደጋፊና አገልጋይ ካልሆነ በስተቀር በሀገሩ ምድር ቀና ብሎ የመናገር፣ የመጻፍ፣ የመደራጀት እና የመስራት መብቶች ፈጽመው መገደባቸው የአደባባይ ምስጢር ነው። ወያኔዎች ግንቦት 20ን የድል ቀን ብለው ማክበር ከጀመሩ ጀምሮ በሀገሪቱ ከጽንፍ እስከ ጽንፍ የግፍ ጽዋ ሞልቶ ፈሷል። ህዝቦቿ በሄዱበት ሁሉ የውርደት ካባ እየተከናነቡ ተቆርቋሪ ያጣ ዜጋ በመሆኑ ዋይታና ልቅሶው ከመቸውም በላይ ጨምሯል። “የድል ቀን ሆይ የት ነሽ?ምንጭሽስ ከቶ ከወደየት ይገኛል?”
በአጠቃላይ ኢትዮጵያ አገራችን የተለያየ መልክና መገለጫ ያላቸው በርካታ መንግሥታትን ያስተናገደች አገር ብትሆንም ለዘመናት ታሪኳን፣ ባህሏን፣ እምነቷን፣ አንድነቷን፣ ድል አድራጊነትን እና ዳር ድንበሯን ጠብቃ አስጠብቃ የኖረች እና መተሳሰብን፣ መከባበርን፣ እንግዳ ተቀባይነትን፣ ዘርንና ጎሳን መሰረት ሳታደርግ ለዘመናት የቆየች የጀግኖች አገር ነበረች። ነገር ግን ግንቦት 20 የለገሰን የአሳርና የግፍ ፍሬዎች በቀላሉ የማይሽሩ እኩይ ተግባር ናቸውና ታሪካዊ አገራችንን አደጋ ላይ ጥሏታል። ስለሆም ጊዜ ሳንሰጥ “የድል ቀን” የሚለውን ተረት ተረት ወደ ጎን በመተው በአንድነትና በህብረት ዛሬውኑ የውርደትን ቀን ወደ የድልና የክብር ቀን ሊቀየር ይገባል። ግንቦት 20 ለኢትዮጵያ ህዝብ የድል ቀን ሳይሆን የሞት፣የውድቀትና የውርደት ቀን ተብሎ ይስተካከል!ምነው ሽዋ! ድንቄም የድል ቀን…………

16 የግንቦት 20 ፍሬዎች!

  • 350
     
    Share
TTPLF
  1. በዐፄ ሠርፀ ድንግል ዘመን ቱርኮች ሀገራችንን ቅኝ ለማድረግ በማሰብ ባሕረ ነጋሽ ይስሐቅን (አሁን ላይ ጥሊያኖች ኤርትራ ያሏት የባሕረ ምድርን ገዥ) በመደለል በገዛ ሀገሩና ሕዝቡ ላይ ክህደት በመፈጸም የሚገዛውን የሀገራችንን ክፍል ይዞ እንዲከዳ በማድረግ ተጀምሮ የነበረው ነገር ግን ወዲያውኑ 1571ዓ.ም. ዐፄ ሠርፀ ድንግል ወደቦታው ዘምተው የከሐዲውን የባሕረ ነጋሽ የይስሐቅንና የወራሪውን የቱርክን ጦር በመደምሰስ ከሽፎ የነበረው፤ በኋላ እንደገና ከአራት ምዕት ዓመታት በኋላ በፋሺስት ጣሊያን ወረራ ለ50 ዓመታት ተነጥሎ የነበረውና ፋሽስት ለቆ መውጣቱን ተከትሎ በተደረገው ዲፕሎማሲያዊ (የአቅንኦተ ግንኙነት) ጥረት እንደገና ወደ እናት ሀገሯ እንድትቀላቀል በማድረግ እንደገና ከሽፎ የነበረው ለበርካታ ምዕት ዓመታት የተደረገው ሀገራችንን ገንጥሎ የመውሰድ የጠላት ሀገራት ጥረትና እንቅስቃሴ በዚያ ምድር ላይ የእነኝህን ጠላት ሀገራት ዓላማ ግብና አቅድ የሚደግፉ የሚያስፈጽሙ የባሪያ ሥነልቡናና ሰብእና ያላቸው የእፉኝት ልጆችን በማፍራቱ እነኝሁ ዜጎች የሚባሉት የገዛ ሀገራቸውን የማፈራረስ ዓላማ አንግበው በመነሣት አሁን ለጊዜው ተደጋጋሚ ሙከራ ሲደረግባት የነበረችውን ባሕረምድር (በባርነት ስሟ ኤርትራን) የገነጠሉና ያስገነጠሉ ገንጣይና አስገንጣይ የጥፋት ኃይሎችን ያገኘንበት፡፡
  2. ዜጎች በዘር በሃይማኖት እንዲከፋፈሉ በመደረጉ የነበረ ፍቅራቸው፣ ትስስራቸው፣ መተማመናቸው፣ ሰላማቸው፣ አንድነታቸው እንዲጠፋ ተደርጎ በጠላትነት እንዲፈላለጉ በጥርጣሬ እንዲተያዩ ሲደረግ ያየንበት፡፡
  3. ግንቦት 20 ያነገሣቸው የጥፋት ኃይሎች መጥተው ከማየታችን በፊት ሊኖሩ ይችላሉ ተብሎ በፍጹም በማይገመት መልኩ “ሰው እንዲህ ሆኖ ይፈጠራል?” በሚያስብል ደረጃ ጠባብ፣ ግፈኛ፣ አርቆና አስፍቶ ማየት ማሰብ የተሳናቸው፣ የማሳስተውሉ፣ “እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል” ባይ፣ ፈጽሞ ኃላፊነት የማይሰማቸውን የነውረኛ የጉድ ፍጥረቶች መንጋ ሀገረ እግዚአብሔር በምትባል ኢትዮጵያ መኖራቸውን ዓይተን ያረጋገጥንበት፡፡
  4. በ20/21ኛው መ/ክ/ዘ በሀገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ ዜጎች የአንድ ብሔር ተወላጆች በመሆናቸው ብቻ ለተለያየ ዓይነት ዘግናኝ የዘር ማጥፋት ወንጀሎች ሲዳረጉ ያየንበት፡፡
  5. ለሽዎች ዓመታት የኖረች ሀገር ያካበተችው ያቆየችው የኖረችው ያለፈችበት ታሪክ፣ ቅርስ፣ እሴት፣ ማንነት ተቀብሮና እንዲጠፋ ተደርጎ በቦታው ለጥፋት ኃይሎቹ የጥፋት ሥራዎች የሚረዱ ሐሰተኛና የፈጠራ የጥፋት ታሪኮች ሀገር ስትሞላ ያየንበት፡፡
  6. “ከምን ጋር የዋለች ጊደር ምን ተምራ ትመጣለች” እንደተባለው በአብዛኛው ቅን፣ ቅዱስ፣ ጨዋ፣ ታማኝ፣ ደግ፣ አዛኝ፣ ተሳሳቢ ከነበረው ሕዝባችን ቀላል የማይባለው ቁጥር ሳይወድ በግዱ ከእነኝህ ጉዶች ክህደትን፣ እብለትን፣ ሐሰትን፣ ሆድ አምላኪነትን፣ ሸፍጥን፣ ማስመሰልን፣ ቀማኛነትን፣ ስግብግብነትን፣ ኅሊናቢስነትን፣ ነውረኛነትን ወዘተረፈ. ተምሮ ሲረክስ ሲባልግ ያየንበት፡፡
  7. ቀደም ሲል ከነበረው በተናጠል ይፈጸም የነበረው ከዝምድናና ከትውውቅ የሥራ ቅጥር፣ ከሙክትና በእጅ የመጨባበጥ ሰላምታ ከምትሰጥ ጥቂት ብር ጉቦና የሙስና አሠራር ወደ መቶ ሚሊዮኖችና ቢሊዮኖች (አእላፋትና ብልፎች) በግልና በቡድን ከሚዘረፍ የሀገር ገንዘብ ዘርን መሠረት ያደረገ የሥራ ቅጥርና የሙስና አሠራ ከመንኮራኩር በፈጠነ ፍጥነት ተወንጭፎ ሲያድግ ያየንበት፡፡
  8. ለመሠረተ ልማት ግንባታ ስም የሚመጣው ብድርና እርዳታ በጥቂቱ እጅ የወረደ የጥራት ደረጃ ያለው ብላሽ ሥራ ተሠርቶ አብዛኛው በብድርና እርዳታ የመጣ የሕዝብ ገንዘብ እየተዘረፈ እየተበላ ግለሰቦችና ቡድን ሲበለጽጉበት ሰማይ ሲተኮሱበት ሀገርና ሕዝብ ለድርብርብ ጉዳትና ኪሳራ ተዳርገው በትውልደ ትውልድ ተከፍሎ ከማያልቅ የዕዳ ማጥ ውስጥ ሲጠልቁ ሲሰምጡ ያየንበት፡፡
  9. የኢትዮጵያ ሕዝብ ሀገሪቱ የጥቂቶች በመደረጓና እሱ መተፋቱን ዓይቶ በሀገሩ ተስፋ ከማጣቱና ከመቁረጡ የተነሣ ሀገሪቱን ጥሎ የትም ቢሆን ለመሰደድ የሌት ከቀን ሕልሙ የሆነበትና እየተሰደደም ለበረሀ አውሬ፣ ለባሕር ዓሣና ለአሕዛብ ካራ እንደተዳረገ ዕያየ ያላንዳች መደናገጥና ማቅማማት አሁንም ለመሰደድ ሲገደድ ያየንበት፡፡
  10. ዜጎች ኢትዮጵያዊያን በመሆናቸው ብቻ ስደት በየሔዱበት ሀገራት የሚዋረዱበት፣ የሚታሰሩበት፣ የሚገደሉበት፣ ኩራትና ክብር የነበረው ኢትዮጵያዊነት እርግማን ሆኖ በዓለምአቀፉ ማኅበረሰብ ፊት ብሔራዊ ውርደት ተከናንበን ተሸክመን ስንቀመጥ ያየንበት፡፡
  11. እንደ ሰባዎቹ (1961-1970ዓ.ም.) ዘመናት ወጣቶች ትውልዱ ጠያቂ ሞጋች ተቆርቋሪ አፋጣጭ፣ ሞትንም እንኳ ሳይፈራ የዜግነት ኃላፊነቱንና ግዴታውን ለመወጣት የሚተጋ ሆኖ ሥልጣናቸውና ደኅንነታቸው ችግር ላይ እንዳይወድቅ በማሰብ ትውልዱን ለማፍዘዝ ለማደነዝ በተሠራው ሥራ ትውልዱ በደረሰበት የቅስም (የሞራል) ልሽቀት ስብራት ድቀት ውድቀት የተነሣ ነፍዞና ደንዝዞ ድሮ ድሮ የድሩየነት የወሮበላነት የከንቱነት መለያ የነበረው ጫት ቃሚነትና ሱሰኝነት የዱርየነት መለያ ከመሆን ወጥቶ የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎችና መምህራን መለያ ሲሆን ያየንበት፤ አሁን አሁን ደግሞ በየቢሮው (በየመሥሪያ ቤቱ) በግላጭ ሲያመነዥኩትና ሲጠቀሙት ያየንበት፡፡
  12. የትምህርት ጥራት ድራሹ ጠፍቶ እንኳን ሌላ ስማቸውን እንኳ አስተካክለው የማይጽፉ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራቂዎችን ያየንበት፡፡
  13. በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ኃላፊነቱንና ግዴታውን የማያውቅ፣ የሀገር ፍቅር ስሜቱ የሞተ፣ ለማንነቱ ለክብሩ ለኩራቱ ክብርና ዋጋ የማይሰጥ፣ ከሆዱ በቀር ምንም የሚያሳስበው የሌለው፣ ለሆዱ ሲል ሀገሩን እናቱን ሌላው ቀርቶ “እኔ ከሌለሁ መቸ ልበላው ነው?” ብሎ እንኳ ሳያስብ ራሱንም የሚሸት ትውልድ ፈርቶ ያያንበት፡፡
  14. የኑሮ ውድነት ጣራ ነክቶ ሀብታም፣ መሀከለኛ፣ ድሀ የሚባል የነበረው የዜጎች የኑሮ ደረጃ ፈርሶ ማዕከላዊውን አጥፍቶ በጣም ጥቂት የናጠጡ ሀብታሞችን ጥቂት ድሆችንና እጅግ በጣም ብዙ የድሀ ድሀዎችን በመፍጠር የኑሮ ደረጃዎች ሲዛቡ ያየንበት፡፡
  15. የሀገሪቱ ቅርስና ባለውለታ የሆነችው የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን አስተምህሮዋ፣ ዶግማዋ፣ ቀኖናዋ፣ ክብሯ፣ መታፈሯ፣ መፈራቷ ተጥሶ ተድሶና ተገርስሶ የምናምንቴዎች መጫወቻና መቀለጃ ስትሆን ያየንበት፣ ምናምንቴዎቹም “እንዳታንሰራራ አድርገን አከርካሪዋን ሰብረናል!” ብለው ሲፎክሩ የሰማንበት፡፡
  16. ኧረ የግንቦት 20 ፍሬ ስንቱ ተወርቶ ይዘለቃል? እናንተን ሥራ ማስፈታት ይሆናል እንጅ ዓመት ቢወራ ያልቃል እንዴ! ባጠቃላይ ግንቦት 20 ኢትዮጵያ የጨለማ ዘመኗን ሀ ብላ የጀመረችበት፣ ሕዝብ ሀገሩን የተቀማበትና በገዛ ሀገሩ በቀየው በመንደሩ ግፍ ሰቆቃ የሚቆጥርበት የሚጋትበትን፣ ኢትዮጵያ እንደ ሀገር የወደቀችበት ሕዝቧ እንደ ሕዝብ የተዋረደበትን የአጋንንት መንጋና ዘመን ያገኘንበት ዕለት ነው ግንቦት 20፡፡
መድኃኔዓለም ክርስቶስ ፈጥኖ ከእንቅልፋችን ቀስቅሶ ማቃችንን አውልቀን እንድንጥል ያስችለና!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!! ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!

በሐረርጌ የተቀሰቀሰው የተማሪዎች አመጽ ወደ ሌሎች ቦታዎች ተዳረሰ (የፍኖተ ዴሞክራሲ ራድዮ አጫጭር ዜናዎች)

 በተመድ ስር የሚሰሩ ወታደሮች ደሞዛቸው በወያኔ ባለስልጣናት እንደሚበዘበዝ ተጋለጠ
 ስደተኞች ለመቆጣጠር የተቋቋመው የአውሮፓ ህብረት ግብረኃይል የሊቢያን ጠረፍ ጠባቂዎች
እንዲያሰለጥን መመሪያ ተሰጥተው
 በኬኒያ ኩሱሙ በምትባለው ከተማ የተቃውሞ ኃይሎች ያካሄዱትን ሰላማዊ ሰልፍ ለማፈን
ፖሊሶች በወሰዱት እርምጃ ቢያንስ አንድ ሰው ተገደለ
 በዳርፉር መስጊድ ውስጥ የነበሩ ስምንት ሰዎች በአረብ ሚሊሺያዎች ተገደሉ
13254093_10102296231320823_8172214177964234618_n
ዝርዝር ዜናዎች
 ለሳምንታት ጋብ ብሎ የነበረው የተማሪዎች ተቃውሞና የሕዝብ እንድቅስቃሴ እንደገና መቀስቀስ
መጀመሩ ታወቀ። በሐረጌ በዓለማያ ዩኒቨርስቲ ውስጥ ያገረሽው የተማሪዎች ተቃውሞ እንቅስቃሴ
ለማፈን የወያኔ አግአዚ ጦርና የፌዴራል ፖሊስ ወደ ዩነቨርስቲው ግቢ ውስጥ በመግባት
የተማሪዎችን የመኝታ ክፍሎች ከቀላል መፈንከት እስከ አጥንት ስብራት የደረሰ ድብደባ
መፈጸማችው የሚታወቅ ሲሆን በዚህ የጭካኔ ድብደባ ምክንያት ተቃውሞና ሕዝባዊ ንቅናቄው
በሌሎች የኒቨርሲቲዎናች ከተሞች የተዛመተ መሆኑ ይነገራል። በወለጋ በነቅምት ዩኒቨርሲት
ተማሪዎች ተቃውሟቸውን እንደገና ማሰማት የጀመሩ ሲሆን ወያኔም እንደተለመደው ነፍሰ ገዳይ
አግአዚ ወታደሮችን አሰማርቷል። የሆሩ ጉድሩና የከምቦልቻ ከተማ ነዋሪዎችም ዳግም የመብት
ጥያቄን አንግበው አደባባይ መውጣት ጀምረዋል።
 የወያኔ አገዛዝ ዓለም አቀፍ አስዳሪዎቹን ለማስደሰትና እግረ መንገዱንም ጠቀም ያለ ገንዘብ
ለመሰብሰብ በማሰብ በተመድ ስር በሺህ የሚቆጠሩ ወታድሮች ያሰማራ መሆኑ ይታወቃል። ተመድ
ከፍተኛ የሆነ ደምዝ ለወታደሮቹ በየጊዜው ቢከፈልም የወያኔ የጦር አለቆች ገንዘቡን በመረከብ
ወታደሮችን እየበዘበዙ መሆናቸው ታውቋል። ወታደሮቹ የሞት አደጋ ሲደርስባቸው በግልጽና በይፋ
የማይነገር ሲሆን የተመድ የህይወት ካሳ ክፍያንም ባለስልጣኖቹ እንደሚቀራመቱት ይታወቃል።
ተመድ ባለፈው ሳምንት የተመድ የሰላም አስከባሪዎች ቀንን ምክንያት በማድረግ በተመድ ተልእኮ
ስር ሆነ የተገደሉ ስምንት የወያኔ ወታደሮችን የሸለመ ሲሆን የተለያዩ አገሮች ዜጎች የሆነ 128
ወታደሮቹን ተልእኮውን በመፈጸም ህይወታቸው በማለፉ ክብርና ሚዳሊያ ሰጥቷል።
 በኬኒያ ምዕራባዊ ግዛት በምትገኘው ኩሱሙ በምትባለው ከተማ የተቃዋሚ ኃይሎች ደጋፊዎች
ትዕንተ ሕዝብ ያካሄዱ ሲሆን ከፖሊሶች ጋር በተካሄደው ግጭት ቢያንስ አንድ ሰው የሞተ መሆኑን
የዜና ምንጮች ዘግበዋል። ሟቹ የተገደለው ከፖሊሶች በተተኮሰ ጥይት ነው የሚለውን ዜና የፖሊሱ
ክፍል አስተባብሎ ግለሰቡ ወድቆ መሞቱን ገልጿል። ባለፈው ሳምንት በኬኒያ ዋና ከተማ
በተደረገው የተቃውሞ ስልፍ ፖሊሶች ሰልፉን ለመበተን የኃይል እርምጃ መውሰዳቸው ይታወሳል።
በኩሱሙ የተደረገው ስልፍ የተቃዋሚ ፓርቲዎች የምርጫ ኮሚሽኑን የአድልዎና ብልሹ አሰራር
በመቃወም በተከታታይ ካደረጓቸው ስለፎች ውስጥ አራተኛ መሆኑ ነው።
 የአውሮፓው ኅብረት ሰኞ ግንቦት 15 ቀን ባደረገው ስብሰባ ስደተኞች የሚዲትራኒያን ባህር
አቋርጠው ወደ አውሮፓ እንዳይዘለቁ ለመከላከል የተቋቋመው የባህር ኃይል ግብረ ኃይል የሊቢያ
ጠረፍ ጠባቂዎችን በማሰልጠን ተግባር ላይ እንዲሰማራ ተጨማሪ ኃይላፊነት የሰጠው መሆኑ
ተገልጿል። አፕሬሽን ሶፊያ በመባል የሚታወቀው ይኸው ግብረኃይል በሚቀጥለው ሐምሌ ወር
ውስጥ ኃይላፊነቱ የሚያበቃ መሆኑ የታወቀ ሲሆን በብራስል የተሰበቡት 28 የአውሮፓ አገሮች
የግብረኃይሉን እድሜ ለአንድ ዓመት እንዲራዘም አድርገዋል። ግብረኃይሉ ከተቋቋመ ጀምሮ
ያስገኘው ውጤት አነስተኛ ነው በሚል በተደጋጋሚ ወቀሳ የቀረበበት ሲሆን ኃይሉ እንዲጠናከርና
በማሰልጠን ተግባር ላይ እንዲሰማራ የተወሰነው ድክመቱን አርሞ ውጤት እንዲያስገኝ ነው
ተብሏል።
 በዳርፉር የአረብ ሚሊሺያ አባሎች በአንድ መስጊድ ውስጥ በተሰበሰቡ ሰዎች ላይ በወሰዱት ጥቃት
ቢያንስ ስምንት ሰዎች መገደላቸው ታውቋል። ቀደም ብሎ በአንድ የገበያ ቦታ አንድ የአረብ
ብሔረሰብ አባል የሆነና አንድ የመሳሊት ማህብረሰብ አባል የግል አለመግባባት ፈጥረው በተደጋጋሚ
በዱላ የተመታው መሳሊት አረቡን በስለት ገድሎት እንደነበር ከቦታው የተገኘው ዜና ይገልጻል።
የአረቡ ሚሊሺያ አባሎች ለአረቡ መገደል በወሰዱት የበቀል እርምጃና በአካሄዱት የእሩምታ ተኩስ
በመስጊድ ውስጥ የተሰበሰቡ ስምንት ነዋሪዎችን መግደላቸውንና ከእነዚህ ውስጥ ሁለቱ ልጆች
መሆናቸውን የዜና ምንጮች ገልጸዋል።
 በደቡብ አፍሪካ በፕሬቶሪያ ከተማ ሰሜናዊ ክፍል በህገ ወጥ መንገድ የተሰሩ ቤቶችን ለማፍረስ
የጸጥታ ኃይሎች የወሰዱትን እርምጃ በመቃወም ነዋሪዎቹ የተቃውሞ እንቅስቅስቃሴ
ማድረጋቸውን ከስፍራው የተገኘ ዜና ያስረዳል። ሰኞ ግንቦት 15 ቀን በነበረው ግጭት ቤቶች
ለማፍረስ ከተላከው የአፍራሽ ግብረኃይል አባላት ውስጥ ቢያንስ ሁለቱ መገደላችውን የደቡብ
አፍሪካ ባለስልጣኖች ገልጸዋል። ባለስልጣኖቹ ሃማንስክራል በሚባለው የከተማው አካባቢ በሺ
የሚቆጠሩ ሰዎች በህገ ወጥ መንገድ የሚኖሩ መሆናቸውን ጠቁመው ቦታውን ለማጽዳት ከፍርድ
ቤት ፈቃድ የተሰጣቸው መሆኑን ገልጸዋል።

ጋዜጠኛው አበበ ገላው ያደረገውን በፌስቡክ ጠቅሰህ ሕዝብን ለማነሳሳት ተጥቅመህበታል በሚል በሽብር ተከሰሰ


  • 609
     
    Share
Negere-Ethiopia-edtor-Getachew-Assefa-300x200.jpg
(ዘ-ሐበሻ) የኦሮሚያ ተማሪዎች አመጽ በተቀጣጠለበት ሰሞን መንግስት አስሮ ለረዥም ጊዜ ክስ ሳይመሰርትበት የቆየው ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው በፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ጋዜጠኛ አበበ ገላው ያደረገውን አድንቀህ ሕዝብን ለማነሳሳት ተጠቅመህበታል እና ከኢሳት ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም ጋር በፌስቡክ እና በስልክ አውርተሃል በሚል የሽብርተኝነት ክስ ቀረበበት::
እንደ ክሱ ዝርዝር ከሆነ
“ተከሳሽ (ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው) በሚጠቀምበት ማህበራዊ ድህረገአጽ በተለይም ፌስቡክ አድራሻው ተጠቅሞ በውጭ ሃገር የሚገኝ የሽብር ቡድኑ አመራር እና አባል ከሆነው አበበ ገላው በልደታ ከፍተኛ ፍ/ቤት በጸረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ተከሶ በመዝገብ ቁጥር 112546 የጥፋተኝነት ውሳኔ ከተሰጠው ጋር ግንኙነት በመፍጠር በቀን 01/9/2006 ዓ.ም በአቶ መለስ ላይ ያደረገው ተቃውሞ መስቀል አደባባይ ላይ ከሚደረግ አንድ ሚሊዮን ሕዝብ የተሳተፈበት የተቃውሞ ሰልፍ የማይተናነስ ነበር:: አሁንም እንዲሁ ኦባማ ላይ ደግሞታል:: የአቤ ጩኸት ዝም ብሎ ያለመገዛት አንድ ድምጽ ብትሆን ለውጥ እንደምታመጣ በጽኑ የማመን ለውጥ አይመጣም ብሎ በተስፋ መቁረጥ ከመቀመጥ የራስን አስተዋጽኦ ማድረግ የተግባር ሰው መሆን ነው በማለት ከሽብር ቡድኑ አባል ጋር የአመጽ ጥሪ በማስተላለፉ”
የሽብር ክስ ተመስርቶበታል 

ዛሬም በቦሌ ክፍለከተማ ወራ ጋኑ አካባቢ 2 ሰዎች በፌደራል ፖሊስ ተገደሉ * በርካታ ሰዎች የደረሱበት ጠፋ

Filed under: News Feature,የዕለቱ ዜናዎች | 
  • 972
     
    Share
(ቤታቸው የፈረሰባቸው ወገኖች በአደባባይ እንዲሁም ፌደራል ፖሊሶች አካባቢውን ወረውት)
(ቤታቸው የፈረሰባቸው ወገኖች በአደባባይ እንዲሁም ፌደራል ፖሊሶች አካባቢውን ወረውት)
(ቤታቸው የፈረሰባቸው ወገኖች በአደባባይ እንዲሁም ፌደራል ፖሊሶች አካባቢውን ወረውት)
(ቤታቸው የፈረሰባቸው ወገኖች በአደባባይ እንዲሁም ፌደራል ፖሊሶች አካባቢውን ወረውት)
(ቤታቸው የፈረሰባቸው ወገኖች በአደባባይ እንዲሁም ፌደራል ፖሊሶች አካባቢውን ወረውት)
(ቤታቸው የፈረሰባቸው ወገኖች በአደባባይ እንዲሁም ፌደራል ፖሊሶች አካባቢውን ወረውት)
(ዘ-ሐበሻ) በአዲስ አበባ ከተማ በቦሌ ክፍለ ከተማ ስር ባለው ወራ ጋኑ በተባለው አካባቢ የመንግስት ሃይሎች የአካባቢውን ነዋሪዎችን መኖሪያ ቤቶች በማፍረስ ለሃብታሞች መሬቱን እየቸበቸቡት ሲሆን ዛሬም ቤቶቹን ለማፍረስ ከሄደው ግብረሃይል ጋር የነበረው ፌደራል ፖሊስ 2 ሰዎችን መግደሉን የአካባቢው ሰዎች አስታወቁ::
ከስፍራው የሚመጡ መረጃዎች እንደጠቆሙት በዚሁ አካባቢ ሰሞኑን መሬቱን ለባለሃብቶች መሸጡን ተከትሎ ከ6 ሺህ የማያንሱ ቤቶች ህገወጥ ናቸው በሚል ፈርሰዋል::
ፌደራል ፖሊስ ባለፈው ሳምንት እንዲሁ በዚሁ አካባቢ ቤቶችን ሲያፈርስ በህዝቡ ተቃውሞ ሲደርስበት ከ10 በላይ ሰዎችን መግደሉን ዘ-ሐበሻ መዘገቧ የማይዘነጋ ሲሆን ዛሬም ድርጊቱን የተቃወሙና የት ሄደን እንኑር ያሉ ወገኖች ከመደብደባቸውም በተጨማሪ 2ቱ ሲገደሉ ከ20 በላይ ሰዎችም ታፍነው መወሰዳቸውና የት እንደደረሱ እንደማይታወቅ የአካባቢው ሰዎች ገልጸዋል::

መንገዱን ጨርቅ ያድርግላችሁ ብሎ ሞተ (ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም)

መስፍን ወልደ ማርያም
መንገዱን ጨርቅ ያድርግላችሁ፣ ይቅናችሁ ማለት ነው፤ ለልማት ለሚሰማሩ ሰዎች ምርቃት ይሆናል፤ ለጥፋት ለሚሰማሩ ሰዎች እርግማን ነው፤ እርግማን ብቻም አይደለም፤ የጥፋት ምኞትም ነው፤ ሰዎች ለጦርነት ሲዘጋጁ፣ ሰዎች ሌሎች ሰዎችን ለመግደል ሲሰናዱ፣ ሰዎች እርስበርሳቸው ለመገዳደል ጦራቸውን ሲስሉ መንገዱን ጨርቅ ያድርግላችሁ ማለት ከጀግና አንደበት የሚወጣ አይደለም፤ ብዙ ሰዎች ለእንጀራ ብለው ሕይወታቸውን ወደአጥርነት ለውጠው ሕይወቱን የሚጠብቁለት ሰው ጦር ቢወረወር አይደርስብኝም ብሎ ሌሎችን ለሞት ቢዳርግ አይደንቅም ይሆናል፤ አጥሩን ጥሶ ወደሱ የሚገሰግስ ሞት ሲያይ ቢፈረጥጥም አያስደንቅም፤ ሆኖም የሞት መንገድ ከጎን ብቻ ሳይሆን ከላይም ሊሆን እንደሚችል አለማወቁ ቀላል አለማወቅ አይባልም፡፡Mesfin Woldemariam
ባህላችን ገዳይን የምናከብር፣ ለገዳይ የምንዘፍን ሕዝብ ቢያደርገንም፣ በድንቁርና ዘመን የነበረውን ይዘን ዛሬ ትንፋሽ የማትችለዋ ቢምቢ ሰውን መግደል እንደምትችል እያወቅን ለገዳይ ብንዘፍን ለሰውነታችን ውርደት ይሆናል፤ ይህንን ብለን ጉዳዩን እንዳንዘጋው በመግደል ልቡ የደነደነ፣ በድን ያልሆነለትን ሁሉ መግደል ልማዱ የሆነ፣ ከመግደል በቀር እምነቱን የሚገልጽበት መንገድ የሌለው፣ ከመግደል ሌላ እንጀራ የሚበላበት ሙያ የሌለው … እንዲህ ያሉ ሰዎች ሁሉ ተሰባስበው መገዳደልን የኑሮአቸው ዓላማና ዘዴ ሲያደርጉ በዝምታ መቀበል፣ ማለት አባቱ ሲገደል ልጁ ዝም ሲል፣ ባልዋ ሲገደል ሚስት ዝም ስትል፣ … ማንም ሰው አለፍርድ ሲጠቃ እያዩ ዝም ማለት ገዳዮችን ያራባል እንጂ ግድያን አያቆምም፤ እንዲህ ያለው በመንፈስ የሞቱ የበድኖች ዓለም ነው፤ በአውሬዎች ዓለም ጉልበት ያለው ደካማውን እየበላ ይኖራል፤ የተፈጥሮ ሕግ ነው፤ የሰው ልጅ በዚህ በአውሬዎች የተፈጥሮ ሕግ አይመራም፡፡
የሰው ልጅ በተፈጥሮ ሕግ የማይመራበት ምክንያት ምንድን ነው? አውሬዎች አያስቡም፤ የሰው ልጅ ግን ያስባል፤ የሰው ልጅ አእምሮ አለው፤ አእምሮ ስላለው ያስባል፤ ያስባል ማለት ከተግባር በፊት ትክክለኛውንና ስሕተት ያለበትን ለይቶ ያውቃል፤ ይህ የተፈጥሮ ሕግ አይደለም፤ የሰው ልጅ ሕግ ነው፤ ያሰበውንም ይናገራል፤ የሚወደውንና የሚጠላውን ስሜቱን ለይቶ ይናገራል፤ የሰው ልጅ ኅሊናም አለው፤ ‹‹ሌሎች ለአንተ እንዲያደርጉልህ የምትፈልገውን አንተም ለሌሎች አድርግ!›› ይላል፤ ይህ የተፈጥሮ ሕግ አይደለም፤ የሰው ሕግ ነው፤ ስለዚህም መግደል፣ በተለይም የመግደል ሱስ፣ የአራዊት እንጂ የሰው ልጅ የችግር መፍቻ ዘዴ አይደለም፤ አራዊት የሚገድሉት ሊበሉ ነው፤ ሰውም ወደአራዊትነት ሲለወጥ የሚገድለው ሊበላ ነው፤ እዚህ ላይ ሰውና አራዊት ይመሳሰላሉ፡፡
በመሠረቱ የመግደል ዓላማ ዝም ለማሰኘት ነው፤ ድንቁርና ነው እንጂ ካፍ ከወጣ አፋፍ ነውና የሚጠሉት ሀሳብ በሌላ ሰው አንደበት ይደገማል፤ መግደል የመጨረሻውን ዝምታ የሚያስከትል ቢሆን ክርስትናም እስልምናም 2007 ዓ.ም. አይደርሱም ነበር፤ ገዳዮች ሰዎችን ሁሉ ጨርሰው ብቻቸውን በመቅረት የሚያገኙት ጥቅም እንደሌለ ስለሚያውቁ የመግደል አማራጮች በሆኑ ሌሎች ዘዴዎች ይጠቀማሉ፤ አንዱ ማሰቃየት ነው፤ ሌላው ማሰር ነው፡፡
ሰዎችን በሀሳብና በእምነት ገባር ለማድረግ ጉልበተኞች የሚጠቀሙባቸው ዘዴዎች መግደል፣ መግደል አላዋጣ ሲል ማሰቃየት፣ ማሰቃየት አላዋጣ ሲል ማሰር፣ ማሰር አላዋጣ ሲል አስሮ ማሰቃየት ነው፡፡
አውሬነትን የተላበሱ ሰዎች የማይገባቸው አንድ ነገር አለ፤ የሚጠሉትና ሰዎችን እስከመግደል፣ እስከማሰርና ማሰቃየት የሚያደርሳቸው ነገር በውስጣቸው ተቀብሮ አለ፤ ነፍሳቸው ከዚያ ነገር ጋር ተቆራኝታለች፤ በመጨረሻም የሚሸነፉት በዚያው ነፍሳቸው ውስጥ በተቀበረው ነገር ነው፤ በውስጣቸው የተቀበረው ነገር አስገድሎ አስገድሎ በመጨረሻ ይገድላቸዋል፤ ጥላቻም አስገድሎ አስገድሎ ይገድላል! በጥላቻና በመጋደል ሰላም አይገኝም፤ ‹‹ለክፉዎች ሰላም የላቸውም ይላል እግዚአብሔር!›› (ኢሳይያስ 48/22)
መንገዱን ጨርቅ ያድርግልን! ለሰላም!
መንገዱን ጨርቅ ያድርግልን! ንስሐ ለመግባት!
መንገዱን ጨርቅ ያድርግልን! ይቅር ለእግዚአብሔር ለመባባል!
የዛሬ ዕብሪተኞች የሙሶሊኒን (ተዘቅዝቆ የተሰቀለውን)ና የጋዳፊን ቦይ ውስጥ ተወትፎ የተገኘውን አስበው ልባቸውን ለምሕረትና ለእርቅ እንዲከፍቱና ለልጆቻቸው የፍቅርና የመተማመን ዘመን እንዲያውጁ እግዚአብሔር መንፈሳዊ ወኔ ይስጣቸው፡፡

በጋዜጠኛ ጌታቸው ሺፈራው ላይ የቀረበው የሽብር ክስ ዝርዝር

Ethiopia Human Rights Project
የፌደራል አቃቤ ህግ ግንቦት 10/2008 ዓ.ም በተጻፈ የክስ ማመልከቻ የሽብር ክስ የመሰረተበት የነገረ ኢትዮጵያ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ሺፈራው ላይ የቀረበው ክስ የጸረ ሽብር አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 7(1) ላይ የተመለከተውን የወንጀል ድርጊት መተላለፍ የሚል ነው፡፡Getachew Shiferaw
ተከሳሹ ከ24/05/2006 ዓ.ም እስከ 13/04/2008 ዓ.ም ድረስ ባሉት ጊዜያት ግንቦት ሰባት ከተባለ የሽብር ድርጅት አመራሮች ጋር በማህበራዊ ድረ ገጽ በተለይም ፌስቡክ እና ስልክ ግንኙነት በመፍጠር ለሽብር ቡድኑ ተልዕኮ የተለያዩ መረጃዎች በማስተላለፍና በሽብር ድርጅት ውስጥ መሳተፍ ወንጀል ፈጽሟል ሲል አቃቤ ህግ በክሱ ላይ ጠቅሷል፡፡
በአቃቤ ህግ ክስ ላይ እንደተመለከተው ተከሳሽ ጋዜጠኛ ጌታቸው ሺፈራው በህግ ተመዝግቦ በሀገር ውስጥ ህጋዊና ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ የሚያደርገው ሰማያዊ ፓርቲ አባላት ጋር ያደረገው የመልዕክት ልውውጥ ክስ ሆኖ ቀርቦበታል፡፡
ጋዜጠኛ ጌታቸው ሺፈራው ከተለያዩ ውጭ ሀገር ከሚገኙ ሚዲያዎች ባለሙያዎች በተለይም ኢሳት ጋር ያደረጋቸው ቃለ-መጠይቆችና የመረጃ ልውውጦችም በሽብር ክስነት ቀርበውበታል፡፡ ተከሳሹ በሽብርተኝነት ክስ ተከሰው በእስር ላይ የሚገኙ ዜጎች ቤተሰቦቻቸውን እንዴት ማገዝ ይቻላል በሚል ከዳያስፖራ አባላት ጋር በማህበራዊ ድረ ገጽ የተለዋወጣተቸው መልዕክቶችም በክሱ ላይ ተካተው ቀርበዋል፡፡
በአጠቃላይ ጌታቸው ‹‹…በተለያዩ አካባቢዎች ከሚገኙ የሽብር ቡድኑ አባላት ጋር እየተገናኘ መረጃ በመሰብሰብ በውጭ ሀገር ለሚገኙ የሽብር ቡድኑ አመራሮች መረጃ በማስተላለፍ….›› በሽብር ድርጅት ውስጥ በማናቸውም መልኩ መሳተፍ ወንጀል ክስ ቀርቦበታል፡፡
ጋዜጠኛ ጌታቸው ሺፈራው ለአምስት ወራት በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ቆይቶ ባለፈው ሳምንት ክስ ተመስርቶበት ቂሊንጦ በእስር ላይ ይገኛል፡፡ ግንቦት 26/2008 ዓ.ም የቀረበበት ክስ በፍርድ ቤት ሊነበብለት ቀጠሮ ተሰጥቶታል፡፡

Wednesday 4 May 2016

Ethiopia: Endless Injustices against Oromo Nation in the Name of Law Enforcement - See more at: http://www.zehabesha.com/ethiopia-endless-injustices-against-oromo-nation-in-the-name-of-law-enforcement/#sthash.tTEWaJ2C.dpuf

HRLHA Press Release
May 3, 2016
The Human Rights League of the Horn of Africa (HRLHA) strongly condemns the TPLF/EPRDF Government’s endless manipulations of the justice system to its own political ends, which was once again manifested in the fully fabricated allegations and charges filed against 22 (twenty-two) Oromo nationals. It surprised no one that the TPLF/EPRDF Government, as usual, used the infamous legal tool of the Anti-Terrorism Law, as a result of which thousands of innocent Oromos and other nationals have been victimized, to arrest, detain and take to court another batch of Oromo activists. These newest allegations and attempts of abusing the justice system are taking place following the months-long and region-wide public protests in Oromia; and are, undoubtedly, parts of the heavy-handed crackdown, which included the imposition of martial law in the Regional State in an effort to suppress the public anger and demands for change.
ETHIOPIA-UNREST
As described by some international legal analysts, the Ethiopian Anti-Terrorism Law “… criminalizes basic human rights, especially freedom of speech and assembly. The law defines terrorism in an extremely broad and vague way so as to give the government enormous leeway to punish words and acts that would be perfectly legal in a democracy”. This is the reality that came into play in the case of these newly made allegations against 22 Oromo nationals.
According to documents obtained by HRLHA, the 22 Oromo nationals, including top political leaders of the opposition Oromo Federalist Congress party, such as Mr. Bekele Gerba (Deputy Chairman) and Mr. DejeneTafa (Deputy Secretary General), Addisu Bulala and others have been charged with allegedly conspiring to overthrow the government by means of instigating a public revolt and protests as well as collaborating with other political organization called Oromo Liberation Front. The new creation in this case is that attempts were made to associate the officially registered and legally operating political parties like the OFC with opposition political organizations that were deemed outlaw by the Ethiopian Government in order to criminalize their legitimate existence and activities.
It is so unfortunate that Mr. Bekele Gerba is being subjected to such politically and racially motivated injustice and the resultant sufferings in Ethiopian substandard jails for the second time in a matter of two years.
The HRLHA has ample documents that hundreds of thousands of innocent Oromos and members of other nationalities have already fallen victims of such injustices and dictatorship committed particularly using this Anti-Terrorism Law, described by some as “a tool to stifle dissent”, as a legal weapon.
Local, regional and international communities have repeatedly witnessed over the past twenty-five years that the TPLF/EPRDF Government of Ethiopia misuses the political power, the justice system, and other public resources to silence and/or eliminate all forms of oppositions and political descents, despite the constitutionally declared democracy, in order to ensure monopoly and lasting partisan political goals. But, no tangible and effective actions are taken so far to make the Ethiopian Government refrain from punishing its own citizens just for exercising or attempting to exercise some of their basic and constitutionally provided democratic rights.
The HRLHA, first of all, calls upon the Ethiopian Government to unconditionally release these Oromo nationals detained and charges for allegedly committing acts of terrorism; as their words and/or acts are undoubtedly legal and, above all, constitutional. HRLHA also calls upon the international community’s so that they condemn the Ethiopian Government, acts of injustices against innocent citizens, and request that these unjustly detained and falsely charged Oromos are freed unconditionally.
RECOMMENDED ACTION: Please send appeals to the Ethiopian Government and its concerned officials as swiftly as possible, in English, Amharic, or your own language expressing:
For the immediate and unconditional release of prisoners illegally detained
Urging the Ethiopian authorities to ensure that these detainees would be treated in accordance with the regional and international standards on the treatment of prisoners,
- See more at: http://www.zehabesha.com/ethiopia-endless-injustices-against-oromo-nation-in-the-name-of-law-enforcement/#sthash.tTEWaJ2C.dpuf

የላብ አደሮች ቀን ለኛ በተለይ ለሴቶች ምናችን ነው? (አርሴማ መድህኑ – ኦስሎ ኖርዌ)

አርሴማ መድህኑ – ኦስሎ ኖርዌ
ካፒታሊስት አገሮች አንድ የቆየና ጊዜ ያነኩዋኮተው አባባል አላቸው። ይህንን አባባል ያስታወሰኝ ዛሬ እዚህ ያሰባሰበን ” የላብ አደሮች ቀን” ነው። ይቅርታ ይደረግልኝ ” ወይንም የዓለም የወዛደሮች ቀን” ኢትዮጵያችንን ጨምሮ መሆኑ ነው። ያው እንግዲህ የዚሁ ዓለም አካል በመሆናችን !!
አባባሉ እንዲህ ነው። “በካፒታሊስት ስርዓት ውስጥ ሰራተኛ የስርዓቱ ባሪያ ነው። ሴት ደግሞ የባሪያ ባርያ ናት” ይህን አባባል ኢህአዴግ ወደ ሚገዛት አገራችን ህወሃታዊ ቁዋንቁዋ ስንመልሰው ” በጥቅሉ የ ላብ አደሮች የህወሃት ባሪያዎች ናቸው። ሴቶች ደግሞ የባሪያ ባሪያዎች ናቸው” እንግዲህ ኢህአዴግ በጥቅሉ የህወሃት ባሪያ ድርጅት ከሆነ አባባሉ መሻሻያ ሊደረግበት ግድ ነው። ሲሻሻል ” ኢህአዴግ የህወሃት ባሪያ ከሆን ሁሉም “ላብ አደሮች የህወሃት ባሮች ናቸው። ሴቶቹ ደግሞ ይበልጥ ባሮች ናቸው”
በአገራችን ላብ አደሮች አሉ።ላብ አደሮቹ በሙሉ አምነውም ይሁን ሳያምኑ ኢህአዴግና አፍቃሪ ህወሃት ናቸው። በድንገት በተስፈነጠሩት የህወሃት የነገር አባት አባባል ” በመርህ ደረጃ” ሁሉም ሰራተኛ የ “ተጠረነፈ” ካልሆነ በስተቀር ” ላብ አደር ” የሚለውን ክብር አያገኝም። ስለዚህ ላብ አደር ለመሆን ቅድሚያ ህወሃትን የግል አምልኮ አድርጎ መቀበል ግድ ነው። አለያ ስራ አይታሰብም። ኑሮም ገደል ነው። ካብራክ የወጡ ልጆችን አቃምሶ ማሳደርና ማስተማር ህልም ይሆናል።
ባገራችን ነጻ ማህበር በሎ ነገር የለም። ነጻ ሆኖ የመደራጀት ጭላንጭል አይታይም። ህወሃት ባርኮና መርቆ፣ መሪ ሰይሞና መተዳደሪያ ደንብ አርቅቆ ያላቁዋቁዋመው ድርጅት ይፈረሳል። ተለጣፊ ተስይሞለት በፍርድ ቢት ሙዋምቶ እንዲከስም ይደረጋል። በዚህ ሃቅ መሰረት ላብ አደሮች ኢትዮጵያ ውስጥ ማህበር የላቸውም። እና በዛሬው ቀን አገራቸው ውስጥ በነጻነት መደራጀትና ጥቅማቸውን ማስከበር ያልቻሉ ላብ አደሮች የዓለም የወዛደሮች ቀን ምናቸው ነው? እስኪ ከሴቶች ጋር ላገናኘው።
ሴቶች በፐሮቶኮል ስምምነት ወደ አረብ አገራት እየተሻገሩ ሲደፈሩ፣ ሲንገላቱ፣ ከፎቅ ላይ ሲወረወሩ፣ በየጎዳናው ሲጎተቱ …….. መስማትና ማየት የተለመደ ነው። በረሃና ባህር የበላቸውን ቤት ይቁጠራቸው። ራስን መግቦ ለማሳደር አለመቻል በሚፈጥረው የስነልቦና ህመም፣ ህወሃትን አምለኮ አድርገው ያለመቀበል ጣጣ፣ ድህነት፣ ቅጥ ያጣው ብሔርን መሰረት ያደረገ አድልዎና የፖለቲካው ውል አልባ መሆን አንድ ላይ ተዳምሮ በተለይም ሴቶችን ክፉኛ ተጎጂ አድርጉዋቸዋል።
ለዚህ ነው ይህ ታላቅ ቀን በውስጡ በያዛቸው ፈሬዎች ሲለካ ” ሚያዝያ 23 ለኔ ምኔ ነው ?” ያልኩት!! አዎ መሳሪያ በያዙበት ወቅት ሲሞካሹ የነበሩትን የራሱን ሴት የበረሃ አባላት የበላ ህወሃት ለሌሎች ሴቶች ዜጎች ይራራል ማለት ህልም ነው። እናም በፕሮቶኮል ስምምነት ለአረብ አገራት ባርነት የሸጣቸውን ሴት ዜጎችን እያሰብን፣ ተሽጠውም የት ደረሱ ሳይባሉ፣ ከዓለም የስራተኛ ህግ ውጪ የሚበዘበዙ ሴቶች ጥሪ ወደ ጎን በሚባልበት ስርዓት ውስጥ ሆኖ ” የዓለም የወዛደሮች ቀን” ን ማክበር ፋይዳው አይታየኝም። እንደውም ስላቅ ነው። ፍሬዎቹ የደረቁበት ክብረ በአል እንደ ” ጣኦት አምልኮ ” ድንጋይ ስር እንደመርመጥመጥ ነው።
በኦሮሚያ ሴት እህቶችና እናቶች እስረኛ የጥፋባትን በማፈላለግ ላይ ናቸው። የተቀሩትም ስንቅ አመላላሽ ናቸው። እርም ያወጡም አምጦ መውለድን እየረገሙ ነው። በሰሜን የማንነት ጥያቄ ሃጢያት ሆኖ እናትና እህቶችን ሃዘን ደረት እያስደቃቸው ነው። በሶማሌ፣ በአፋር፣ በደቡብ ኢትዮጰያ እንዲሁ የሴቶች ችግር አሳሳቢና ህሊናን የሚወጋ ነው። በጋምቤላ የችግሩ ገፈት ቀማሾች ሴቶች ናቸው። ራሱ ህወሃት ይህን ሲነግረን አላፈረም። በዚህ ሁሉ ላይ ችጋር እየጠበሰን ነው። ችግሩ ተደምሮ የት እንደሚያደርሰን ሲታሰብ ቀውስ እንጂ መፍትሔ አይታይም። ግና ኢትዮጵያ የወላድ መካን አይደለችምና ተስፋ አለን።

የ25 አመቱ አጋጅ መሪ (ቢንያም ሙሉጌታ – ከኖርዌይ)

ቢንያም ሙሉጌታ ከኖርዌይ
ወያኔ በቆርጦ ቀጥል የቅንብር መርሁ መሰረት የህዝብን ጥያቄና እሮሮ ከሚፈልገው የበሬ ወለደ ዘገባው ጋር በማዛመድ 25 ለሚያህሉ በአምባገነናዊነት በተሞሉ አመታት በብቸኝነት
binyam mulugeta
ቢንያም ሙሉጌታ
በተቆጣጠረው የሀገሪቱ ሚዲያዎች፤ በጋዜጣ፣ በራዲዮ፣ በቴሊቪዥን፣ እና በመሳሰሉት የመገናኛ አውታሮች እውነታውን በመደበቅ ህዝብን በማስመረር ይገኛል ይህ ብቻ አይደለም በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የሚደርሰውን ወከባ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ከመገናኛ ብዙሀን አፈናው ጋር ተደምሮ በተለይም በአሁን ወቅት በተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች ላይ እየተደረገ ያለው አሰቃቂ ድርጊት ለአለም ሁሉ በገሀድ የሚታይ የአደባባይ ሚስጢር ሆኗል።
ነጻ ፕሬስ አልያም በጥቅሉ የመገናኛ ብዙህን መድረኮች ህዝብን ከመንግስት ጋር እንዲሁም ግልፅነት በተሞላበት አካሔድ የመንግስትን አሰራር ለህዝብ እያቀበለ እያስተዋወቀ መካከለኛ በመሆን  የዜጎችን  አስተያየትና ጥያቄዎች ለሚመራው መንግስትና ለሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ማስተላለፊያ ድልድይ ነው፡፡ መንግስትና ህዝብን አገናኝ፣ አስተያየትና ብሶትን መተንፈሻ፣ መፍትሄን መቀየሻ መሳሪያ ነው ፡፡ ነጻ ሚዲያ መልካም ሀሳቦች እንዲጎለብቱ፣ መታረም ያለባቸው ደግሞ እንዲታረሙ መጠቆሚያ ብርቱ ክንድም ጭምር ነው፡፡
ህዝብ ከገዢው  ወገን ትክክለኛ እና ወቅታዊ የሆኑትን መረጃዎን ለማግኘት እጅጉን ከባድ በሆነበት፤ ሒደቶችን  ከዜጋው በመደበቅ አሊያም በመሰወር በሀገራችን ምን እየተከናወነ እንደሆነ  የመገናኛ ብዙሀን አዋቂዎች ሙያቸውን ተጠቅመው  ለመግለጥ የሚያደርጉት ሁሉ ድምፃቸው ታፍኖ ትክክለኛው  የመረጃ ምንጭ ሆነው እንዳይሰሩ በማስፈራራት፤ይልቁንም ደግሞ ታላቅ ግፍ እና ውንጀላ እየተፈፀመባቸው ጋዜጠኞቻችንን እና ፀሀፍቶች በሙሉ ከአሽባሪ ጎራ ተመድበዋል። የህትመት ውጤቶች በእንዲህ አይነት  ውንጀላ መፈረጅ በራሱ በፍርድ የሚያስጠይቅ ጉዳይ ነው።  በእርግጥም ገዢው ፓርቲ  ለፕሬሱ ሆነ ለሚዲያው እድገት መጫዎት የሚገባው የራሱ ሚና ጎልቶ መውጣት በተገባው ነበር፤ ምክንያቱም የፕሬሱ እድገት የሀገሪቱን  አሰራር ዘመናዊ፣ ግልጽና ተጠያቂነት የሰፈነበት የማድረግ ሚናው የላቀ ስለሆነ ማለት ነው፡፡
የወያኔን ከወረቀቱ የማይከብድ  ህገ-መንግስት ተብዬውን ያየነው እንደሆን   ዜጎች በአመቻቸው መንገድ ሁሉ ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትን ሰጥቶ እንደገና በተግባር ግን መብቱን በአደባባይ እየጣሰ ይገኛል፡፡ ወያኔ ሌብነቱ መዝበራው ግድያውና ጭቆናው እንዲሁም በራሱ ላይ የሚቀርቡበትን ማናቸውም አይነት ትችት በመፍራት ጋዜጦችን እና መጽሔቶችን ይዘጋል፤ ያግዳል፤ ድህረ-ገጾችን ‹ብሎክ› ያደርጋል፤ እንዲሁም ጋዜጠኞችን በተደጋጋሚ ለእስርና ለእንግልት፣ አንዳንዴም ለሞት እንዲዳረጉ በማድረግ የህዝብን መረጃ በነጻነት የማግኘትን መብት በከፋ ሁኔታ እያፈነ ይገኛል፡፡
በአንድ ያደገ ሀገር ብቃት ያለው ህዝብን የሚያገለግል ሚዲያ አለ፤ ህዝብም የመረጃ ነፃነት እንዳለው ያውቃል ይህንንም የሚያስፈጽም መንግሥት አለ። በመሆኑም መንግሥት ህዝብና ሚዲያ በመቀናጀት ብቃት ያለው መረጃ ለህዝብ ያደርሳሉ። እኛ ግን ለዚህ ፈፅሞ አልታደልም!!!
ወያኔ ከሚጠቀምባቸው የማገጃ ስልቶች የመጀመሪያው “አዳዲስ ሕጎችን በማውጣት በነጻነት ሐሳብን መግለጽን መከልከል እና እንዲህ የሚያደርጉትንም ማሰር”  ነው። ሌላው ደግሞ ሰዎችን በገንዘብ በመደለል ስለ መንግሥታቱ በጎ ነገር (እንዲጽፉ፣ እንዲናገሩ፣ እንዲያሰራጩ) ማድረግ እንዲሁም አሉታዊ ሐሳብ የሚያስፋፉትን ሰዎች ድረ ገጾች በዘዴ በመስረቅ (hijacking and hacking) በስማቸው ተገቢ ያልሆነ ነገር መለጠፍ የሚለው ነው። ይህንንም ዓለም በስፋት እየተጠቀመች ያለውን  ፌስ ብክ አንድ ሰው ከአንድ በላይ አካውንት በመክፈት ብሔርን ከብሔር ጎሳን ከጎሳ በማባላት እና በማጋጨት ደርጃ ወያኔ በዚህ ተልካሻ ስራ ተጠምዶ እንዳለ ግልፅ ነው። ይህም ድርጊት ተግባራዊ የሚሆንበት ወጪ የሚገኝውም ከደሀው  ሕዝቡ  በተነጠቀ ገንዘብ ነው። ማንነታቸው የማይታወቁ ሰዎችን በኢንተርኔት ላይ በማሰማራት የተለያዩ ደጋፊ ሐሳቦችን ማሰራጨት፣ የኢንተርኔት የውይይት አቅጣጫዎችን ማስቀየር፣ ተቃዋሚዎችን በተለያየ መንገድ ማዋረድ እና ክብራቸውን መንካት፣ ስለ ተቃዋሚዎች መሠረት የለሽ አሉባልታዎችን በመንዛት በአደባባይ ስለ ኢትዮጵያቸው እየታገሉ ያሉትን ስም ማበላሸት የወያኔ ዋነኛ እንቅስቃሴ ነው። ይህም ከፍርሀት የሚመጣ መሆኑን ሁሉም ይስማማበትል።
ወያኔ ከ20 ሚሊዩን ህዝብ በላይ  ተርቦ እህል እና ሌሎችም የልብስ የመጠለያ እንዲሁም የመድሀኒት እርዳታ ለማድረግ መረባረብ ሲገባው ከሀዲዎችን ቀጥሮ ለዚህ ሀገር በታኝ ተልዕኮው ማሰማራቱ ምን ያህል ስግብግብ እና ከፋፋይ መሆኑን በግልፅ የሚያሳይ ነው። በኢትዮጵያ ህዝብ ገንዘብ  ከሚሠሩት አፈና ባሻገር የማይደግፏቸውን ጦማርያን፣ የሚዲያ ተቋማት እና የፖለቲካ ፓርቲዎች የኢንተርኔት አድራሻዎች ማለትም ፌስቡክና ትዊተሮችን፣ ድረ ገጾችንና ብሎጎችን በመመዝበርም ይታወቃሉ። ወደ ተቃዋሚዎቻቸው የኢንተርኔት አድራሻዎች ሰብረው በመግባት የማይፈልጉትን ዘገባ፣ ዜና፣ ሐተታ ይለውጣሉ፤ የድረ ገጾቹን ባለቤቶች ሙያዊ ክብር ለማዋረድ እና ተቀባይነት ለማሳጣት የማይሆን ነገር ይለጥፋሉ፤ የሚለዋወጧቸውን ኢ-ሜይሎች ያነብባሉ፤ በክስ ወቅትም ለፍርድ ቤት በማስረጃነት የሚቀርቡት በተፈበረኩ የሀሰት ሰነዶች ምክንያት ደብዛቸው የጠፉ ምሁራን እጅግ ብዙ ናቸው። ይህንንም በመፍራት እና በመሸሽ በተገኘው አጋጣሚ ከሀገር ተሰደው በየበረሀውና በባህርም ሰጥመው የቀሩ ዜጎቻችንን ስናስብ በእጅጉ እናዝናለን። ከወያኔ አጋችነት እና አፋኝነት የተነሳ በዓለም ሁሉ የኢትዮጵያውያን አንገት እንዲደፋም ተደርጓል። ይህም የሚያሳየው ኢትዮጵያ ለዜጋ መብት ብሎም  እድገት የቆመ እና የሚታገል መሪ እንደሌላት ያስረዳል።
አጋጁ ማገድ ማንነቱ ነውና ሁሉን ያስራል ሲያሻው ለፖለቲካው መሰሪነት ሲል ይፈታል። በኢትዩጵያ ያልታገደ የለም። ለወያኔ እንቅፋት የሆነ ሁሉ ይያዛል፤ ብዙ የወንበዴ ብዕሮች ለሆዳቸው ያደሩቱ የፈራረሰውን ስርዐት ለመጠጋገን ቢሞክሩም እውነት ሁልጊዜም ትረታለችና ኢትዮጵያን ለ25 ዓመታት የሚመራው አጋጁ መሪ በኢትዮጵያውያን የተባበረ ክንድ ይገረሰሳል።
ኢትዩጵያ ለዘላለም ትኑር!!!

ከሆላንድ ወደ ኢትዮጵያ የገባውን ዲያስፖራ ስምንት ቦታ በሳንጃ ወግተው የገደሉት አልተያዙም!

Ethiopian Diaspora from Holland, Leykun Eshetu
(ኢ.ኤም.ኤፍ) ከሚኖርበት  ሆላንድ  ወደ  ትውልድ  ሃገሩ  ኢትዮጵያ  የገባው  ወጣት ለይኩን  እሸቱ  በፋሲካ  በዓል ዋዜማ  ስምንት ቦታ በስለት  ወግተው  የገገደሉት  ወንጀለኞች  እስካሁን  አልተያዙም። የአካባቢው ነዋሪዎች  እንደሚሉት ከሆነ  ገዳዮቹ  ባለጊዜዎች ስለሆኑ ሟች ደመ ከልብ ሆኖ ቀርቷል።
ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ አንድ የአካባው ነዋሪ ሲናገሩ፣  “ፍጹም፣ ቴዲ እና ባርያው በመባል የሚታወቁ እነዚህ ተጠርጣሪ ነብሰ ገዳዮች በአካባቢው ነዋሪን በእጅጉ ሲያስጨንቁ የኖሩ ናቸው። ይህ ግድያ የመጀመርያቸው አይደለም። ከወር በፊትም የንጹህ ዜጋ አይን አፍስሰዋል። ፖሊስ ግን አይይዛቸውም። ”  ብለዋል።
ይህ ሁሉ ሲሆን ፍትህ የሚያስከብር የመንግስት አካል እና  ህግ አስከባሪ ጉድዩን ችላ ብሎታል::  ከአንዳንዶች እንደሚሰማው ከሆነ ፖሊስ ለወንጀለኞቹ ሽፋን እየሰጣቸው ነው።  ከሟች የቀብር-ስነ ስርዓት በኋላ ህዝቡ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ  በሚገኘው ፖሊስ ድረስ በመሄድ ተጠርጣሪዎቹ በአስቸኳይ  እንዲያዙ ቢጠይቅም፤  ፖሊስ ለህዝቡ በጎ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ በህዝቡ ላይ ተኩስ መክክፈት ለቀስጠኛው  እንዲበተን አድርጓል።  ቪድዮውን ይመልከቱ።
የሟች ጓደኛ ዳንኤል ንጉሴም በግድያው  በተጠረጠሩት  አምስት  ግለሰቦች  በሳንጃ ተወግቶ ጥቁር አንበሳ  ሆስፒታል  ከፍተኛ ቀዶ ጥገና  ተደርጎለታል።
ለዚህ አሰቃቂ ግድያ እና አደጋ መነሻ የሆነ ምክንያት እንደሌለ ነው ሰዎች የሚናገሩት። ከህግ በላይ የሆኑ ባለግዜዎች እና  ጉልበተኞች እንዲሁ በማናለብኝነት የፈጸሙት ወንጀል ነው። ሃገሪቱ  ሰው ከቤቱ በስላም ወጥቶ ለመግባት ምንም ዋስትና የሌለበት ሃገር ሆናለች።
ይህ አሰቃቂ ግድያ  በሆላንድ የሚኖሩ የለይኩን ወዳጆችን በእጅጉ አስደንግጧል። ከቶውንም “ዲያስፖራ” ፣” ኢንቨስተር” ወዘተ እየተባለ የሚለፈለፈው ሁሉ ለዲያስፖራው ዋስትና ከማይሰጥ መንግስት መሆኑም አሁን ግልጽ የሆነ ይመስላል።

Home » ጦማሮች፣ አስተያየቶች እና ሌሎችም... » የኢትዮጵያ ወይንስ የትግራይ አየር መንገድ? (ይሄይስ አእምሮ) የኢትዮጵያ ወይንስ የትግራይ አየር መንገድ? (ይሄይስ አእምሮ)

ይሄይስ አእምሮ
የ2008ን የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ አንድ የኢትዮጵያ ይሁን የትግራይ ውሉ ባልታወቀ አየር መንገድ ውስጥ የሚሠራ ሰው በቤቱ ምሣ ጋበዘኝ፡፡ ተራ ጎረቤቱ እንጂ የሰማሁትን በሆዴ የማላሳድር ወሬ አራጋቢ መሆኔን አያውቅም፡፡ በሀገር ተቆርቋሪነት ስሜት በቀድሞው አጠራር ስለኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሁኑ ደግሞ ስለ”ትግራይ አየር መንገድ” እየተንገፈገፈ ሲናገር እንደማንኛውም ተጋባዥ አደመጥኩ፡፡ የምፈልገውን ወሬ ከጨበጥኩ በኋላ የተከፈተልኝን ቢራ እንኳን በቅጡ ሳልጨርስ ወደቤቴ አመራሁ –  እንደልማዴ ልጫጭር፡፡ ኢትዮጵያዊ የሆንክና አሁን የምነግርህን ከአሁን በፊት ያልሰማህ ሁሉ ይህን የወያኔዎች ቅሌት ልብ ብለህ ስማ! ኢትዮጵያ ዳግመኛ እንዳታንሠራራ ሆና በወያኔ መዶሻ እየተቀጠቀጠች መሆንዋንም አስተውል፤ ልጆችህ ሀገር አለን ብለው የማይኮሩባት አዲስ ኢትዮጵያ መፈጠሯንም ተገንዘብ፤ በተበተንክበት የስደት ዓለም ጠፍተህ እንድትቀር የተፈረደብህ ተስፋቢስ ትውልድ መሆንህን አትርሣ፡፡ ስለአየር መንገዱ የሚነገረው በባሰ ሁኔታ በሌሎች ላይ የሚሠራበት ወያኔያዊ አሠራር ነው – ለ25 ዓመታት የተሠራበት፡፡ በዚህ ተቋም እንዲህ የተሠራ በሌላው ምን ሊያቅታቸው?Ethiopian Airlines Boeing 767-300 flight from Addis Abba to Rome
ባለፈው ሰሞን አየር መንገዱ 27 ሆስተሶችን (የሴት አስተናጋጆችን)  አስመርቋል፡፡ በሚያስገርም ሁኔታ ሃያ ሰባቱም ትግሬዎች ናቸው፡፡ አዲስ አበባን የማያውቁና ብዙዎቹ አዲስ አበባ ውስጥ ቤተሰብ የሌላቸው ፍጹም ባላገር ሴቶች ናቸው፡፡ የተቀጠሩት ሁሉም ከትግራይ ምድር ነው፡፡ ለመሃላ እንኳን አንድም የሌላ ዘውግ አልተቀላቀለባቸውም – ቴክኒሻንና አብራሪም ሲመለመል እንዲሁ ነው፡፡ ከነዚህ ሆስተሶች ብዙዎቹ ዐማርኛ ቋንቋ አይችሉም፤ እርግጥ ነው – ከልጅነት እስከ ዕውቀት ዘመናቸው ዐማርኛ ከሚወገዝበት ክልል ተወልደውና አድገው የመጡ ወጣቶች በመሆናቸው በነሱ አይፈረድም፡፡ ነገር ግን የአየር መንገዱ አንደኛው የሥራ ቋንቋ የሆነውን ዐማርኛን ባለመቻላቸው ችግር እየፈጠሩ ይገኛሉ – ማኅበራዊነት (ሶሻላይዜሽን) ስለሚጎድላቸው ደግሞ ከሌሎች ሠራተኞች ጋር በቀላሉ መግባባት ካለመቻላቸውም በተጓዳኝ ቋንቋ አለመቻላቸው ሥራቸው ላይ ትልቅ አሉታዊ ጫና እየፈጠረባቸው ነው፡፡  አንድ ተጨባጭ ምሣሌ እንይ፡፡ በውነቱ ሕወሓት የትግራይ ሕዝብ በቀጣይ ታሪኩ እጅጉን የሚያፍርባቸው ብዙ ሰቅጣጭ ተግባራትን እየፈጸመ ነው፡፡ ስለወያኔ ትግሬዎች ሁላችንም ማፈር አለብን፡፡ ሃያ ሰባቱም ትግሬ? ውይ …ው ይ….ውይ…
ባለፈው አንድ ጊዜ ወደ አፋር ዋና ከተማ ወደ ሠመራ አንድ የሀገር ውስጥ በረራ ነበር፡፡ አንዷ ዐማርኛ እንደቁመት ያጠራት አስተናጋጅ ትግሬ “ህጅ አሥመራ ስለተቃሪብና ለቀቦቷቹ አጣብቁት” በማለት ለተሣፋሪዎች ማስታወቂያ በመናገሯ ተሣፋሪዎች አውሮፕላኑ ተጠልፎ አሥመራ ገብቶ ነው በሚል ተደናግጠው ክው ይላሉ፡፡ በኋላ ግን የቋንቋ ችግር መሆኑ ተነግሯቸው አሥመራ ሣይሆን ሠመራ እንደደረሱ ተገልጾ ይቅርታ ተጠይቀዋል – ተሣፋሪዎች፡፡ ሀሰት እንዳይመስልህ ሁሉም የአየር መንገዱ ሠራተኛ ሰምቶ የሚያላግጥበት እውነተኛ ታሪክ ነው፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ራሱ “የትግሬ” ወይም በተወራራሽ የቃላት አጠቃቀም “የትግራይ አየር መንገድ” ነው የሚባለው፡፡ በዚህ ዓይነት መንገድ በኢትዮጵያ ውስጥ ትግሬነትን አስጠልተውት እንዳይቀሩ እፈራለሁ – ከአሁኑ አንዳንድ ሁኔታዎች ተነስቼ እንደምታዘበው ይህን ጉዳይ በሚመለከት ችግር የለም ብሎ ራስን ማታለል የዋህነትና ከኃላፊነትም የመሸሽ ዝንባሌ ይመስለኛል፡፡ ብዙ ነገር መሠራት ሊኖርበት ነው – እንዴ? አያያዛቸው በጣም ያሣፍራል እኮ!
ከ27 አስተናጋጅ አንድ ሰባት ያህል እንኳን ለማስመሰል ከሌላው ብሔር ቢቀላቀል ምን ነበረበት? ይህን ምን ይሉታል? ምን ዓይነት መታወር ነው? ጭንቅላታቸው ውስጥ ጭቃ ነው ንፍጥ የታጎረው? የምትቀርቧቸው በተለይም ጤናማ ነን የምትሉ ትግርኛ ተናጋሪ  የሆናችሁ የትግራይ ልጆች እስኪ ጠይቋቸው፡፡ ከሰው አይደለም ከእንስሳም እንዲህ ዓይነት ድንቁርና አይጠበቅም፡፡ በስመ አብ!
በሌላ ቦታ በዐይኔ በብረቱ ያየሁትን ነገር ሳልረሳው ጣልቃ ላስገባ መሰለኝ፡፡ ቦታው ሲቭል ሰርቪስ ዩንቨርስቲ የሚባለው ድንጋይ ማምረቻ የትምህርትና የ“ኢንዶክትሪኔሽን”ማዕከል ነው፡፡ ከአንድ የመንግሥት ተብዬ መሥሪያ ቤት በስኮላርሽፕ ወደዚህ ማዕከል የተላኩ ሰዎች ስም ዝርዝር ተለጥፎ አየሁና ማንበብ ጀመርኩ፡፡ አንብቤ ስጨረስ ደነገጥኩ፡፡ ከተኮለኮለው ወደ ሃያ የሚጠጋ የስም ዝርዝር ውስጥ አንድም ዐማራ ዜጋ የለም፡፡ ሦስት ይሁኑ አራት ገደማ የደቡብና የኦሮሞ ስሞች አሉ – ቀሪው በሙሉ ከሐጎስና ከአብረኸት ውጪ ሌላ የለም፡፡ አዘንኩላቸው፤ አንዳንዴም አእምሮው በዘረኝነት ልምሻ፣ በጠባብነት ምችና በድንቁርና መብረቅ ለተመታ ሰውም ማዘን መጥፎ አይደለም – “እንደነዚህ አታድርገኝ” ብሎ መጸለይ ከተመሣሣይ የአስተሳሰብ መካንነትና የአመለካከት ድውይነት ይሠውራል፡፡ ረጋ ብለው ሲያስቡት እነዚህ ወንድሞቻችን የገቡበት የዘረኝነት አዘቅት ከመለኮታዊ መቅሰፍት የማይተናነስና በቁም ነፍስ ይማር የሚያሰኝ ትልቅ አደጋ ነው፡፡ እናም ለነሱም እንዘን፡፡
የአየር መንገዱ ዘበኛና ሴኪዩሪቲ ሁሉ ከትግራይ ነው የሚቀጠረው – ሁሉም የአየር መንገዱ የሥራ ዘርፍ  ሙሉ በሙሉ በትግሬ ሊሸፈን የቀረው ጥቂት ጊዜ ነው – ጥረቱም በስፋትና በጥልቀት ቀጥሏል፡፡ የመለስን ራዕይ እውን ለማድረግ የአየር መንገዱ የትግሬዎች የማኔጅመንት አካል ሌት ከቀን እየደከመ ነው፡፡ ጥቂት ወታደሮች ከጋምቤላ ተቀጥረው የብሔር ተዋፅዖ ያለ ለማስመሰል ይሞክራሉ እንጂ ሌላው ሁሉ ከትግራይ ነው የሚመጣው፤ እነዚህ ወታደሮችም አዲስ አበባንና የትግሬውን አገዛዝ መላመድ ስለሚቸግራቸው በየጊዜው ይጠፋሉ፡፡ እግዚኦ የሚያስብል ዘመን ውስጥ እንገኛለን፡፡ የሚገርመው ደግሞ ሌላው ዜጋ ሁሉ ለነዚህ እፍኝ ለማይሞሉ አጭበርባሪና ዘረኛ ትግሬዎች ሁሉን ነገር አስረክቦ እግሩ ባወጣ በመሰደድ በተዋራጅነት ለመኖር ራሱን ዝግጁ ማድረጉ ነው፡፡ ቆንጆ ሀገሩን ለወሮበላ አስረክቦ ራሱን የሚያጠፋና በከንቱ ማስኖ የሚቀር ዜጋ ቢኖር ኢትዮጵያዊ ዜጋ ብቻ ነው፡፡ የነሱን ዘረኝነት ስናገር እኔም ዘረኛ የሆንኩ እየመሰለኝ አፍራለሁ – እውነተኛ ኢትዮጵያዊ ነኝ ብሎ የሚያምን ሰው ዘረኛ ሊሆን እንደማይችል ሳስብ ግን እጽናናለሁ፡፡ በተለይ ዐማራ እስካሁን ያልሆነ ካሁን ወዲያ ዘረኛ ይሆናል ብዬ አልገምትምና ከኢትዮጵያዊነት ብቸኛ የመታገያ ሥልትና መንገድ ውጪ በወያኔ ቦይ ገብቶ እንዳይዳክር አደራችሁን እላለሁ፡፡ በርግጥ ዐማራ ሆኖ ስለዐማራ አለማሰብ ብልኅነት አይደለም፤ ወዶና ፈቅዶ ባልተፈጠረበት፣ ይሁነኝ ብሎ ባልሆነበት ማንነቱ ሲጨፈጨፍና ሲሳደድ እንኳንስን ተመሣሣይ ዕጣ የተፈረደበት ዜጋ ሌላውም ሊረዳውና ከዕልቂት ሊታደገው ሰብኣዊና ዜግነታዊ ግዴታ አለበት፡፡ ዐማራን እያስጨረሰው ያለው በዐማራነት ራሱን ለመፈረጅ መቸገሩ ነው፤ ከጥንት ከጧቱ ሰውነቱና ሥነ ልቦናው ሲታነፅ በኢትዮጵያዊነት እንጂ “ትግራይ አደይ፣ ዐምኻራ ሀድጊ፣ ዐምኻራን ተመንን እንተረከብኻ ቀዲምካ ንዐምኻራ በሎ…” እየተባለ በዘፈንም በሽለላና በቀረርቶም በወንድሞቹ ላይ እንዲዘምት በዐማራ ታሪካዊ ጠላቶችና በጣሊያን የባንዳ ልጆች እንደተገደደው የትግራዩ ወንድሜ ከልጅነቱ ጀምሮ የሚኮተኩተውና የሚያበረታታው አክራሪ ሰው ቢኖር ኖሮ ዐማራ ምን ሊሠራ እንደሚችል እኔ ሣልሆን ወያኔዎች ራሳቸው አሣምረው ያውቃሉ፡፡ ተኝቷል የሚባለው የዐማራው ልሂቅ እንኳን ይህን በዐማራው ላይ እየወረደ የሚገኘውን ወያኔያዊ ውርጅብኝ በማመንና ባለማመን መካከል ሆኖ በስማም እንደተባለበት ሰይጣን ዝም ብሎ ተቀምጧል – አብዛኛው፡፡ ስለዐማራው መብት ቢጮኽ ከወያኔዎቹ ያነሰ መስሎ ስለሚታየው ይመስለኛል በዝምታው ጸንቷል፡፡ ለማንኛውም የነበረ ያልነበር ይሆናል – ምንም ነገር ባለበት አይቀጥልም፤ የመደንቆሪያ ጊዜ አለ – የመስሚያ ጊዜም አለ፤ የልደት ቀን እንዳለ ሁሉ የመሞቻ ቀንም አለ፤ ለጥጋብ ቀን አለው – ለርሀብም እንዲሁ፡፡ አሁን ያለ የሚመስለውም ነገ የለም፡፡ ሞኝነትም ብልጥነትም ያረጃሉ፤ ይሞታሉም፡፡… የልብ መደፈንን በጊዜ ካልደረሱበትና መድሓኒት ካላገኙለት ግን ዳፋው ተዝቆ አያልቅም፡፡
ከአዲስ አበባ መቀሌ ስትገባ እዚያ ያሉ የአየር መንገዱ ሠራተኞች በግልጽ “እንኳን ወደ ኢትዮጵያ ዋና ከተማ በሰላም መጣችሁ” ይሉሃል፡፡ አፍረህ ዝም ትላለህ፡፡ አንድ ሰው ቢናገራቸው በቀጥታ ለዋናው የአየር መንገዱ ሥራ አስኪያጅ ለአቶ ተወልደ ይደውሉና የፈለጉትን እርምጃ ያስወስዱብሃል፡፡ አየር መንገዱ የተወልደ የግል ንብረት ያህል – በዚያውም የወያኔ የግል ሀብት ያህል እንጂ የኢትዮጵያ እንዳልሆነ ለማወቅ ብዙ ጉድ ትሰማለህ፤ ታያለህም፡፡ ጆሮህንና ዐይንህን ማመን እስኪያቅትህ በትንግርቱ ትገረማለህ፡፡ ለካንስ ዕድሜ የሰጠው ብዙ ያያል? በበኩሌ በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ ይህን ሁሉ ወያኔያዊ ድራማ አያለሁ ብዬ አላሰብኩም ነበር፡፡ በጣም ቸኮሉ፡፡ ይገርማል – ሰው ሲቸኩል ይሉኝታንና ሀፍረትን ጨርሶ ይረሳል ማለት ነው፡፡
ሠራተኛ ከየትም ሊቀጠር ይችላል – ከጎንደርም፣ ከባሕር ዳርም፣ ከድሬ ዳዋም ተቀጥሮ ሊመጣ ይችላል፡፡ ነገር ግን ከየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል ቢመጣ ወያኔዎች ያን ምልምል ተቀጣሪ ትግሬ መሆኑን ሳያረጋግጡ የአየር መንገዱን ግቢ አያስረግጡትም፡፡ እጅግ፣ እጅግ በጣም የሚገርሙ “ሰዎች” ናቸው፡፡
በሁሉም የሥራ ዘርፍ የነሱን ሰው ያሰለጥኑና ሌላውን አበሳጭተው ወይም አባረው በነሱ ይተካሉ፡፡ የሚተኳቸው ትግሬዎች ደግሞ በአብዛኛው ችሎታም ሆነ ዕውቀት ስለሌላቸው ሥራውን ያበላሻሉ፤ የብዙ ዓመት የሥራ ልምድና በቂ ሥልጠና የሚፈልግን አንድ ሥራ በለብ ለብ ለጥቂት ጊዜ በ”ሰለጠነ” ትግሬ መተካት ደግሞ በተለይ አየር መንገድን በመሰለ ተቋም ሊያስከትል የሚችለው ችግር ከባድ ነው፤ የሰውን ሕይወት በአየር ይዞ ለሚቀዝፍ የአየር ላይ መርከብ የወያኔ ዓይነት አሠራር ሀገራዊ ኪሣራን ማስከተሉ አይቀርም፡፡ ኦ..ኦ..ኦ… በጣም ንቀውናል ጎበዝ! “ትንሽ ሰው አያሸንፍህ” የሚባለው ምርቃት እንዴት ትክክለኛ ነው እባክህን! ትንሽ ሰው አሸንፎ አገር ያቀናበት ዘመን ደግሞ የትም የለም፡፡ ትንሽ ሰው ሲያሸንፍ ሁሉ ነገር ብርቅ ይሆንበትና አገር ምድሩን መቆሚያና መቀመጫ ያሳጣል፡፡ ወያኔዎችም እንዲህ ናቸው፡፡ ትንሽ ሰው ስል ግን በሰውነት አቋም ወይም በሥነ ተፈጥሯዊ የፍጥረታት ደረጃ ምደባ ሣይሆን በአስተሳሰብና ርዕዮተ ዓለም ረገድ ማለቴ ነው፡፡ በጅስምማ ሁላችን እኩልና የአዳምና የሔዋን ልጆች ነን፤ ግን አንዳችን ቃየልን ሌላኛችን አቤልን እየሆን ለዚህች አጭር ምድራዊ ዕድሜ እንባላለን፡፡
በዚሁ ሰሞን አንዱን የአየር መንገዱን ነባር ባለሙያ እንዲህ አሉት አሉ፡፡ “ይህን የያዝከውን ቦታ ልቀቅልን – በጣም እንፈልገዋለን፡፡ ደሞዝህን ግን አንቀንስብህም፤ ወደሌላ ቦታ እናዛውርህ፡፡…” እርሱም እምቢ የሚልበት አቅም የለውምና ሳይወድ በግዱ ለቀቀላቸው፡፡ ሥራውን ግን እያበለሻሹት ነው ይባላል – ወሬ ተደብቆ አይቀርም መቼም – ከዚያው አካባቢ የሚናፈስ ትኩስ መረጃ ነው፡፡ ሥራ ሲበላሽ ማየት ደግሞ አያስችልምና ባለሙያው በዳር ሆኖ እያገዛቸው ነው፡፡ እነሱ ስለሀገር ባይጨነቁ እርሱ ግን እነሱን አልሆነም፡፡
ኧረ ሌላ በኢሳት የሰማሁትን ጉድ ደግሞ ልንገራችሁ – ያልተከታተላችሁ ካላችሁ፡፡ አንድ ወልቃይቴ ከወንድማገኝ ጋሹ ጋር እየተወያዬ ነው፡፡ ወያኔዎች ስላደረሱበት በደልም እያብራራ ነው፡፡ እንዴት አምልጧቸው እንደተሰወረባቸው ሲናገር አልደረስኩበትም ወይም አልፎኛል፡፡ ያደረሱበት ስቃይና መከራ እጅግ የሚዘገንን መሆኑ እንዳለ ሆኖ ወደ አንድ ገደል ወስደው ምን እንዳሉት ሲናገር ብትሰሙት ከነዚህ ሰዎች ጋር ወደፊት እንዴት እንደምንኖር ግራ በመጋባት ትጨነቃላችሁ፡፡ “አየኸው ይሄን ገደል? ዘመዶችህን (ወልቃይቶችን ማለቱ ነው) እያመጣን የምንጥለው እዚህ ገደል ውስጥ ነው፡፡ አጥንታችሁ እዚህ ይከማቻል፡፡ ትግራይ ነፃ ስትወጣ በማሽን እየፈጨን ለትግራይ የእርሻ መሬቶች ማዳበሪያ እናደርገዋን … ምን አስቸኮለህ፤ አንተንም ገድለን እዚሁ እንጥልሃለን…” ነበር ያለው – ልበ ድፍኑ የወያኔ ካድሬ፡፡ ለመሆኑ ይህን ሁሉ ጭካኔ ማን አሰረጸባቸው? ለዐማራ ያላቸውስ ጥላቻ እንዴት አይበርድም? ትግራይስ ነፃ የምትወጣው ከማን ነው? ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያውያንን በምዕራቡ ዓለም ያልተቋረጠ ልዩ እገዛ ማሸነፋቸው ከ25 ዓመታት በኋላም እንደህልም የማይታመን ሆኖባቸዋል ማለት ይሆን? ጥልቅ እንቅልፉን የሚደቃው ዐማራ በህልማቸው እየመጣ እንዴት ቢያስፈራራቸው ይሆን እንዲህ አቅላቸውን ስተው የሚበረግጉትና በዚህን መሰል የማሰቃያ “ጥበብ” ዐማራውን የቁም ስቅል የሚያሣዩት?
እነዚህን ጉዶች ሰው ቢያቅተው ፈጣሪ እንዴት አቃተው? በኢትዮጵያና ሕዛቧ ላይ አለ አንዳች ዕረፍት ከ25 ለሚበልጡ ዓመታት ጥሬ እንትናቸውን ሲለቁብን፣ በትዕቢትና በዕብሪት ተነፍተው እንዲህ ሲያስታውኩብን ምን ነው ሃይ የሚላቸው አንድም ምድራዊም ይሁን ሰማያዊ አካል ጠፋ? “የኢትዮጵያ አምላክ” እየተባለ የሚንቆለጳጰሰው አምላከ ሰማይ ወምድር ምን ሆኖ ነው እንዲህ በኛ ላይ የጨከነው? ምን ኃጢኣተኞች ብንሆን  አለርህራሄ እንደክርስቶስ ይህን ያህል እንድንወገር መፍቀዱ ለምን ይሆን? ሀገረ ማርያም ኢትዮጵያ በነዚህ ጥፍራም ወያኔዎች ስትጠፋ፣ ባልተገራ ብልግናቸው እንዲህ ሲጨመላለቁብን በውነቱ ፈጣሪ በመንበሩ ካለ እንዴት አስቻለው? በትምህርትም ሆነ በልምድ እዚህ ግቡ የማይባሉ 27 ባላገር ትግሬዎች በዘረኝነት ከአንድ ክፍለ ሀገር ተለቅመው ይህን በዓለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ የነበረ አየር መንገድ እንዲቀላቀሉና በዘረኝነት ግማት እንዲያከረፉት ከተደረገ በሌላው ማኅበራዊና መንግሥታዊ ተቋምማ ከዚህ የበለጠ ወንጀል እንዴት አይሠራ? የድፍረታቸው ምንጭ ምን ሊሆን ይችላል? የኛ ፍርሀት ወይንስ የነሱ “ጀግንነት”? የኛ “ትግስት” ወይንስ የነሱ ጀብድ? ምሥጢሩ ምን ይሆን?  ጥቂት ሺዎች በብዙ ሚሊዮኖች ዘንድ እንዲህ ግፍ ሊሠሩ የሚችሉበት አገባብ አልገባህ ብሎኝ ተቸግሬያለሁና የሚያብራራልኝ ባገኝ እጅግ በጣም ደስ ይለኛል፡፡ ሕይወት ብቻ ሣትሆን ኢትዮጵያም ዕንቆቅልሽ ሆነችብኝ – መፈቻው የራቀ ዕንቆቅልሽ፤ ሀገር የማይሰጥበት ክፍለ ዘመናዊ ምሥጢር፡፡  ጥቂቶች በአንደርባቸው ሚሊዮኖችን አፍዝዘው ወደ ተናጋሪ ዕቃነት(ዞምቤነት) የለወጡባት የምትገርም ሀገር – ኢትዮጵያ! ሁሉም ነገር ግራ የሚያጋባበት ሁኔታ የተፈጠረባት አስገራሚ ሀገር፡፡ እንደብልኅ በዐርባ ቀን ቀርቶ እንደሞኝ እንኳን በዐርባ ዓመት ልብ መግዛት ያልተቻለባት የዘመናችን ባቢሎንያውያን ሀገር – ኢትዮጵያ፡፡ ወደኋላ እንጂ ወደፊት የማይሮጥባት፣ ባሉበት ቆሞ መቅረትም ራሱ ዕርም ሆኖባት ወዳልነበረችበት የጥፋት ዘመን የኋሊት ሽምጥ የምትጋልብ ሀገር – አቢሲንያ፡፡
ለኢትዮጵያ ቆመናል የምትሉ የሰላማዊም ሆናችሁ የብረት ትግል ተቃዋሚዎች፣ የሰብኣዊ መብት ተሟጋቾች፣ በውጪም ሆነ በውስጥ የምትገኙ የነፃነት ፋኖዎች፣ … አሁንና ዛሬ ወዴት አላችሁ? ከዚህ የበለጠ ውርደት የት አለ? ከዚህ በላይስ ምን እስኪያደርጉን ትጠብቃላችሁ? ሥጋችንን እስኪበሉ? ደማችንን በስሪንጅ እስኪመጡ? እነዚህ ቫምፓየሮች ከዚህ በላይ ምን እስኪያደርጉን ትጠብቃላችሁ?
“ወደሽን ቆማጢት…” እንዳትሉኝ እንጂ ሁሉም የመንግሥት ሠራተኛ ትግሬ ይሁን – ለጊዜው ግዴለም እንበል፡፡ ግን የተማረና በአግባቡ የሠለጠነ ትግሬ ቢሆን ምናለበት? ወያኔዎች ሆይ! ሁሉንም ዜጎች ከሥራ አውጡና በትግሬ ተኩ፤ ጀምራችሁ እያጠናቀቃችሁት እንደምትገኙት ከዳር እዳር ሁሉንም ሙያዎችና የጥቅም ቦታዎች እናንተው ያዙ – ግን እባካችሁን ሰዎቻችሁ በቂ ሥልጠናና የማኅበራዊ ተግባቦት ችሎታ እንዲኖራቸው አድርጉ – የምትቃዡባትን የትግራይ “ሪፓፕሊክ”ን መሥርታችሁ እስክንገላገላችሁ ድረስ ያው እናንተም እንደኛው ኢትዮጵያውያን መባላችሁ አይልቀረምና ስለናንተ ፀያፍ የዘረኝነት ተግባር እኛም እያፈርንባችሁ ነው – ከሚደርስብን ቁሣዊና ሥነ ልቦናዊ ጉዳት ባልተናነሰ በእናንተ ምክንያት ሀፍረቱም አሸማቀቀን – እውነቴን ነው – ከናንተ ጋር የአንዲት ሀገር ዜጋ መባሉ ራሱ በበኩሌ ቃላት ከሚገልጹት በላይ እያሣፈረኝ ነው – 27 ሆስተስ ከትግራይ ብቻ? ይህ ተግባር ብቻውን አይደለም ኢትዮጵያውያንን በእንስሳዊነት የጋራ ተፈጥሮ ምክንያት ዓሣማና ጅቦችንም በሀፍረት አንገት ሊያስደፋ የሚችል አጸያፊ ወያኔያዊ ድርጊት ነው(እናንተን እስፖንሰር ያደረጉ ምዕራባውያን ፀረ-ኢትዮጵያ ኃይሎች ይህን ተግባራችሁን አያውቁም አልልም፤ ከነሱም ሆነ ከናንተ ከዚህ የሚብስ ግፍ እንጂ መልካም ነገርን አልጠብቅም – ተፈጥሯችሁን ለአፍታም አትዘነጉምና)፡፡ በዋናነት ታዲያ ዐውሬ ትግሬዎችን ከጫካና እልም ካለ ገጠር እያመጣችሁ በአንጻራዊነት ሻል ባለ የሥልጣኔና የንቃተ ኅሊና ደረጃ በሚገኝ ሕዝብ ላይ እንደውሻ ጃዝ አትበሉ፡፡ ሕዝቡን እያስመረሩና እያስለቀሱ፣ የሀገሪቱንም ምስል እያበላሹ ነውና በጣም እየተዋረድን ነው፡፡ እርግጥ ነው – ኢትዮጵያን ማዋረድና ከምድረ ገጽ ማጥፋት ትልቁ አጀንዳችሁ መሆኑን እናውቃለን – ግን በቅጡ አጥፉን እባካችሁን፡፡ ፕሮፌሽናል በሆነ ሥልጡን መንገድ አጥፉን እንጂ ይህን ያህል የለዬላችሁ ‹ፋራ› አትሁኑ፡፡
ወያኔዎች ፈጣሪንም አግተው እንደያዙ አሁን አሁን መጠራጠር ጀምሬያለሁ፤ እንዲያ ባይሆን ይህን ሁሉ ግፍ እየሠሩ ሃይ የሚላቸው ባልጠፋ ነበር እላለሁ፡፡ …. በርግጥም ለኢትዮጵያ አሁን ያልታዘነ መቼም አይታዘንላትም፡፡ 27 ሰው ከአንድ ቀየ? የመንግሥት ተቋማትን ሁሉ በአንድ ክልል ሰዎች ማስያዝ? ማን ናቸው … እኚያ ስመጥር ፕሮፌሰር አሁን የት ነው ያሉት? የለም፣ የለም… እርግጥ ነው … ትግሬ ሣይሆኑ የሆኖሉሉ ዜጎች ናቸው በወያኔ እየተጠቀሙ ያሉት፡፡ ትግሬዎች ምን በወጣቸው? 27… ወይ መድሓኔ ዓለም… ምኑን አመጣህብን፤ ምን ጉድ ነው እያሳየኸን ያለኸው… ለማንኛውም እግዜሩን እግዜር ይይለት፡፡
“ሰውነት ቢያብጥ በምላጭ ይበጣል – ምላጭ ቢያብጥ በምን ይበጣል?….”  አዎ፣ አሁንም እውነት ነው –  “እህል ቢያንቅ በውኃ ይዋጣል፤ ውኃ ቢያንቅስ በምን ይዋጣል?” ፍርዱን ለራሱ ለፈጣሪ ሰጥቻለሁ፡፡