Saturday 10 January 2015

የአንድነት የምስራቅ ቀጠና አደራጅ የሆነው ምርቱ ጉታ በደህንነት ሐይሎች ታፈነ!

ምርቱ ጉታ የአዳማ ከተማ አንድነት ሰብሳቢ ሆኖ በ2006ዓ/ም ሲያገለግል ጀምሮ ክትትል ሲደረግበትና ዛቻ ሲፈጸምበት ቆይቶ በዛሬው ዕለት ወደአዲስ አበባ ለመሄድ ከቤቱ በማላዳ ሲወጣ በተከታተሉት የደህንነት ሰዎች አማካኝነት ታፍኖ መወሰዱን ከአይን ምስክሮች ለማወቅ ተችሏል፡፡በመልካም ስነምግባሩና ለትውልዱ ካለው ተቆርቋሪነት የተነሳ በሚኖርበት ቀበሌ የህዝብ ቤተመጽሀፍት በማቋቋም ምስጋና የተቸረው ይኸው ወጣት በህዝቡ ላይ ያለውን ጫና ለመቀነስ ከሚያደርገው ጥረት በተጨማሪ በ1997 ዓ/ም በአንድ ሲቪል ድርጅት አማካኝነት ስለምርጫ አፈጻጸም በሚያስተምርበት ወቅት ነበር ስለፖለቲካ ግንዛቤውን ማስፋት የጀመረው፡፤በዚያም ወቅት በሲቪል ድርጅቱ የተሰጠውን ስራ በመስራት ላ ሳለ ወከባና ክትትል ሲደረግበት ወደ አዲስ አበባ በመሄድ የሆቴል ሙያን በማጥናት በሸራተንናበኢትዮጵያ አየር መንገድ ሲሰራ ቆይቷል፡፡አንድነት ፓርቲ ሲመሰረትም ከወጣቶቹ የፓርቲው አባላት ጋር በመሆን ፓርቲውን መስርቷል፡፡
‹‹ልጅህን ብታሳድግ ይሻልኃል፡፡››እየተባለ ማስፈራረሪያ ሲደርስበት የከረመው ምርቱ በዛው ዕለት በማለዳ ለስብሰባ ወደ አዲስአባባ ሊጓዝ ከቤቱ ሲወጣ ጀምሮ በመኪና ሲከታተሉት የነበሩት ሰዎች ማንነታቸው ተገልጦ ከኋላዋ ክፍት በሆነች መኪና ላይ በአንድ ደህንነትና በሶስት ፖሊሶች ታጅቦ መወሰዱን የአይን ዕማኞች ገልጸዋል፡፡
የአዳማ አንድነት ጽ/ቤት በደርጅታችን የወጣቶች ጉዳይ ሐላፊና በቀጠናው አደራጅ ላይ የደረሰውን አፈና ለማጣራት በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡እስካሁን በሁለት የከተማው ፖሊስ ጣቢያዎች ባደረግነው ጥያቄ ለም የሚል ምላሽ ተሰጥቶናል፡፡በሰላማዊ ትግላችን ኢህአዴግን ከስልጣን ለማውረድ የምናደርገውን ትግል እንቀጥላለን፡፤
ድል የሕዝብ ነው!
የአዳማ አንድነት ጽ/ቤት10930100_1513059112292103_1900285716832279613_n

No comments:

Post a Comment