Friday 9 January 2015

በመላው ሀገሪቱ ለምትገኙ ለአንድነት ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች በሙሉ! ወሳኝ የትግል ምእራፍና ወሳኝ ሰዓት ላይ እንገኛለን !!!

ኢህአዲግና ምርጫ ቦርድ በስውር ከተደራጁ ህገ-ወጥ የማፊያ ቡድኖች ጋር በመሆን አይበገሬና በቆራጥ ሰላማዊ የነፃነት አርበኞች የተገነባውን አንድነት ፓርቲን ላለፉት ጊዜያት ፓርቲያችንን ለመበታተንና የህዝብ አለኝታነቱን በማሳጣት ከምርጫ ለማስወጣትና ሰላማዊ የትግል ሂደቱን ለማኮላሸት ያልፈነቀሉት ድንጋይ እንዳልነበረ፤..መላው ለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያውያንና የአንድነት አባላት ሲከታተሉት የነበረ ሀቅ ነው፡፡ ……በኢህአዲግ የበላይነት የሚመራው ምርጫ ቦርድ፤….. በህወሀት ካድሬዎች ተቀባብሎ የሚሰጠውን አንድነትን ኢላማ ያደረገ ጥይት ለመተኮስ ወደኋላ አልተመለሰም፡፡ ….ከጥቂት የስርአቱ ተላላኪ በአንድነት ውስጥ የተሰገሰጉ ሰርጎ ገቦችና በገንዘብ የተገዙ የሀገርም ሆነ የወገን ፍቅር የሌላቸው ባንዳዎች ጋር በመደራጀት አንድነትን የመፈረካከስ ውጥናቸውን ለማሳካት በሚሊየን የሚቆጠር ገንዘብ በጅተው ሲንቀሳቀሱ ሰንብተዋል፡፡ ….ለነዚህ ህገ-ወጥ የማፊያ ቡድኖች፤…የህጋዊ ነን ጥያቄ የሽፋን ምላሽ የሰጠው ምርጫ ቦርድ፤….የአንድነት አመራሮች ላይ ለህጋዊና ሀገራዊ ፋይዳ ላለው ጉዳይ የማያዥጎደጉድትን ደብዳቤ ህፀፅ እየፈለጉ የተልእኮ ምእራፋቸውን ጀመሩ፡፡ ነግር ግን ጉዳዩን በታላቅ ፖለቲካዊ ብስለትና ህጋዊ አካሄድ ሲመረምሩትና ሲከታተሉት የነበሩት በሳል የአንድነት አመራሮች፤…የውሀ ቀጠነ አይነት የምርጫ ቦርድ ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ በመስጠት የፓርውን ህጋዊነት ያረጋገጡ ቢሆንም፤….አላማው ‹‹የኢህአዲግንና የባንዳ ሰርጎ ገቦቹን ተልእኮ ማስፈፀም የሆነው ምርጫ ቦርድ ግን በሰላማዊ ትግል ውስጥ ታሪክ ሊሽረው የማይችል ጥቁር ነጥብ አሳርፎ፤……አንድነትን የመበታተን ተልእኮውን በማገዝ ላይ ይገኛል፡፡ …በዚሁም መሰረት ይኸን ጠንካራ ህዝባዊ ፓርቲ መርህን እናስከብራለን የሚሉት የህወሀት የማደጎ ልጆች የሆኑት የምርጫ ቦርድ ሀላፊ ተብዬዎች መርህን ባልተከተለ መልኩ አንድነትና መኢአድ በምርጫው አይሳተፉም ሲሉ በድፍረት በሚዲያዎች ሲዘባርቁ ተሰሙ፡፡ …… ይህ ግን ምን ያህል ዋጋ እንደሚያስከፍላቸው ጠንቅቀው አለመረዳታቸውና አንድነት እነርሱ በሚያደርጉት ስውር ደባ ሰላማዊ ትግሉን በማጠናከር፤መከፈል ያለበትን መስዋትነት በመክፈል እንደሚገፋበት ባለመገንዘባቸው ይኸን ታሪካዊ ቅሌት ሊሰሩ ተገዷል፡፡
ውድ የአንድነት ደጋፊና አባላት፤……ይሄ ‹‹አንድነትን ከምርጫ አትሳተፍም›› የሚል ውሳኔ ሁላችንም የምንመለከተው ‹‹ባቄላ አለቀ ቢሉት፤…..›› እንደተባለው የሀገራችን ብሂል ነው፡፡ ….አንድነት በህዝብ ያለውን ሰፊ መሰረት በመጠቀም የተዘጋውን በር አስከፍታለሁ ብሎ ያለቅድመ ሁኔታ በምርጫው ለመሳተፍ ሲወስን ምርጫውን ያለማንም አለማቀፍም ሆነ ሀገራዊ ታዛቢዎች እራሱ አዘጋጅቶ ሊበላው ያቀደው ዋንጫ መሆኑን ሳንረዳ ቀርተን አይደለም፡፡ …… አንድነት ፓርቲ በገዢው የኢህአዲግ መንግስትም ሆነ በአጃካሪዎቹ ምርጫ ቦርድና ሌሎች ተላላኪዎች ሴራ ጥቂት እንኳ አይደነብርም እንደውም ትግሉን አጠናክሮ ይገፋበታል እንጂ፤…….ወደደም ጠላም አንድነት በ2007 ዓ.ም ለለውጥ የሚያደርገውን ግስጋሴ አንዳችም አካል ሊገታው እንደማይችል ሊረዱት ይገባል፡፡ ……እናም የአንድነት አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲያችን የሚሻለውን አማራጭ ሁሉ ተጠቅሞ፤….አልሆን ሲለው ለሚወስደው ቆራጥ ፖለቲካዊ ውሳኔ ከወዲሁ ቀበቷችንን ጠበቅ በማድረግ፤…… በዚህ ወሳኝ የትግል ምእራፍ ላይ ኢህአዲግንም ሆነ የማደጎ ልጆቹን አንገት ማስደፋት ይጠበቅብናል፡፡ ድል የሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብ ነው!!! …….. ለለውጥ እንነሳ!!!10153833_587630041337455_4078181881316786241_n

No comments:

Post a Comment