Monday 22 February 2016

ሰልፈኞች በኮፋሌ የሕወሓት (ኤፈርት) ንብረት የሆነውን የጭነት መኪና በእሳት አጋዩት

ሰልፈኞች በኮፋሌ የሕወሓት (ኤፈርት) ንብረት የሆነውን የጭነት መኪና በእሳት አጋዩት

Share5  2795  5 
 Share6

kofale
(ዘ-ሐበሻ) በኦሮሚያ ክልል ባለው ተቃውሞ ወደዚያው ክልል እንዳይሄዱ ማስጠንቀቂያ ከተሰጣቸው የሕወሓት ኤፈርት እና የአላሙዲ መኪኖች ናቸው:: ይህን ተላልፈው በሚገኙት ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ ቀድሞ በተሰጠው ማስጠንቀቂያ መሠረት ሰልፈኞች ንብረትነቱ የኤፈርት የሆነውን የጭነት መኪና በ እሳት አነደዱት::
በአጋዚ ሰራዊት ጥይት እየተተኮሰበት በኮፈሌ ተቃውሞውን የቀጠለው ሕዝብ የጭነት መኪናውን ያነደደው ለስ ዓቱ ያለውን ተቃውሞ ለማሳየት ነው ተብሏል::
ሰልፈኞቹ መኪናውን ሲያቃጥ;ኡት በረዳቱና በሹፌሩ ላይ ምንም ዓይነት ጉዳት አለማድረሳቸው ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ ጠቁሟል::
በኦሮሚያ ክልል ለሾፌሮች ማስጠንቀቂያ መሰጠቱና የአላሙዲን እና የኤፈርትን መኪኖች የማይነዱ አሽከርካሪዎች ሰልፈኞችን ሲያገኙ ነጭ ጨርቅ ካውለበለቡ ማንም እንደማይነካቸው መግለጹ ይታወሳል::

No comments:

Post a Comment